TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፒው ሪሰርች የተባለው አለም አቀፍ የጥናትና ምርምር ማእከል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ቁጥር 36 ሚልዮን እንደሆነ እና ይህም ከአውሮፓ እና ሩስያ ውጪ ከፍተኛው ቁጥር መሆኑን አዲስ ባወጣው ሪፖርት አሳወቀ።

ምንጭ ፦ ፒው ሪሰርች

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሳዑዲ አረቢያ በሙስና ጠርጥራ ያሰረቻቸውን ከፍተኛ ባለስልጣናትና ባለሀብቶችን ገንዘብ እና ንብረት እንደምትወርስ አስታወቀች፡፡ ሀገሪቱ ንብረቶችን የመውረሻ የጊዜ ሰሌዳ ባታስቀመጥም የሮይተርስ ምንጮች 1‚700 የባንክ ሂሳቦች
መታገዳቸውን ገልጸዋል።

ምንጭ ፦ ሮይተርስ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቃባይ አቶ መለስ አለም ተናገሩ..

“በኢትዮጵያ መንግስት እና በግብጽ መንግስት መካከል ጠንካራ የትብብር ግንኙነት አለ፡፡ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብቷን መጠቀም በተመለከተ የማንንም
ወገን ወይም አካል ይሁንታ መጠየቅ አይጠበቅባትም”

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እንደ ሮይተርስ ዘገባ በሳዑዲ አረቢያ በእስር ላይ ያሉት ሼክ መሐመድ አላሙዲ የ10.4 ቢሊዮን ዶላር ሀብት ባለቤት ናቸዉ፡፡ ሼህ አላሙዲ በግንባታ፣
ግብርናና የኃይል ዘርፎች በኢትዮጵያ፣ ሳዑዲ አረቢያና ስዊዲን የተሰማሩ በርካታ ድርጅቶች አሏቸው።

ምንጭ ፦ ሮይተርስ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አንዳንድ ተራ የሚመስሉ ንግግሮች በሰዎች ላይ ከባድ ተፅእኖን ይፈጥራሉና ዘወትር መልካም ንግግር ተናገር።

የጥላቻ በር ይዘጋ!

💚💛❤️ሰላም እደሩ💚💛❤️

@tsegabwolde @tikvahethiopia
መቄዶንያ! በ3ብር መኪኖች ፣ ባጃጅ ፣ ሞተር! የርሶ የቱ ይሆን?ይላኩ!የሚላክሎን ያንብቡ!አረጋውያን ይርዱ!አሁን ይላኩ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወጣት ንግስት ይርጋ ዛሬ ኅዳር 1/2010 ዓ.ም ለፍርድ በልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት ትቀርባለች።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሀገር ኩራት የሆነው ቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ የገጣጠማቸው ዘመናዊ የተማሪዎች አውቶብሶች በአዲስ አበባ ከተማ አገልግሎት መስጠት ሊጀምሩ ነው።
በአውሮፓና በአሜሪካ ተማሪዎች ብቻ የሚመላለሡበት የተማሪዎች አውቶብስ በያዝነው ህዳር ወር በአዲስ አበባ አገልግሎት መስጠት ሊጀምር ነው። 100 አውቶብሶች ተገጣጥመው አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ ሆነዋል። 30 የሚደርሱ አውቶብሶች ሰሞኑን ተማሪዎችን ማመላለስ ይጀምራሉ። የአውቶብሶቹን የመገጣጠም ስራ የሰራው ቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ ነው።

ምንጭ ፦ ጋዜጠኛ ጥኡመልሳን ሰለሞን(ከአዲስ አውቶሞቲቭ)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የደብረብርሀን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጥያቄ ይዘው ቢወጡም ዩኒቨርሲቲው አረጋግቶ መልሷቸዋል።
በደብረብርሀን የሰዎች ህይወት እየጠፋ ነው ሰዎች እየተሰወሩ ነው ያሉ የደብረብርሀን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በግቢው ሰልፍ በማድረግ ዩኒቨርሲቲውን ስለ ጉዳዩ እንዲያሰረዳቸው ሊጠይቁ ቢነሱም አስተዳደሩ አረጋግቶ መልሷቸዋል። ተማሪዎች እንደሚሉት ባለፈው ረቡዕ ዕለት አንዲት ልጅ ህይወቷ አልፏል። በተጨማሪም አንዲት ልጅ ትላንት ለሊት ጠፍታ እስካሁን የገባችበት አልታወቀም።

በግቢው ከምሽት 2 ሰዓት በኃላ መንቀሳቀስ እንደሚያስፈራ እና በጭንቀት ምክንያትም ትምህርታቸው ላይ ተፅእኖ እያደረ መሆኑን መረጃውን የላኩልኝ ተማሪዎች ገልፀውልኛል።

