TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የዩኒቨርሲቲ_መውጫ_ፈተና

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ከሁሉም መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የሚመረቁ ተማሪዎች በሰለጠኑባቸው ሙያዎች ብቁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ እንዲወስዱ የሚጠበቀውን የመውጫ ፈተና ወደ ተግባር እንዲገባ ዝግጅት መደረጉን አስታውቋል።

የመውጫ ፈተናውን በተመለከተ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንቶች በተገኙበት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምክክር እየተደረገ ይገኛል።

የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የምክክር መድረክ ባዘጋጀው ውይይት የመውጫ ፈተናው አስፈላጊነት፤ የፈተናው አወጣጥና አፈታተን እንዲሁም በተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር እየተደረገበት ነው።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ፤ መንግስት በመጪዎቹ አምስት ዓመታት የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ጠንካራ ትግበራ እና ርምጃዎችን እንደሚወስድ አንስተዋል።

በቀጣይ አምስት ዓመታት አዲስ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ እንደማይኖር የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይልቁንም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አቅም እና ጥራት ማሻሻል ላይ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

በሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙ ተመራቂ ተማራዎች ፈተናዉን እንዲወስዱ በቂ ዝግጅት መደረጉን ጠቁመዋል።

የመውጫ ፈተናው በእያንዳንዱ ዩኒቨርሲቲ በየሙያው እና ትምህርት ዘርፍ ተዘጋጅቶ የሚሰጥ ሲሆን ለዚህም ትግበራ ፖሊሲና ዝርዝር ማስፈፀሚያ መመሪያ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

በህግና በህክምና ሙያ የሚሰጠው የመውጫ ፈተናና የብቃት ማረጋገጫ ፍተሻ እንደ ልምድ ይወሰዳል ተብሏል።

ምንጭ፦ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ

@tikvahuniversity
👎1.27K👍93453😱47😢38👏26🥰18😭1
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከፍተኛ ጫና እያሳደረብን ነው " የ2013 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈትነው ምደባ የሚጠባበቁ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች ምደባው እንዲፋጠንለቸው በድጋሚ ጠይቀዋል። የመጀመሪያውን ዙር ፈተና ተፈትነው እና ውጤታቸውን አውቀው ቤታቸው የተቀመጡ ተማሪዎች 6ኛ ወራቸውን ሊደፍኑ እየተቃረቡ ይገኛሉ። እስካሁን ምደባ ይፋ የሚሆንበት ቀን ይፋ ያልተደረገ ሲሆን ይህ ሁኔታ ተማሪዎችና ወላጆችን ጫና ውስጥ…
#የዩኒቨርሲቲ_ምደባ

የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው መግለጫ ፤ ከተያዘው ሳምንት መጨረሻ ጀምሮ የ2013 ዓ.ም ብሄራዊ ፈተና ተፈታኞች የዩኒቨርሲቲ ምደባቸውን ማወቅ ይችላሉ ሲል አሳውቋል።

መቼ ? በየትኛው ቀን ? ስለሚለው ጉዳይ አንድ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊ ቁርጥ ያለውን ቀን ለማሳወቅ እየተሰራ መሆኑን እና ሚኒስቴሩ ቀኑን እንደሚያሳውቁ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
👍1.05K👎321😢69👏6056😱44
#የዩኒቨርሲቲ_መምህራን !

በዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበራት በኩል የቀረቡ ጥያቄዎች ፦

• መንግሥትን የደመወዝ ጭማሪ እና የዕርከን ዕድገት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

• ለዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ እና ቴክኒካል ረዳቶች የተሰራውን አዲሱን የስራ ደረጃ ማሻሻያ JEG በተመለከተ ቅሬታ አላቸው።

• የመምህራን የቤት አበልን በተመለከተ በፍጥነት አሁን ያለው የቤት ኪራይ ዋጋ ከግምት አስገብቶ ተሻሽሎ ተግባራዊ እንዲደረገ ጠይቀዋል።

• በመንግስት የተደረገው የደረጃ ማሻሻያ ረጅም ጊዜ በዩንቨርሲቲ ያስተማሩ መምህራንን ልምድ ያላገናዘበ በመሆኑና በመምህራን መካከል በቀጣይ ፍትሀዊ የደምወዝ ልዩነት እንዲኖር ስለማያስችል የደረጃ ማሻሻየው የመምህራንን ልምድ እና ማዕረግ ያገናዘበ እንዲሆን ጠይቀዋል።

• የረዳት ፕሮፌሰር የአካዳሚክ ማዕረግ ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታ የ3ኛ ዲግሪ መደረጉን በተመለከተ ያለን ቅሬታ አላቸው።

• የአካዳሚክ ቴክኒክ ረዳቶች ዝቅተኛው ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ የመጀመሪያ ዲግሪ መሆኑ ላይ አቤቱታ አላቸው።

• የቺፍ ቴክኒካል ረዳት II የትምህርት ደረጃን ፒ ኤችዲ ዲግሪ መሆኑም ላይ አቤቱታ አላቸው።

ጥያቄዎቻችን መልስ ይሰጣቸው እያሉ የሚገኙት መምህራኑ ይህ ካልሆነ እስከ ስራ የማቆም አድማ መምታት ድረስ ዕርምጃ እንደሚወስዱ ገልፀዋል።

👉 ትምህርት ሚኒስቴር ለሪፖርተር ፥ " ጥያቄ እንዳለ እናውቃለን። ነገር ግን አሁን ላይ ለውጦች ለማምጣት ጥናት እየተካሄደ ነው። ከዚህ ባለፈ የምንለው ነገር የለም። የደመወዝ ጉዳይ የትምህርት ሚኒስቴር ብቻ አይደለም የሲቪል ሰርቪስ ጉዳይም ነው "

ያንብቡ : telegra.ph/ETH-08-07-2

@tikvahethiopia
👍1.5K👎20066🙏62👏44🥰24😢13