*ሀገር ቤት ሲታሰብ*
(ምግባር ሲራጅ)
ያነፈሰን ነፋስ
ያቃጠለን ፀሐይ
የመሸብን ፅልመት
የጋረደን ሰማይ፡፡
በኑሯችን መሃል
የሰማነው አዛን
አሜን ያልነው ኪዳን
ተጋግዘን ያዘንነው
የባልንጀራ ሃዘን፡፡
ከረመዳን ጧሚ
የቀመስነው አፍጥር
አንጀት ያስጠፈረን
የማርያም ለት ዝክር፡፡
ሰላም ለመሳጣት
ካስቀዳሽ ትከሻ
ስመን ያነሳነው
የከርቤ እንክብል
ከሩቅ የሰማነው፤ ያድባር ሽማግሌ
የሚከረክር ሳል፡፡
ጣራችን ያረፈ
የደመራ ቁራጭ
ጥቋቁር ጥላሸት
በድግግም ብዛት
ተቀብለን ያልነው
መንዙማ ማህሌት፡፡
አንድነት፤
ባንድነት፡፡
በስውር መዳፉ፤ እያጨባበጠ
ሀገር ከመናፈቅ፤ የለም ያመለጠ፡፡
#ዘንባባ ከተሰኘችው መፅሀፍ የተወሰደ
@getem
@getem
@getem
(ምግባር ሲራጅ)
ያነፈሰን ነፋስ
ያቃጠለን ፀሐይ
የመሸብን ፅልመት
የጋረደን ሰማይ፡፡
በኑሯችን መሃል
የሰማነው አዛን
አሜን ያልነው ኪዳን
ተጋግዘን ያዘንነው
የባልንጀራ ሃዘን፡፡
ከረመዳን ጧሚ
የቀመስነው አፍጥር
አንጀት ያስጠፈረን
የማርያም ለት ዝክር፡፡
ሰላም ለመሳጣት
ካስቀዳሽ ትከሻ
ስመን ያነሳነው
የከርቤ እንክብል
ከሩቅ የሰማነው፤ ያድባር ሽማግሌ
የሚከረክር ሳል፡፡
ጣራችን ያረፈ
የደመራ ቁራጭ
ጥቋቁር ጥላሸት
በድግግም ብዛት
ተቀብለን ያልነው
መንዙማ ማህሌት፡፡
አንድነት፤
ባንድነት፡፡
በስውር መዳፉ፤ እያጨባበጠ
ሀገር ከመናፈቅ፤ የለም ያመለጠ፡፡
#ዘንባባ ከተሰኘችው መፅሀፍ የተወሰደ
@getem
@getem
@getem
👍2