TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
🔘 ያለ ፀሎት አትውጣ
🔘 ያለ ተስፋ አትሩር
🔘 ያለ አላማ አትጓዝ

💚💛❤️ሰላም እደሩ💚💛❤️

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ነገ እሁድ ጥቅምት 26 በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ በዝግጅት ላይ የነበረው ሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ሰልፍ እዉቅና እንደተነፈገው አስታወቀ።

የሰማያዊ ፓርቲው አቶ ጌታነህ ባልቻ እንደገለፁት “የከንቲባው አማካሪ ‘ጥበቃ የማደርግበት ኃይል የለኝም፤ ሰልፉን እንድታደርጉ እውቅና አንሰጣችሁም’ ሲሉ መለሱን፡፡ ማዘጋጃ ቤቱ እውቅና ስላልሰጠው ሰልፉን ለማድረግ እንቸገራለን” ብለዋል።

ምንጭ ፦ ዶቼ ቬለ

@tikvahethiopia @tsegabwolde
የአማራና የኦሮሞ ህዝቦች የምክክር መድረክ የኢትዮጵያን ህዝብ መዝሙር በመዘመር እና በቅርቡ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች የህሊና ጸሎት በማድረግ ተጀምሯል፡፡

ምንጭ ፦ አብመድ

@tikvahethiopia @tsegabwolde
በመቀሌ ሮማናት አደባባይ የተጠራው ሰልፍ ያለምንም ችግር በሰላም ተጠናቋል።

@tikvahethiopia @tsegabwolde
ተጨማሪ ፎቶዎች መቀሌ ሮማናት አደባባይ የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ።

@tikvahethiopia @tsegabwolde
ባህርዳር : "አብሮነታችን ለሰላማችን፣ሰላማችን ለአብሮነታችን" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ የሚገኘው የአማራ እና የኦሮሞ ህዝቦች የምክክር መድረክ እንደቀጠለ ነው፡፡

ምንጭ፦ አብመድ

@tikvahethiopia @tsegabwolde
እንዲህም ያለ ስልጣን አለ...

የቂ/ክ/ከ/ነዋ/ፎረም ዋና ፀሀፊ እና የመልካም አስተዳደር ሰብሳቢ እንዲሁም የክ/ከተማው የዜብራ የግራ መንገድ የመንገድ ደህንነት ኮሚቴ ዋና ሰብሳቢ

ምንጭ ፦ በፌስቡክ ሲሰራጭ የተገኘ

@tikvahethiopia @tsegabwolde
በጅማ ስታዲየም እየተደረገ በሚገኘው የመጀመሪያው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሜርሊግ የጅማ አባ ጅፋር እና ሀዋሳ ከነማ ጨዋታ ላይ የተገኘው የፖሊስ ቁጥር አስገራሚ ነው።

ምንጭ ፦ BeSu J-T
@tikvahethiopia
ማስታወቂያ : የሁለተኛ ዓመትና ከዚያ በላይ ሆናችሁ በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ስትማሩ ለነበራችሁ የኦሮሚያ ክልል ተወላጅ ተማሪዎች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ስትማሩ ለነበራችሁ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ተወላጅ ተማሪዎች፡-

ተከስቶ በነበረው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት ተማሪዎች በጊዜያዊነት ወደ ሌሎች የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ተዛውረው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ መንግስት
በወሰነው መሰረት ጊዜያዊ ምደባ የተሰጣችሁ ስለሆነ በጊዜያዊነት ወደ ተመደባችሁበት የከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት በመሄድ ትምህርታችሁን እንድትከታተሉ እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፦

ጊዜያዊ ምደባው በትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ www.moe.gov.et ላይ ይገኛል፡፡

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ.ትምህርት ሚኒስቴር

@tsegabwolde @tikvahethiopia
🔘⚪️ሰበር ዜና⚪️🔘

ሁለተኛ አመት እና ከዚያ በላይ የሆኑ በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን የሚከታተሉ የኦሮሞ ተወላጅ ተማሪዎች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ የሶማሌ ክልል ተወላጅ ተማሪዎች በጊዜያዊነት በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ተደረገ።