በአካባቢው ሰዎች ለወንዝ እየተገበሩ ነው የሚል ወሬ ቢሰማም ሁኔታውን ለማረጋገጥ እድል አላገኘሁም።

ምንጭ ፦ የደብረብርሀን ተማሪዎች

@tikvahethiopia
ግጭት የነበረባቸው የኦሮሚያና የሶማሌ ክልል ድንበር አካባቢዎች ወደ ሰላምና መረጋጋት ተመልሰዋል ሲሉ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ትላንት ማምሻውን በሰጡት መግለጫ ገልፀዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ባለሥልጣን ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍላችሁ፣ ያለ ፌርማታችሁ የሚያስወርዳችሁ፣
የሚሰድባችሁና የሚያንጓጥጣችሁ የታክሲ ሹፌርና ረዳት ከገጠማችሁ በነፃ የስልክ መስመር 888 ጠቁሙኝ እስከ 1 ሺ ብር ድረስ እቀጣላችኋለው ብሏል፡፡

ምንጭ ፦ ቴዎድሮስ ብርሃኑ (ሸገር 102.1 FM)

@tikvahethiopia @tsegabwolde
‹አቶ አባዱላ በቴሌቪዥን ወጥተው
መናገራቸው ስህተት ነው››

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አባዱላ ገመዳ ከአፈ ጉባዔነት ለመልቀቅ ጥያቄ ስለማቅረባቸው በቴሌቪዥን ወጥተው መናገራቸው ስህተት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ትላንት አመሻሹን በጽሕፈት ቤታቸው በሰጡት
መግለጫ፣ ከሪፖርተር በኢሕአዴግ ውስጥ ስላለ ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት ጥያቄ ቀርቦላቸዋል ነው ይኼን ምላሽ የሰጡት፡፡

‹‹ ኢሕአዴግ የሚታወቅበት ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት በአሁኑ ወቅት አለ ማለት ይቻላል ወይ ? አፈ ጉባዔ አባዱላ የኦሮሞ ሕዝብን መብት ለማስከበር እታገላለው ማለታቸው የዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት
በኢሕአዴግ ውስጥ መጥፋቱን እንደሚያመላክትና ይህም ኢሕአዴግን ሊበትነው አይችልም ወይ?›› በሚል ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ፣

‹‹ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት የማይገረሰስ የኢሕአዴግ መርህ ነው፤›› ሲሉ መልሰዋል፡፡ "አፈ ጉባዔ አባዱላ መልቀቂያ ስለማቅረባቸው ሪፖርተር በመዘገቡና ከወጣ አይቀር ሐሳቤን በደንብ መግለጽ አለብኝ በማለት ወደ ሚዲያ ሊሄዱ ችለዋል። ወደ ሚዲያ መሄዳቸው ስህተት ነው። ምክንያቱም በውስጣችን እንፈታው ነበር። ሆኖም አሁንም በድርድር ላይ የለ ጉዳይ በመሆኑ ዲሞክራሲያዊ ማእከላዊነትን ጥሰዋል ማለት አይቻልም፤” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

ነገር ግን ወደ ሚዲያ መውጣታቸው ስህተት ነበር ብለዋል፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ጉዳይ ኢሕአዴግን የሚፈርስ አድርጎ ማሰብ ድርጅቱን አለማወቅ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም፣ ‹‹ታላቁ መሪያችን አቶ መለስ ዜናዊ በሞቱ ጊዜ እንኳን አልተበተነም፤›› ብለዋል፡፡

አቶ አባዱላ ከአፈ ጉባዔነታቸው የሥራ መልቀቂያ ካስገቡ በኋላ ጥያቄያቸው ተቀባይነት ሲያገኝ ምክንያታቸውን እንደሚገልጹ መግለጫ ሰጥተው ነበር፡፡

ከዚያም ኃላፊነታቸውን የለቀቁት የድርጅታቸው ኦሕዴድ እና የሕዝባቸው ክብር በመነካቱ መሆኑን መግለጻቸው ይታወሳል፡፡ በቅርቡም ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም የአፈ ጉባዔው የሥራ የመልቀቂያ ጥያቄ ላይ እየተደራደሩ መሆናቸውን ሪፖርተር መዘገቡ ይታወሳል፡፡

ምንጭ ፦ ዮሀንስ አምበርብር(ሪፖርተር)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1
ከሀዋሳ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ተከታይ የተላከ ጥንቃቄ አዘል ጥቆማ ...

