አሳዛኝ ዜና
ጋዜጠኛ፤ ተርጓሚ እና ደራሲ #ግርማ_ለማ ደሳለኝ ህይወታቸው አለፈ፡፡
★የቅርብ ዘመድ፤ ወገን ስለሌላቸው በማዘጋጃ ቤት ሊቀበሩ ነበር ተብሏል፡፡
በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ “እንዲህ ቢሆንስ” “ድሮና ዘንድሮ” “ሃሳብ አለኝ” የተባሉ አምዶች አዘጋጅ ነበሩ፤ የዘመን መፅሄት መስራች እና የአምድ አዘጋጅ ነበሩ፤ ከ1983 በኋላ መፅሄቶች በብዛት ለገበያ መውጣት በጀመሩበት ወቅት “አፍሮዳይት” እና “ዛቬራ” በተሰኙ መፅሄቶች ላይ በ ዋና አዘጋጅነት ሰርተዋል፡፡
በሬዲዮ ፋና በአስተዳዳሪነት ና በ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ ተወዳጅ የነበረውን “ታቦት ፍለጋ” በሚል ርዕስ በተከታታይ ይወጡ የነበሩ የግርሃም ኩክ ስራዎችም የእሳቸው ትርጉሞች ነበሩ፡፡
እንዲሁም አሁን ከህትመት በወጣችው ኢትዮ ቻናል ጋዜጣ ላይ በ “ማህደር” አምድ ተወዳጅ የነበረውን እና በኋላም በመፅሃፍ ታትሞ ለአንባቢ የቀረበውን “የንጉሱ ገመና” የተሰኘ ፅሁፍ እና ሌሎች ስራዎችንም ያስነበቡት አንጋፋው ጋዜጠኛ ፣ጸሃፊ፣ ደራሲና አማካሪ የነበሩት ግርማ ለማ ደሳለኝ በዛሬው እለትሰ ህይወታቸው አልፏል፡፡
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በህዝብ አስተዳደር በከፍተኛ ማዕረግ በዲግሪ የተመረቁት ጋሽ ግርማ “ የንጉሱ ገመና” ከተሰኘው መፅሀፍ በተጨማሪ “የካህሊል ጅብራን ምርጥ ስራዎች” የተሰኘ ትርጉም ስራ ለአንባቢ ያቀረቡ እና ለህትመት ያልበቁ አምስት ያህል የትርጉምና የራሳቸው ወጥ ስራዎች ነበሯቸው፡፡ባለሙያው ከላይ የተዘረዘሩት ሁሉ የትርፍ ሰዓትስራዎቻቸው ሲሆኑ በመደበኛነት የሂውማን ሪሶርስ ማኔጅመንት አማካሪ ነበሩ፡፡
በህይወታቸው መጨረሻ በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ሲሰሩ የነበሩ ሲሆን በጠና ታመው አልጋ ላይ ከዋሉ መቆየታቸውን የገለጹልን ምንጮቻችን በዛሬው እለት በተከራዩበት ቤት ህይወታቸው ማለፉን ተከትሎ የቅርብ ዘመድም ሆነ ወገን ስለሌላቸው አስክሬናቸው በመንግስት( ማዘጋጃ ቤት) ሊቀበር እንደነበርም ታውቋል፡፡
ጉዳዩን ከሰሙት መካከል የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ባልደረባ የሆነው ጋዜጠኛ ጌታቸው ለማ እና ባለሙያውን የሚያውቁ ጥቂት ወዳጆቹ ሁኔታውን ለፕሬስ ድርጅት እና ለ ቀድሞ ባልደረቦቹ በማሳወቅ እና በማስተባበር በመንግስት እንዳይቀበር ያደረጉ ሲሆን በነገው እለትም በ6፡00 አዲሱ ገበያ በሚገኘው እግዚአብሄር አብ ቤተክርስትያን የቀብር ስነ ስርዓቱ የሚፈጸም መሆኑን ገልጸው በሙያው ላይ ያሉ ሁሉ ለአንጋፋው ባለሙያ ሽኝት እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡
ምንጭ፦ ሸገር ታይምስ
--------------------------------------
ሰው እያለ አጠገባችን ፤
መልካም ስሙን ፣ መጥራት ሲያመን
<< ሰው ካልሞተ ፣ ወይ ካልሄደ
አይነሳም >> እንላለን።
እንዲህ እያልን ፣
አበባውን ቀጥፈን ጥለን
አበባ እናስቀምጣለን።
((( ነብይ መኮንን )))
እስከመቼ ይሆን ..??? ዛሬም የነብይ መኮንን ግጥም እንደ #ትንቢት እኛ ሀገር በደንብ ይሰራል
ግርማ ለማ ግን አበባ ቀርቶበት....በወጉ የሚቀብረው የለም .....? ዘመድ ይቅር..ወገን ምን ማለት ነው.....?
እስከዛሬ የፃፈልን ነገሮች ስናነበብ የነበርነው ለባዳ ህዝብ ነበር?
