ለምን አልሰለምኩም?
2.91K subscribers
51 photos
10 videos
42 files
187 links
ይህ ቻነል ቅዱሱ የአምላካችን ቃል በ1ኛ ጴጥ 3:15 ላይ ባዘዘን መሠረት ሙስሊም ወገኖቻችን በክርስትና ላይ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች እና ትችቶች ምላሽ የምንሰጥበት፣ ጥያቄዎቻቸውን ከነመልሳቸው በየጊዜው እያዘጋጀን የምንለጥፍበት፣ ለምን እንዳልሰለምን ፣ እንደማንሰልምም የምንገልጥበት ፣ የኢስላምን የጨለማ መንገድነት በእውነት ብርሀን የሚገልጡ ፅሁፎችን የምናስነብብበት መድረክ ነው።
Download Telegram
እግረ መንገዴን ቴሌግራም ገብቼ የሰዎችን ውይይት እየሰማሁ፣ አንድ የሙስሊሞች ግሩፕ ውስጥ አንዱ ክርስቲያን ልጅ ስለ እዮብ 33:4 ጠቅሶ መንፈስ ቅዱስ ፈጣሪ መሆኑን እንደሚያሳይ ይነግረዋል። ክፍሉ እንዲህ ይላል:
"4፤ የእግዚአብሔር መንፈስ ፈጠረኝ፥ ሁሉንም የሚችል የአምላክ እስትንፋስ ሕይወት ሰጠኝ።"

ከዛ፣ ሙስሊሙ ልጅ፣ የግሪክ ሰፕቱያጅንቱ እንደዛ አያሳይም። የአረፍተ ነገሩ ባለቤት "እግዚያብሄር" ነው የሚለው። ስለዚህ የእግዚያብሔር መንፈስ ነው እንጂ መንፈሱ እግዚያብሔር አይደለም ይለዋል። probably ልጁ ከኡዝታዞቹ የሰማውን ነው እንጂ ቋንቋውን አያውቅም። ለማንኛውም ክፍሉን እንመልከት።

Job 33:4
[4]πνεῦμα θεῖον τὸ ποιῆσάν με πνοὴ δὲ παντοκράτορος ἡ διδάσκουσά με

ክፍሉን ከግሪኩ በቀጥታ ሲተረጎም "Divine spirit made me መሎኮታዊው መንፈስ ሰራኝ πνεῦμα θεῖον τὸ ποιῆσάν με" ይሆናል። ምክኒያቱም

1. θεῖον የሚለው ቃል "እግዚያብሄር" አይደለም። መሃል ላይ ያለችው iota "ῖ" ትርጉሙን ትለውጠዋለች። ትርጉሙም "መለኮት" ወይም ደግሞ "አማልክት gods" ማለት ነው። ከአውዱ የምንረዳው ግን ብዛትን ሳይሆን ስለ አንዱ መለኮት ስለሆን ትርጉሙ መለኮት ይሆናል ማለት ነው።

2. θεῖον ግዑዝ ፆታ ነው። እግዚያብሔር ግን θεος ሲሆን፣ ግራማቲካሊ ማስኩሊን ፆታ ነው። የመለኮት masculine gender ደግሞ θεῖος ነው። እዚህ ክፍል ላይ ግን አጨራረሱ ተቀይሮ θεῖον የሆነው፣ መንፈስ፣ የሚለው የግሪክ ቃል πνεῦμα በተፈጥሮ grammatically neuter ወይም ግዑዝ ስለሆነ ነው። ስለዚህ፣ "መለኮት" የሚለው ቃል በግሪክ ሰዋሰዋዊ ህግ የዓረፍተ ነገሩን ባለ ቤት ሲገልፅ በ case, gender, number መመሳሰል ስላለበት ወደ ግዑዝ ተቀይሯል። ይህ ማለት #መንፈስ የአረፍተ ነገሩ ባለ ቤት እንጂ ገላጭ አለመሆኑን ያሳያል። ስለዚህ የሙስሊሞቹ ሙግት ውድቅ ነው ማለት ነው። የአማርኛ መፅሐፍ ቅዱሳችንም የትርጉም ጉድለት እንዳለበት ማወቁ አይከፋም።

መልካም ቀን!!

@Jesuscrucified