በሀዋሳ ከተማ በተለይ 07 አካባቢ ከፍተኛ የሆነ ዝርፊያ እየተፈፀመ ነው። ሰዎች በገዛ ሀገራቸው በምሽት መንቀሳቀስ ስጋት እንየፈጠረባቸው መሆኑን መልዕክቱን ያደረሰኝ ወዳጄ ነግሮኛል። ትንሽ ጨለም ባሉ አካባቢዎች ሰዎች እየተወጉ ንብረታቸው እየተዘረፍ ነው። በየዕለቱ የሰዎች በስለት መወጋት የተለመደ ነገር እየሆነ እንደመጣም ገልጾልኛል። ይህን መልዕክት የላከልኝ ወዳጄ እንደነገረኝ ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች ባሳለፍነው ሳምንት ከአንድ ጓደኛው ላይ ሁለት ስልኮችን ደብድበው መቀበላቸውን ገልፆልኛል።

የከተማው ፖሊስ ይህን ነገር በመከታተል ሰዎችን ከዝርፊያ ሊጠብቅ እና ወንጀለኞችንም ለፍርድ ማቅረብ አለበት እንዲሁም የከተማው አስተዳደር ለወንጀል አመቺ የሆኑ ቦታዎች በማጥራት ማብራት የመትከል ስራ ቢሰራ የሚል መልዕክት በቻናሉ ስም ለማስተላለፍ እወዳለሁ።

ምንጭ ፦ ባባ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሀረማያ ዩኒቨርሲቲ በቅጡ ትምህርት ሳይጀመር ከሳምንታት በላይ ተቆጥሯል።

የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ትላንት ከተማሪዎች ጋር በነበረው ስብሰባ መግባባት ላይ ሳይደርስ ቀርቷል።

የዩኒቨርሲቲው አስተዳደሮች በግቢው ውስጥ የሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ግቢውን ለቆ አይወጣም በማለታቸው ተማሪዎች ፌደራሎች እስካልወጡ ትምህርት አንማርም በሚለው አቋማቸው ፀንተዋል።

ዩኒቨርሲቲው ትላንት በግዳጅ ተማሪዎች ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ቢያዝም ዛሬ አስተማሪ እንጂ ተማሪ በክፍል ሳይገኝ ቀርቷል።

በዚህ ምክንያት ተማሪዎች መጉላላት እየደረሰባቸው ነው። በርካታ መሸፈን ያለባቸውን ትምህርቶች ሳይማሩ እስከ ዛሬ ቆይተዋል በዚህም ጊዚያቸው እየባከነ መሆኑን ይናገራሉ።

ትምህርት ሚኒስቴር ለዚህ ጉዳይ እልባት እንዲሰጥ እና በግቢው የሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ለቆ እንዲወጣ እንዲሁም ከተማሪዎች የሚነሱ ጥያቄዎች ተመልሰው ወደ መደበኛ ትምህርት ስርአት እንዲመለሱ ፍላጎታቸው እና ጥያቄያቸው መሆኑን የግቢው ተማሪዎች ገልፀዋል።

ምንጭ ፦ የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለሀዘን፣ለፍቅር፣ለደስታ፣ለችግር፣ማነው የሚመረጥ ለሰው፤ከሰው ወዲያ በምድር።

💚💛❤️ሰላም እደሩ💚💛❤️

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የህወሓት ነባር ታጋይና በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ትግራይን በመወከል ምክትል ፕሬዝዳንት የነበሩት የአይተ ተክለወይኒ ሰሞኑን ለሚዲያና በስብሰባ የተናገሯቸው ብዙውን ሰው ያስገረሙ ንግግሮች

(1) "የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ጉባኤ መቐለ ቢካሄድ ጥሩ ነው፣ ማታ ማታ ከትግራይ ቆነጃጅት ጋር ዘና ትላላችሁ"

(2) "እኔ የድርጅቴ ሲኒዬር ስትራቴጅስት እኮ ነኝ፣ ሃይለማሪያም ምን ያውቃል፣ ከፈለገ አምጣውና እንከራከር፣ አናስተምረዋለን"

(3) የኢትዮጵያ ቡና ክለብ የቦርድ ሊቀመንበር የሆኑትን አዛውንት መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞን ደግሞ በስብሰባ መሃል "አንተ አደናቃፊ ሰውዬ ዝምበል"

(4) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት የሆኑትን ጁነዲን በሻን ደግሞ በኢትዮ FM 107.8 ላይ "ጁነዲንን አትቀባጥር አትመረጥም ብዬዋለሁ"

የትግራይ ክልል በትላንትናው ዕለት የሰውዬውን ውክልና እንዳነሳ
አሳውቋል።

ምንጭ፦ ENF

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዛሬ ጥዋት ያደረጉት ሰልፍ። ተማሪዎቹ በካፌ አገልግሎት ጥራት ማነስ ላይ ያላቸውን ቅሬታ አሰምተዋል።
የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው አግልግሎት ላይ ያላቸውን ቅሬታ እና ሌሎች ጥያቄዎቻቸውን ይዘው ሰላማዊ ሰልፍ ወጡ። ተማሪዎቹ እንደገለፁት ዩኒቨርሲቲው የሚያቀርብላቸው ምግብ ጥራቱን ያልጠበቀ እና ከደረጃ በታች ነው ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ተማሪዎቹ የክልሉ ፕሬዘዳት አቶ ለማ መገርሳ እንዲያነጋግሯቸው እንደሚፈልጉም ገልፀዋል።

ምንጭ፦ የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች

@tsegabwolde @tikvahethiopia