(ለአባቴ)
ደህና ነኝ፡፡
መንታላ ገላዬን ችጋር ቢደቁሰው
ፍቅር ስጠቀለል ክፋትን ብጎርሰው
ህልሜ ቢጨናገፍ መንገዴ ቢያደክመኝ
እንዳለኸኝ ሳስብ ተስፋ አለኝ ደና ነኝ፡፡
፥
ማግኘትና ማጣት ቢፈራረቁብኝ
ዋዛ ሆኜ ብታይ ቁምነገር ቢያጡብኝ
ፈርሷል ብለው ሲያልፉ ሰባብረውት ውስጤን
አንተ የኔ ጋሻ ነገዬን በማጤን
በርታ 'እንጂ ስትለኝ
ተዛ እለት ጀምሮ ተስፋ አለኝ ደህና ነኝ፡፡
---
ምን አፍራሽ ቢበዛ ከየጎዳናው ጫፍ
ያዘን እንጉርጉሮ በአካላቴ ቢያልፍ
ብጎብጥ ባቀረቅር 'መላም የለህ' ብሰኝ
አባቴ ፊቴ ቁም
ስትኖረኝ ተስፋ አለኝ፡፡ ስትኖረኝ ደህና ነኝ፡፡
#ELU @Username_under_construction
@GETEM
@GETEM
ደህና ነኝ፡፡
መንታላ ገላዬን ችጋር ቢደቁሰው
ፍቅር ስጠቀለል ክፋትን ብጎርሰው
ህልሜ ቢጨናገፍ መንገዴ ቢያደክመኝ
እንዳለኸኝ ሳስብ ተስፋ አለኝ ደና ነኝ፡፡
፥
ማግኘትና ማጣት ቢፈራረቁብኝ
ዋዛ ሆኜ ብታይ ቁምነገር ቢያጡብኝ
ፈርሷል ብለው ሲያልፉ ሰባብረውት ውስጤን
አንተ የኔ ጋሻ ነገዬን በማጤን
በርታ 'እንጂ ስትለኝ
ተዛ እለት ጀምሮ ተስፋ አለኝ ደህና ነኝ፡፡
---
ምን አፍራሽ ቢበዛ ከየጎዳናው ጫፍ
ያዘን እንጉርጉሮ በአካላቴ ቢያልፍ
ብጎብጥ ባቀረቅር 'መላም የለህ' ብሰኝ
አባቴ ፊቴ ቁም
ስትኖረኝ ተስፋ አለኝ፡፡ ስትኖረኝ ደህና ነኝ፡፡
#ELU @Username_under_construction
@GETEM
@GETEM