ለምን አልሰለምኩም?
2.89K subscribers
51 photos
10 videos
42 files
187 links
ይህ ቻነል ቅዱሱ የአምላካችን ቃል በ1ኛ ጴጥ 3:15 ላይ ባዘዘን መሠረት ሙስሊም ወገኖቻችን በክርስትና ላይ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች እና ትችቶች ምላሽ የምንሰጥበት፣ ጥያቄዎቻቸውን ከነመልሳቸው በየጊዜው እያዘጋጀን የምንለጥፍበት፣ ለምን እንዳልሰለምን ፣ እንደማንሰልምም የምንገልጥበት ፣ የኢስላምን የጨለማ መንገድነት በእውነት ብርሀን የሚገልጡ ፅሁፎችን የምናስነብብበት መድረክ ነው።
Download Telegram
በነገራችን ላይ ዮሐንስ 10:30 ላይ "እኔ እና አብ አንድ ነን" የሚለውን ሙስሊሞች ግሪኩን ሲጠቃቅሱት እያየሁ ነው። heis, hen, mia የሚለውን ትርጉም ሲሰጡት አይቻለው። የአላማ አንድነት፣ የህላዌ አንድነት...ምናምን። እንዲህ አይነት ትርጉም በአጭሩ በዘመናዊው ቋንቋ "ሳክስ" ይባላል።😊 ከዬትኛውም ተአማኒ ግሪክ ኤግዝጄስስ ሙግትህን ማስደገፍ አትችልም። እነኚህ ቃላቶች ትርጉማቸው "አንድ" ማለት ሲሆን በግሪክ ግራማቲካል ፆታ ብቻ ነው የሚለያቸው። እሱም እንደ adjective ከመጡ ከሚገልፁት ባለቤት ጋር ለመስማማት ነው፣ except in few exceptions። አንዱ እንዲህ አይነት exception ምሳሌ፣ እራሱ ዮሐንስ 10:30 ነው። በዚህ ክፍል ላይ፣ ግሪኩ "ኤጎ ካይ ሆ ፓቴር #ሄን ኤስሜን" ይላል። 'ኤጎ' ማለት እኔ ሲሆን 'ፓቴር' ማለት ደግሞ አብ ማለት ነው። ሁለቱም masculine gender ናቸው። ስለዚህ፣ በኖርማል ግራማቲካል ሕግ ቀጥሎ መምጣት የነበረበት "ሄስ"(masculine) እንጂ "ሄን"(neuter) መሆን አልነበረበትም። ነገር ግን፣ እንደ ታላቁ ስኮላር ሮበርትሰን "Word pictures of the NT" ፣ #ሄን የተጠቀመበት ምክንያት አብ እና ወልድ አንድ አካል አለመሆናቸውን ለማሳየት እና እንዲያውም በEssence አንድ መሆናቸውን ለማሳየት እንደሆነ ፅፏል።
ዮሓኒስ ደግሞ ቴዎሎጂካል መልዕክቱን ለማስረዳት፣ አንዳንዴ የሰዋ ሰው ህጎችን እንደሚጠመዝዝ የታወቀ ነው። ለምሳሌ፣ Dr. T.Cowden Laughling በ1902 የPHD dissertationኑን በራዕይ መፅሃፍ ውስጥ ዮሓኒስ እንዴት አድርጎ ግራመር እንደተጠቀመ የሚያጠና The Solecism of the Apocalypse ብሎ የፃፈውን ደስ የሚል ጥናት ማየት ይቻላል።

@Jesuscrucified
@Jesuscrucified