እዚህ ሀገር ዘፋኝ እና አርቲስት ብቻ ነው አሸሼ ገዳሜ ሚበዛለት...? ደራሲዋቻችን ከሰጡን ነገር አንፃር የሚኖሩት ኑሮ ለነሱ ሚገባ ነው..? አሁን ጭራሽ ሲሞቱ ሚቀብራቸው .....ከዚህ በላይ ልብ የሚሰብር ነገር አለ..?😭😭😭😭😭😭😭😭😭
@balmbaras
@getem
@getem
ጋዜጠኛ፤ ተርጓሚ እና ደራሲ #ግርማ_ለማ ደሳለኝ ህይወታቸው አለፈ፡፡
★የቅርብ ዘመድ፤ ወገን ስለሌላቸው በማዘጋጃ ቤት ሊቀበሩ ነበር ተብሏል፡፡
በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ “እንዲህ ቢሆንስ” “ድሮና ዘንድሮ” “ሃሳብ አለኝ” የተባሉ አምዶች አዘጋጅ ነበሩ፤ የዘመን መፅሄት መስራች እና የአምድ አዘጋጅ ነበሩ፤ ከ1983 በኋላ መፅሄቶች በብዛት ለገበያ መውጣት በጀመሩበት ወቅት “አፍሮዳይት” እና “ዛቬራ” በተሰኙ መፅሄቶች ላይ በ ዋና አዘጋጅነት ሰርተዋል፡፡
በሬዲዮ ፋና በአስተዳዳሪነት ና በ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ ተወዳጅ የነበረውን “ታቦት ፍለጋ” በሚል ርዕስ በተከታታይ ይወጡ የነበሩ የግርሃም ኩክ ስራዎችም የእሳቸው ትርጉሞች ነበሩ፡፡
እንዲሁም አሁን ከህትመት በወጣችው ኢትዮ ቻናል ጋዜጣ ላይ በ “ማህደር” አምድ ተወዳጅ የነበረውን እና በኋላም በመፅሃፍ ታትሞ ለአንባቢ የቀረበውን “የንጉሱ ገመና” የተሰኘ ፅሁፍ እና ሌሎች ስራዎችንም ያስነበቡት አንጋፋው ጋዜጠኛ ፣ጸሃፊ፣ ደራሲና አማካሪ የነበሩት ግርማ ለማ ደሳለኝ በዛሬው እለትሰ ህይወታቸው አልፏል፡፡
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በህዝብ አስተዳደር በከፍተኛ ማዕረግ በዲግሪ የተመረቁት ጋሽ ግርማ “ የንጉሱ ገመና” ከተሰኘው መፅሀፍ በተጨማሪ “የካህሊል ጅብራን ምርጥ ስራዎች” የተሰኘ ትርጉም ስራ ለአንባቢ ያቀረቡ እና ለህትመት ያልበቁ አምስት ያህል የትርጉምና የራሳቸው ወጥ ስራዎች ነበሯቸው፡፡ባለሙያው ከላይ የተዘረዘሩት ሁሉ የትርፍ ሰዓትስራዎቻቸው ሲሆኑ በመደበኛነት የሂውማን ሪሶርስ ማኔጅመንት አማካሪ ነበሩ፡፡
በህይወታቸው መጨረሻ በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ሲሰሩ የነበሩ ሲሆን በጠና ታመው አልጋ ላይ ከዋሉ መቆየታቸውን የገለጹልን ምንጮቻችን በዛሬው እለት በተከራዩበት ቤት ህይወታቸው ማለፉን ተከትሎ የቅርብ ዘመድም ሆነ ወገን ስለሌላቸው አስክሬናቸው በመንግስት( ማዘጋጃ ቤት) ሊቀበር እንደነበርም ታውቋል፡፡
ጉዳዩን ከሰሙት መካከል የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ባልደረባ የሆነው ጋዜጠኛ ጌታቸው ለማ እና ባለሙያውን የሚያውቁ ጥቂት ወዳጆቹ ሁኔታውን ለፕሬስ ድርጅት እና ለ ቀድሞ ባልደረቦቹ በማሳወቅ እና በማስተባበር በመንግስት እንዳይቀበር ያደረጉ ሲሆን በነገው እለትም በ6፡00 አዲሱ ገበያ በሚገኘው እግዚአብሄር አብ ቤተክርስትያን የቀብር ስነ ስርዓቱ የሚፈጸም መሆኑን ገልጸው በሙያው ላይ ያሉ ሁሉ ለአንጋፋው ባለሙያ ሽኝት እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡
ምንጭ፦ ሸገር ታይምስ
--------------------------------------
ሰው እያለ አጠገባችን ፤
መልካም ስሙን ፣ መጥራት ሲያመን
<< ሰው ካልሞተ ፣ ወይ ካልሄደ
አይነሳም >> እንላለን።
እንዲህ እያልን ፣
አበባውን ቀጥፈን ጥለን
አበባ እናስቀምጣለን።
((( ነብይ መኮንን )))
እስከመቼ ይሆን ..??? ዛሬም የነብይ መኮንን ግጥም እንደ #ትንቢት እኛ ሀገር በደንብ ይሰራል
ግርማ ለማ ግን አበባ ቀርቶበት....በወጉ የሚቀብረው የለም .....? ዘመድ ይቅር..ወገን ምን ማለት ነው.....?
እስከዛሬ የፃፈልን ነገሮች ስናነበብ የነበርነው ለባዳ ህዝብ ነበር?
እዚህ ሀገር ዘፋኝ እና አርቲስት ብቻ ነው አሸሼ ገዳሜ ሚበዛለት...? ደራሲዋቻችን ከሰጡን ነገር አንፃር የሚኖሩት ኑሮ ለነሱ ሚገባ ነው..? አሁን ጭራሽ ሲሞቱ ሚቀብራቸው .....ከዚህ በላይ ልብ የሚሰብር ነገር አለ..?😭😭😭😭😭😭😭😭😭
@balmbaras
@getem
@getem