#ትረፊ_ስትለኝ
እራሴን ሳገኛው ከጦጣዎች ተርታ*
ወቅሼህ ነበረ አንተ ታላቅ ጌታ
ታስታውስ እንደሆን
እነሱን ከጎጆ እኔን ደሞ ከዱር
ስለምን ለየኸኝ ሰው ከሚባል ፍጡር
ብዬሀለሁ ያኔ ሳይገባኝ ሰው ማለት
አይገኝም እና ሞት የቀበጡ ዕለት
ትረፊ ስትለኝ ጦጣ አረከኝና
ከሰው ዘር ለየኸኝ ይድረስህ ምስጋና
ከሚታየው ሀጢያት ከዲያብሎስ ስራ
ሰው በረከሰበት ከዚህ አለም ተራ
ለይተህ ያኖርከኝ ሀጢያት እንዳልሰራ
እንኳንም ፈጠርከኝ ጦጣ አደረክና
ትረፊ ስትለኝ
ለዘመናት ሳየው ሰውን አተኩሬ
ያጠራጥረኛል ለአንድም ቀን መኖሬ
በሚሰራው ስራ ሁሌም ተማርሬ
እያፈርኩበት ነው አሁን አሁን እማ
በወንድሙ ደስታ ሲቆስል ሲደማ
የእህቱን ገመና ሲያወጣው በገሀድ ምንም ሳያቅማማ
እጄን ከአፌ አደረኩ ትዝብቴን ላሰማ
አቤት ያንተ ፍጡር ሀጢያቱ የበዛ
ይቅርብኝ ሰው መሆን ጥንቅር ይበል እዛ
ከሰው መጠለያ ውስጡ ሰላም ካጣ
በማይሆን በሚሆን እንዲህ ከተንጣጣ
በጫካ መኖሬም የለብኝም ጣጣ
"የባሰም አለና..." እንዳለው ተረቱ
የሰማዩ ጌታ አንተ ክንደ ብርቱ
ምስጋና ይድረስህ ላረከኝ ጦጢቱ ።
------------------------//------------------------
✍🏽©መቅደስ ተስፋዬ ሞላ
15/11/2016
------------------------//------------------------
@getem
@getem
@getem
እራሴን ሳገኛው ከጦጣዎች ተርታ*
ወቅሼህ ነበረ አንተ ታላቅ ጌታ
ታስታውስ እንደሆን
እነሱን ከጎጆ እኔን ደሞ ከዱር
ስለምን ለየኸኝ ሰው ከሚባል ፍጡር
ብዬሀለሁ ያኔ ሳይገባኝ ሰው ማለት
አይገኝም እና ሞት የቀበጡ ዕለት
ትረፊ ስትለኝ ጦጣ አረከኝና
ከሰው ዘር ለየኸኝ ይድረስህ ምስጋና
ከሚታየው ሀጢያት ከዲያብሎስ ስራ
ሰው በረከሰበት ከዚህ አለም ተራ
ለይተህ ያኖርከኝ ሀጢያት እንዳልሰራ
እንኳንም ፈጠርከኝ ጦጣ አደረክና
ትረፊ ስትለኝ
ለዘመናት ሳየው ሰውን አተኩሬ
ያጠራጥረኛል ለአንድም ቀን መኖሬ
በሚሰራው ስራ ሁሌም ተማርሬ
እያፈርኩበት ነው አሁን አሁን እማ
በወንድሙ ደስታ ሲቆስል ሲደማ
የእህቱን ገመና ሲያወጣው በገሀድ ምንም ሳያቅማማ
እጄን ከአፌ አደረኩ ትዝብቴን ላሰማ
አቤት ያንተ ፍጡር ሀጢያቱ የበዛ
ይቅርብኝ ሰው መሆን ጥንቅር ይበል እዛ
ከሰው መጠለያ ውስጡ ሰላም ካጣ
በማይሆን በሚሆን እንዲህ ከተንጣጣ
በጫካ መኖሬም የለብኝም ጣጣ
"የባሰም አለና..." እንዳለው ተረቱ
የሰማዩ ጌታ አንተ ክንደ ብርቱ
ምስጋና ይድረስህ ላረከኝ ጦጢቱ ።
------------------------//------------------------
✍🏽©መቅደስ ተስፋዬ ሞላ
15/11/2016
------------------------//------------------------
@getem
@getem
@getem
❤1