ያል-ሻረ ፍቅር
°
°
°
መውደዴ ጋ'ራ፤
ማፍቀሬ ተራራ፤
ብውልም ካንቺ ጋ።
ባመሽም ካንቺ ጋ።
ለመድረስ እራቀኝ
ኩይሳው ልብሽ ጋ።
°
°
°
የካቻምናው ንፋስ
ወደ እፉዬ ገላሽ፤
ወደ አንቺዬ ጥላሽ፤
ገፍቶት...ገፍቶት፤
ገለባው ባልሽን
አመጣው ጎትቶት።
°
°
°
ብናኙ ዛሬም ድረስ
ጠረኑ አሁንም ድረስ
አ ስ ነ ጠ ሰ ሽ
ከልብሽ ተሰንቅሮ፤
እኔን ብልሽ፤
አልምር አለሽ፤
እንደ ድሮ።
#ሳሙኤል_አለሙ
@Samuelalemu5
ሀዋሳ , ሰኔ 30-2015 ዓ.ም
@getem
@getem
@getem
°
°
°
መውደዴ ጋ'ራ፤
ማፍቀሬ ተራራ፤
ብውልም ካንቺ ጋ።
ባመሽም ካንቺ ጋ።
ለመድረስ እራቀኝ
ኩይሳው ልብሽ ጋ።
°
°
°
የካቻምናው ንፋስ
ወደ እፉዬ ገላሽ፤
ወደ አንቺዬ ጥላሽ፤
ገፍቶት...ገፍቶት፤
ገለባው ባልሽን
አመጣው ጎትቶት።
°
°
°
ብናኙ ዛሬም ድረስ
ጠረኑ አሁንም ድረስ
አ ስ ነ ጠ ሰ ሽ
ከልብሽ ተሰንቅሮ፤
እኔን ብልሽ፤
አልምር አለሽ፤
እንደ ድሮ።
#ሳሙኤል_አለሙ
@Samuelalemu5
ሀዋሳ , ሰኔ 30-2015 ዓ.ም
@getem
@getem
@getem
👍22❤3🔥2👎1
የተረሳው እንባ
°
°
ዝናቡ ዶፍ ጥሎ ፥ አባርቶ እንዳበቃ፣
ደጅ-ደጁ ናፈቀሽ ፥ እንጃ ለቀጠሮ
እንጃ ለጥየቃ።
ተጣጠብሽ።
ተኳኳልሽ።
ተጫማሽ።
°
°
አየሽ አይደል! ደጁን
መረገጫም የለው፣
ቻው...ቻው...ተባብለን
እስከ----ምን'ለያየው፣
በጎርፍ ተ...ጥ...ለ...ቅ...ል...ቋ...ል።
-----የዘነጋሽውን ፥ እንባዬን አክሏል።
°
°
አየሽ አይደል! ደጁን
አልፎ ሂያጅ ሲዘሉት፤
ለቀናት...ለቀናት...
ከብቶቹ ሲረገጡት፤
ለቀናት...ለቀናት...
ጋሪዎች ሲያምሱት፤
ለቀናት...ለቀናት...
ወጣ ገባ ስትይ ፥ አቁሮ የቀረው፤
እንባዬ ነበረ ፥ ደጅሽ የነበረው።
°
°
#ሳሙኤል_አለሙ
@Samuelalemuu
@Getem
@Getem
@Getem
°
°
ዝናቡ ዶፍ ጥሎ ፥ አባርቶ እንዳበቃ፣
ደጅ-ደጁ ናፈቀሽ ፥ እንጃ ለቀጠሮ
እንጃ ለጥየቃ።
ተጣጠብሽ።
ተኳኳልሽ።
ተጫማሽ።
°
°
አየሽ አይደል! ደጁን
መረገጫም የለው፣
ቻው...ቻው...ተባብለን
እስከ----ምን'ለያየው፣
በጎርፍ ተ...ጥ...ለ...ቅ...ል...ቋ...ል።
-----የዘነጋሽውን ፥ እንባዬን አክሏል።
°
°
አየሽ አይደል! ደጁን
አልፎ ሂያጅ ሲዘሉት፤
ለቀናት...ለቀናት...
ከብቶቹ ሲረገጡት፤
ለቀናት...ለቀናት...
ጋሪዎች ሲያምሱት፤
ለቀናት...ለቀናት...
ወጣ ገባ ስትይ ፥ አቁሮ የቀረው፤
እንባዬ ነበረ ፥ ደጅሽ የነበረው።
°
°
#ሳሙኤል_አለሙ
@Samuelalemuu
@Getem
@Getem
@Getem
👍21😢11❤6
አትፍረጂብኝ...!
°
መኖር አደባባይ ሆነና
እግረ-መንገዴን ፥ እግረ-መንገዷን
መላተም ሆነ
ከኔ ጋ ግዷን።
(ተረፈች'ና...)
°
ቤት ለንቦሳ ማለቷ ቀርቶ
ካይኔ ከጎጆው ፥ ገባች በድንገት
እንባዬን ስታይ ፥ ተደበላልቋል
ሲኦል ከገነት።
(አዘነች'ና...)
°
አጠለለችው የደስታ እንባዬን
ደሞ ዝቃጩን ፥ ቅራሪ ሐዘኔን
ሳትግትልኝ ፥ አሸውት ዓይኔን
ትንኝ ነሽ ብየ
ንክሻሽን ብየ
°
(አትፍረጂብኝ...)
°
የዝግባውን አጥር ፥ ምስጥ እንደበላው
"አለህ ግን..." አትበይኝ ፥ ቆሜ ስላለው
እኔ ለራሴ...
እንደ ጠጅ-ቤት ንብ ፥ ሐዘን ከቦኛል
በዌይራ ባጥነው
እንባ ያመልጠኛል።
°
(አትታዘቢኝ...)