ተከስቶ በነበረው የፀጥታ መደፍረስ ሳቢያ ተማሪዎቹ በጊዜያዊነት በሌሎች የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ተዛውረው ትምህርታቸውን እንዲከትታተሉ መንግስት ወስኗል።

ተማሪዎች ወደተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ በመሄድ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉም ትምህርት ሚንስቴር አሳስቧል።

ጊዜያዊ ምደባውን ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገፅ www.moe.gov.et ላይ ማየት ይችላሉ።

ምንጭ ፦ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚንስቴር

@tsegabwolde @tikvahethiopia
1
በሀረማያ ዩኒቨርሲቲ እንደ አዲስ የተመደባችሁ የ1ኛ አመት ተማሪዎች እና በጊዜያዊነት የተመደባችሁ የሁለተኛ አመት እና ከዚያ በላይ ተማሪዎች የምዝገባ ቀን ሰኞ ጥቅምት 27 መሆኑን አውቃችሁ በተመደባችሁበት ኮሌጅ ቀርባችሁ ምዝገባ እንድታከናውኑ ዩኒቨርስቲው ይጠይቃል።

@tsegbawolde @tikvahethiopia
ከሶማሌ ክልል (ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ) ኦሮሚያ ክልል ወደሚገኙ እና ወደ ሌሎች የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች በጊዜያዊነት የተመደባችሁ የሁለተኛ አመት እና ከዚያ በላይ ተማሪዎች የተመደባችሁበትን የትምህርት ተቋም ከላይ ተመልከቱ።☝️☝️ ©MoE
http://www.moe.gov.et/

ምንጭ ፦ የትምህርት ሚኒስቴር , @roobel

@tikvahethiopia @tsegabwolde
"ምንም እንኳን ቀምሼው ባላውቅም ኢትዮጲያዊነት ልክ እንደ ሀሺሽ ሱስ ነው።"

ኦቦ ለማ መገርሳ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት በባህርዳሩ መድረክ ከተናገሩት።

@tikvahethiopia @tsegabwolde
🕊1
የኢትዮጵያ ወታደሮች ወደ ሶማሊያ መግባታቸውን የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማረጋገጡን አሶሴትድ ፕሬስ ዘገበ።የዶሎው ከተማ ነዋሪዎች ወታደሮቹ በታንኮችና በብረትለበስ ተሽከርካሪዎች ሆነው ወደሶማሊያ መግባታቸውን ተናግረዋል።

ምንጭ ፦ AP

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የመታጠቢያ ቤት እጥረት እንዳለ ተማሪዎች ተናገሩ።
የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ አመት ተማሪዎች በተቋሙ የመታጠቢያ ቤት እጥረት እንዳለ ገለፁ። በፎቶ አስደግፈው በላኩት መረጃም ተማሪዎች የሚታጠቡት ሜዳ ላይ ነው። በየህንፃው መተጠቢያ ቤት እንዳለ የሚናገሩት ተማሪዎች መታጠቢያ ቤቶቹ እንደማይከፈቱ እና ተማሪዎችም እንደማይጠቀሙበት ይገልፃሉ። ወደ ነባር ተማሪዎች ማደሪያ መታጠቢያ ቤቶች ስላሉ አንዳንዴም እዛ እየሄዱ እንደሚታጠቡ ጨምረው ተናግረዋል።

በየህንፃው ያሉት መታጠቢያ ቤቶች ለምንም አገልግሎት እንደተሰሩ ግራ እንደገባቸው የሚገልፁት ተማሪዎች ተቋሙ ይህን ችግር ሊፈታ ይገባል ብለዋል።

ምንጭ፦ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ተማሪዎች

@tsegabwolde @tikvahethiopia