አለሁ እኔ ደግሞ
።።።።።።።።።።።።
ከሰማየሰማይ፥
በፍቅር ተስቦ ፥ ሞቴን በሞቱ እየገደለ
የሞት ሸለቆዬን፥
በህይወት ፅኑ አለት ፥ እየደለደለ
አለኝ አንድ ንጉስ፥ሳልወደው ሚወደኝ
ዘወትር በፍቅር ድምጽ፥
ማልዶ ሚቀሰቅስ ፥ ደጁ የሚወስደኝ።
ደግሞ አለኝ አንድ ሰው፥
ሳይወደኝ ምወደው ፥ ሲሸሸኝ አጥብቆ
ልቤን መርጋት ከልካይ፥
በሱ፥በፍቅሩ እና ፥ በናፍቆቱ ሰብቆ።
አመታት አልፈዋል ፥
በሄደበት ሁሉ ፥ስሄድ ስከተለው
እግሬ በጉልበቱ፥
ነግቶ ማረፊያዬን ፥ በሩ ላይ ተከለው።
ይኼው እዚህ ደግሞ፥
ባለንፁሕ ልቡ፥ ፍቅሬን ብቻ ሽቶ
ከበሬ ማይጠፋ፥ቀን ጠብቶና መሽቶ።
"አንጀትን ባንጀት ነው"፥
የሚል ዘዬ አንግቦ ፥ ክራር ከጁ አያጣም
ክራሩን ሲገርፈው፥
ሆዴ የገባ ብርድ ፥ እስካመት አይወጣም።
አለሁ እኔ ደግሞ፥
ማረፊያ መርከቤ ፥ ቀድማ የሰጠመች
ባይዋሯ ነፍሴ፥
ከሀኪሟ ርቃ ፥
(በመነጠል ደዌ ፥ ላትድን የታመመች።
አለሁ እኔ ደግሞ፥
ከሶስት አንዳቸውን፥ማመስገን ያልታደልኩ
ከአምላኬም መቅደስ፥
ባዶነት አናውጾኝ ፥ ወጥቼ የኮበለልኩ።
አለሁ እኔ ደግሞ፥
መሻቴን ሳሳድድ፥
ብርቱ ናፋቂዬን ፥ በርትቼ ምገፋ
በወዳቂው 'ምትስቅ፥
ተስፋ ቆራጭ ነፍሴ፥ ሞትን ተደግፋ።
አለሁ እኔ ደግሞ፥
ከእግዜሬ ጋራ ፥ ሙግት የምገጥም
የህይወትን ባህር፥
ላላይ እየሸሸሁ፥
የምኞት ባህር ውሰጥ፥ ገብቼ ምሰጥም።
በቃኝ ኧረ በቃኝ!
መሻቴን ቀብሬ ፥
ስጦታዬን ላንሳ ፥ ሻቼን ግባ ልበል
የገፋኝ ይገፋ፥
ስወድቅ ያነሳኝን ፥ በደስታ ልቀበል።
ግባ ሙሽራዬ፥
የኔ ጽኑ ወዳጅ ፥ ያነጸህ መገፋት
አድሳት ህይወቴን፥
ከሙታን ባህር ላይ፥ ለህይወት ጭለፋት።
እንሆ መቅደሴ፥
እጆቼ ይቀጡ፥ በሩን የዘጉብህ
ልቤ ይቅረብ ለፍርድ፥
ፍቅርን ስትዘምር ፥ ስላቅ የሳቀብህ።
እግዜሩም ታረቀኝ፥
ግብዝ ሰውነቴ ፥
ባርከህ በሰጠኸው ፥ ሳይልህ ተመስገን
ሲባክን መኖሩ፥
እርቃኑን ሊሸሽግ፥ ሽቶ ሌላ ተገን።
ያልከውን ሊቀበል፥
ፍቃድህን አምኖ ፥ ፍስሃን ሸምቷል
ተመስገን አምላኬ፥
አዲሱ እኔነቴ
በሙላት ተሰርቶ ፥ ባዶነቴ ሞቷል።
@getem
@getem
@paappii
#dagim hiwot
።።።።።።።።።።።።
ከሰማየሰማይ፥
በፍቅር ተስቦ ፥ ሞቴን በሞቱ እየገደለ
የሞት ሸለቆዬን፥
በህይወት ፅኑ አለት ፥ እየደለደለ
አለኝ አንድ ንጉስ፥ሳልወደው ሚወደኝ
ዘወትር በፍቅር ድምጽ፥
ማልዶ ሚቀሰቅስ ፥ ደጁ የሚወስደኝ።