°
በኩለ ቀን ጅብ እንደ ወለደ ዓይነት
ብርሃን ቀላቅሎ ዝናም የጣለ 'ለት
ብሶት አጭቆ ፥ ጥርሴን ካሳቅሽው
እንባ ያወርዳል ፥ ጉንጬን ባየሽው
°
(አትፍረጂብኝ...)
°
እንባ ከ ጤዛው
እስስት ከቦታው ፥ ታይቶ አይለይም
ወጣልኝ ቢባል ፥ አገኘው ቢባል
እድሌ ሆኖ ፥ ልቤ ሚደረሰው
እኔን የሚለኝ ፥ የአንድ ቀን ሰው።
°
(አትፍረጂብኝ...)
°
#ሳሙኤል_አለሙ
@Samuelalemuu
@Getem
@Getem
@Getem
°
መኖር አደባባይ ሆነና
እግረ-መንገዴን ፥ እግረ-መንገዷን
መላተም ሆነ
ከኔ ጋ ግዷን።
(ተረፈች'ና...)
°
ቤት ለንቦሳ ማለቷ ቀርቶ
ካይኔ ከጎጆው ፥ ገባች በድንገት
እንባዬን ስታይ ፥ ተደበላልቋል
ሲኦል ከገነት።
(አዘነች'ና...)
°
አጠለለችው የደስታ እንባዬን
ደሞ ዝቃጩን ፥ ቅራሪ ሐዘኔን
ሳትግትልኝ ፥ አሸውት ዓይኔን
ትንኝ ነሽ ብየ
ንክሻሽን ብየ
°
(አትፍረጂብኝ...)
°
የዝግባውን አጥር ፥ ምስጥ እንደበላው
"አለህ ግን..." አትበይኝ ፥ ቆሜ ስላለው
እኔ ለራሴ...
እንደ ጠጅ-ቤት ንብ ፥ ሐዘን ከቦኛል
በዌይራ ባጥነው
እንባ ያመልጠኛል።
°
(አትታዘቢኝ...)
°
በኩለ ቀን ጅብ እንደ ወለደ ዓይነት
ብርሃን ቀላቅሎ ዝናም የጣለ 'ለት
ብሶት አጭቆ ፥ ጥርሴን ካሳቅሽው
እንባ ያወርዳል ፥ ጉንጬን ባየሽው
°
(አትፍረጂብኝ...)
°
እንባ ከ ጤዛው
እስስት ከቦታው ፥ ታይቶ አይለይም
ወጣልኝ ቢባል ፥ አገኘው ቢባል
እድሌ ሆኖ ፥ ልቤ ሚደረሰው
እኔን የሚለኝ ፥ የአንድ ቀን ሰው።
°
(አትፍረጂብኝ...)
°
#ሳሙኤል_አለሙ
@Samuelalemuu
@Getem
@Getem
@Getem
👍49❤16🔥1
የት ልንደርስ?
(ሳሙኤል አለሙ)
[እ--ወ--ድ--ሃ--ለ--ው
እ--ወ--ድ--ሻ--ለ--ው]
ባንዲት መኺና ፥ ሞልተው ሊሳፈሩ
መልዕክት መጣና
ተቀጣጠሩ።
እንደ ደረሱ...
ከአፍ መናኸሪያ ፥ ወደ ልብ ሊጓዙ
ለጉዞኣቸው መዳረሻ
ቆሎውን ኩኪሱን ገዙ።
ሊሞላ...ሊሞላ...ሊሞላ
ሊሞላ ሲል
አንተ ነ-ሃ
አንቺ ነ-ሻ
በመሃል ስንባባል
ለካስ ቃል ይደነግጣል።
ይኸው እያቸው...
የሞላውን ትተው ፥ በኔና ባንቺ ኩርፊያ
ይኸው እያቸው...
ወደ መጡበት ፥ ሊመለሱ በጥድፊያ
ይኸው እያቸው...
የጋራ ቃላችንን
ነጥለን ስናሳፍራቸው።
[እ]--[ወ]--[ድ]--ሻ--[ለ]--[ው]
--- --- --- --- --- --- ---
[እ]--[ወ]--[ድ]--ሃ--[ለ]---[ው]
#ሳሙኤል_አለሙ
@Samuelalemuu
@getem
@getem
(ሳሙኤል አለሙ)
[እ--ወ--ድ--ሃ--ለ--ው
እ--ወ--ድ--ሻ--ለ--ው]
ባንዲት መኺና ፥ ሞልተው ሊሳፈሩ
መልዕክት መጣና
ተቀጣጠሩ።
እንደ ደረሱ...
ከአፍ መናኸሪያ ፥ ወደ ልብ ሊጓዙ
ለጉዞኣቸው መዳረሻ
ቆሎውን ኩኪሱን ገዙ።
ሊሞላ...ሊሞላ...ሊሞላ
ሊሞላ ሲል
አንተ ነ-ሃ
አንቺ ነ-ሻ
በመሃል ስንባባል
ለካስ ቃል ይደነግጣል።
ይኸው እያቸው...
የሞላውን ትተው ፥ በኔና ባንቺ ኩርፊያ
ይኸው እያቸው...
ወደ መጡበት ፥ ሊመለሱ በጥድፊያ
ይኸው እያቸው...
የጋራ ቃላችንን
ነጥለን ስናሳፍራቸው።
[እ]--[ወ]--[ድ]--ሻ--[ለ]--[ው]
--- --- --- --- --- --- ---
[እ]--[ወ]--[ድ]--ሃ--[ለ]---[ው]
#ሳሙኤል_አለሙ
@Samuelalemuu
@getem
@getem
👍35❤10🔥3