#ያልፋል_አይደል?
:
:
:
እየደለብኩ እየሰባው፤
መሸ ነጋ ወጣው ገባው።
እንደዘበት እንደኑረት፤
ሽቅብ ፍስስ የዕድሜ ጅረት።
ያለ ቁዝም ያለ ስጋት፤
አሁን ምሽት አሁን ንጋት።
ልብ ሳይለኝ ሰቀቀኑ፤
እንደወትሮ ጋመ ቀኑ።
፡
፡
ኖርኩኝ፤
ሄድኩኝ፤
የት እንዳለው ሳላስታውስ፤
እንዲው ንጉድ እንዲው ፍስስ።
፡
፡
መጓዜንም አላበቃው፤
እግር ሲያጥረኝ ድንገት ነቃው።
ልቤ ቢናኝ፤
ዞሬ ስቃኝ፤
ተንደረደርኩ ልደላደል፤
ከቦኝ ኖሯል ለካስ ገደል።
፡
፡
እንዴት ገባው እንዴት ልውጣስ፣
ማን ያድነኝ ምን አውቄ፤
የሚያኖረኝ አንዱ ተስፋ፣
« ያልፋል አይደል ? » ሚል ጥያቄ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ (@yeneeyita)
@yeneeyita
@getem
@getem
@getem
:
:
:
እየደለብኩ እየሰባው፤
መሸ ነጋ ወጣው ገባው።
እንደዘበት እንደኑረት፤
ሽቅብ ፍስስ የዕድሜ ጅረት።
ያለ ቁዝም ያለ ስጋት፤
አሁን ምሽት አሁን ንጋት።
ልብ ሳይለኝ ሰቀቀኑ፤
እንደወትሮ ጋመ ቀኑ።
፡
፡
ኖርኩኝ፤
ሄድኩኝ፤
የት እንዳለው ሳላስታውስ፤
እንዲው ንጉድ እንዲው ፍስስ።
፡
፡
መጓዜንም አላበቃው፤
እግር ሲያጥረኝ ድንገት ነቃው።
ልቤ ቢናኝ፤
ዞሬ ስቃኝ፤
ተንደረደርኩ ልደላደል፤
ከቦኝ ኖሯል ለካስ ገደል።
፡
፡
እንዴት ገባው እንዴት ልውጣስ፣
ማን ያድነኝ ምን አውቄ፤
የሚያኖረኝ አንዱ ተስፋ፣
« ያልፋል አይደል ? » ሚል ጥያቄ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ (@yeneeyita)
@yeneeyita
@getem
@getem
@getem
❤56👍23🎉3🔥2