ደግሞ አለኝ አንድ ሰው፥
ሳይወደኝ ምወደው ፥ ሲሸሸኝ አጥብቆ
ልቤን መርጋት ከልካይ፥
በሱ፥በፍቅሩ እና ፥ በናፍቆቱ ሰብቆ።
አመታት አልፈዋል ፥
በሄደበት ሁሉ ፥ስሄድ ስከተለው
እግሬ በጉልበቱ፥
ነግቶ ማረፊያዬን ፥ በሩ ላይ ተከለው።
ይኼው እዚህ ደግሞ፥
ባለንፁሕ ልቡ፥ ፍቅሬን ብቻ ሽቶ
ከበሬ ማይጠፋ፥ቀን ጠብቶና መሽቶ።
"አንጀትን ባንጀት ነው"፥
የሚል ዘዬ አንግቦ ፥ ክራር ከጁ አያጣም
ክራሩን ሲገርፈው፥
ሆዴ የገባ ብርድ ፥ እስካመት አይወጣም።
አለሁ እኔ ደግሞ፥
ማረፊያ መርከቤ ፥ ቀድማ የሰጠመች
ባይዋሯ ነፍሴ፥
ከሀኪሟ ርቃ ፥
(በመነጠል ደዌ ፥ ላትድን የታመመች።
አለሁ እኔ ደግሞ፥
ከሶስት አንዳቸውን፥ማመስገን ያልታደልኩ
ከአምላኬም መቅደስ፥
ባዶነት አናውጾኝ ፥ ወጥቼ የኮበለልኩ።
አለሁ እኔ ደግሞ፥
መሻቴን ሳሳድድ፥
ብርቱ ናፋቂዬን ፥ በርትቼ ምገፋ
በወዳቂው 'ምትስቅ፥
ተስፋ ቆራጭ ነፍሴ፥ ሞትን ተደግፋ።
አለሁ እኔ ደግሞ፥
ከእግዜሬ ጋራ ፥ ሙግት የምገጥም
የህይወትን ባህር፥
ላላይ እየሸሸሁ፥
የምኞት ባህር ውሰጥ፥ ገብቼ ምሰጥም።
በቃኝ ኧረ በቃኝ!
መሻቴን ቀብሬ ፥
ስጦታዬን ላንሳ ፥ ሻቼን ግባ ልበል
የገፋኝ ይገፋ፥
ስወድቅ ያነሳኝን ፥ በደስታ ልቀበል።
ግባ ሙሽራዬ፥
የኔ ጽኑ ወዳጅ ፥ ያነጸህ መገፋት
አድሳት ህይወቴን፥
ከሙታን ባህር ላይ፥ ለህይወት ጭለፋት።
እንሆ መቅደሴ፥
እጆቼ ይቀጡ፥ በሩን የዘጉብህ
ልቤ ይቅረብ ለፍርድ፥
ፍቅርን ስትዘምር ፥ ስላቅ የሳቀብህ።
እግዜሩም ታረቀኝ፥
ግብዝ ሰውነቴ ፥
ባርከህ በሰጠኸው ፥ ሳይልህ ተመስገን
ሲባክን መኖሩ፥
እርቃኑን ሊሸሽግ፥ ሽቶ ሌላ ተገን።
ያልከውን ሊቀበል፥
ፍቃድህን አምኖ ፥ ፍስሃን ሸምቷል
ተመስገን አምላኬ፥
አዲሱ እኔነቴ
በሙላት ተሰርቶ ፥ ባዶነቴ ሞቷል።
@getem
@getem
@paappii
#dagim hiwot
👍1
"በሰማይ ላይ ተሾምኩ"
_______________
ከዐይኑ ስር ልሰወር
ደማና ጋርጄ፣ ሰማይ ጉያ ገባሁ
የኔ ሰማይ እሱ፣
እንደሆነ ሲገባኝ፣
ኮኮቦች ለቅሜ፣ እልፍኜን ገነባው
@Getem
@Getem
@paappii
#Dagim_hiwot
_______________
ከዐይኑ ስር ልሰወር
ደማና ጋርጄ፣ ሰማይ ጉያ ገባሁ
የኔ ሰማይ እሱ፣
እንደሆነ ሲገባኝ፣
ኮኮቦች ለቅሜ፣ እልፍኜን ገነባው
@Getem
@Getem
@paappii
#Dagim_hiwot
👍1