ግጥም ብቻ 📘
ለውብ ቀን! 💚 እነሆ አንድ ውብ ግጥም ልጋብዛችሁ ወደድኩ። ገጣሚው ወሰንሰገድ ገብረኪዳን ነው። ይህ ግጥሙ ሰሞነኛውን ስሜታችንን የሚጋራ፣ ግራ መጋባታችንን የሚያብራራ ነው። የዛሬ ሦስት ዓመትም ፌስ ቡክ ላይ ለጥፎት ነበር። እናም አንብቡት - ትደመማላችሁ። በነገራችን ላይ ይህን ግጥም ከማግኘቴ ከሰዓታት በፊት ለረጅም ጊዜያት ስንቀጣጠር ቆይተን የፈጣሪ መሻት ሆኖ ዛሬ ካገኘሁት ወዳጄ ጋር ካወጋናቸው…
#ክፍል 2
ባለፈው ደብዳቤ - ግራ መጋባትሽ - እኔን አይደንቀኝም
ከችግር ተላምደን - ደንዝዘን ገርዝዘን - እያለን የለንም፡፡
“አለን!” የምንለው - ነፍስና ሥጋችን - ባይላቀቅ እንጂ
ሞተናል በቁሙ - እውነቱን ልንገርሽ - የጆሮን በአዋጅ፡፡
ስለዚህ እኮ ነው፡-
ፈልገሽ አፋልገሽ - አገሬን ሳሚልኝ - ብዬሽ የነበረ
ምን የማይለው አለ - መላ ቅጥ ሲጠፋው - ሰው ከተቸገረ!?
አቤት ነው አቤቱ!!
የአገር ልጅ ጭንቀቱ! - ብዛትና ዓይነቱ
ፍትህ መታረዙ - ርትዕ ማጣቱ - ኑሮ ውድነቱ!
ኧረ ስንቱ ስንቱ!!?
በስንቱ መከራ - የአገሩ ሰው ሁሉ - ታስሮ ተጠፍሮ
አንገት ደፊ ሆኗል - መብሰልሰልን መርጧል - መኖር አቀርቅሮ፡፡
/
ደረትን ነፋ አር'ጎ - ቀና ብሎ መሄድ
በአበሻ ምድር ላይ - የህልም ዓለም ሆኗል - የትዝታ መንገድ፡፡
እንዲህ ነው እንግዲህ - ወገኔ 'ምትይው - ኑሮና ህይወቱ
በአካል ይኑር እንጂ - በመንፈስ ተሰዷል - ከአገሩ ከ“ቤቱ”፡፡
/
ስለዚህ እኮ ነው - ተሰዳለች መሰል - ሃገሬ የምልሽ
አንቺ ባለሽበት- ትገኝ እንደሆነ - ሳሚልኝ እባክሽ
.
(ክፍል 3 ይቀጥላል )
@getem
@getem
@balmbaras
ባለፈው ደብዳቤ - ግራ መጋባትሽ - እኔን አይደንቀኝም
ከችግር ተላምደን - ደንዝዘን ገርዝዘን - እያለን የለንም፡፡
“አለን!” የምንለው - ነፍስና ሥጋችን - ባይላቀቅ እንጂ
ሞተናል በቁሙ - እውነቱን ልንገርሽ - የጆሮን በአዋጅ፡፡
ስለዚህ እኮ ነው፡-
ፈልገሽ አፋልገሽ - አገሬን ሳሚልኝ - ብዬሽ የነበረ
ምን የማይለው አለ - መላ ቅጥ ሲጠፋው - ሰው ከተቸገረ!?
አቤት ነው አቤቱ!!
የአገር ልጅ ጭንቀቱ! - ብዛትና ዓይነቱ
ፍትህ መታረዙ - ርትዕ ማጣቱ - ኑሮ ውድነቱ!
ኧረ ስንቱ ስንቱ!!?
በስንቱ መከራ - የአገሩ ሰው ሁሉ - ታስሮ ተጠፍሮ
አንገት ደፊ ሆኗል - መብሰልሰልን መርጧል - መኖር አቀርቅሮ፡፡
/
ደረትን ነፋ አር'ጎ - ቀና ብሎ መሄድ
በአበሻ ምድር ላይ - የህልም ዓለም ሆኗል - የትዝታ መንገድ፡፡
እንዲህ ነው እንግዲህ - ወገኔ 'ምትይው - ኑሮና ህይወቱ
በአካል ይኑር እንጂ - በመንፈስ ተሰዷል - ከአገሩ ከ“ቤቱ”፡፡
/
ስለዚህ እኮ ነው - ተሰዳለች መሰል - ሃገሬ የምልሽ
አንቺ ባለሽበት- ትገኝ እንደሆነ - ሳሚልኝ እባክሽ
.
(ክፍል 3 ይቀጥላል )
@getem
@getem
@balmbaras