#ሰው_ኹሉ_ቢርቀኝ
( አይቆጨኝ፤ አይደንቀኝ፤ • ሰው ኹሉ ቢርቀኝ፤ )
ሀቄን የሚሸከም፣ ማንም እስከማይቀር፣
• ከርግቦች፣
• ከጨቅሎች፣
•ከአበቦች፣
• ከእናቶች፣
• ከዜማ፣
• ከፍቅር፣
#ከእመ_ብርሐን_እና_ከግጥም_በስተቀር።
( አይቆጨኝ፤ አይደንቀኝ፤ • ሰው ኹሉ ቢርቀኝ። )
....................................................
#ሠይፈ__ወርቅ
@getem
@getem
( አይቆጨኝ፤ አይደንቀኝ፤ • ሰው ኹሉ ቢርቀኝ፤ )
ሀቄን የሚሸከም፣ ማንም እስከማይቀር፣
• ከርግቦች፣
• ከጨቅሎች፣
•ከአበቦች፣
• ከእናቶች፣
• ከዜማ፣
• ከፍቅር፣
#ከእመ_ብርሐን_እና_ከግጥም_በስተቀር።
( አይቆጨኝ፤ አይደንቀኝ፤ • ሰው ኹሉ ቢርቀኝ። )
....................................................
#ሠይፈ__ወርቅ
@getem
@getem
👍2
#ተፈፀመ
እየ"ተ"ሸከመ
የስጋዬ ሸክም - ድካሜ ከሰመ
እየ"ተ"ወገረ
የሕይወቴ ቀንበር - ወጥመድ ተሰበረ
እየ"ተ"ገረፈ
የኃጢአቴ ቁስል - ከላዬ እረገፈ
እየ"ተ"ንገላታ
የዛለ ስጋዬ - ከስጋት ተፈታ
እየ"ተ"ሰቃየ
ክፋቴ፣ መርገምቴ፣ ከእኔ ተለያየ
ውኃ እየ"ተ"ጠማ
በጽድቅ እረጠበች - የነፍሴ ባድ´ማ
እየጠጣ ሐሞት
አስደነገጠልኝ - የዕድሜዬን ሙሉ ሞት
እየ"ተ"ሰቀለ
'ኤሎሄ' እያለ
ገላው እየዛለ
ከገዛ እስትንፋሱ - እየ"ተ"ነጠለ
የዘለአለም ሞቴን - በሞቱ ገደለ
°°
ልጇን ሲሰቅሉባት - 'ተዉ' ባይ ሰው አጥታ
ማርያም እያነባች - ሰይፍ አልፎ በአንጀቷ
'እነኋት እናትህ'
ቢለው ለዮሐንስ - "ተ"መስቀል ላይ ጌታ
ሐዘኔ "ተ"ሻረ - በእናትነቷ
••
በቁስሉ ካልዳነች - በደሙ ታክማ
ዓለም ቁስለኛ ነች - የስቃይ አውድማ
..
እየ"ተ"ሸከመ
እየ"ተ"ወገረ
እየ"ተ"ገረፈ
እየ"ተ"ንገላታ
እየ"ተ"ሰቃየ
ውኃ እየ"ተ"ጠማ
እየጠጣ ሐሞት
እየ"ተ"ሰቀለ
'ኤሎሄ' እያለ
ገላው እየዛለ
መድኃኒት ለመኾን - መድኃኒት ታመመ´
ቃሉም " #ተፈፀመ "
°°°| #ሠይፈ_ወርቅ |°°°
@getem
@getem
እየ"ተ"ሸከመ
የስጋዬ ሸክም - ድካሜ ከሰመ
እየ"ተ"ወገረ
የሕይወቴ ቀንበር - ወጥመድ ተሰበረ
እየ"ተ"ገረፈ
የኃጢአቴ ቁስል - ከላዬ እረገፈ
እየ"ተ"ንገላታ
የዛለ ስጋዬ - ከስጋት ተፈታ
እየ"ተ"ሰቃየ
ክፋቴ፣ መርገምቴ፣ ከእኔ ተለያየ
ውኃ እየ"ተ"ጠማ
በጽድቅ እረጠበች - የነፍሴ ባድ´ማ
እየጠጣ ሐሞት
አስደነገጠልኝ - የዕድሜዬን ሙሉ ሞት
እየ"ተ"ሰቀለ
'ኤሎሄ' እያለ
ገላው እየዛለ
ከገዛ እስትንፋሱ - እየ"ተ"ነጠለ
የዘለአለም ሞቴን - በሞቱ ገደለ
°°
ልጇን ሲሰቅሉባት - 'ተዉ' ባይ ሰው አጥታ
ማርያም እያነባች - ሰይፍ አልፎ በአንጀቷ
'እነኋት እናትህ'
ቢለው ለዮሐንስ - "ተ"መስቀል ላይ ጌታ
ሐዘኔ "ተ"ሻረ - በእናትነቷ
••
በቁስሉ ካልዳነች - በደሙ ታክማ
ዓለም ቁስለኛ ነች - የስቃይ አውድማ
..
እየ"ተ"ሸከመ
እየ"ተ"ወገረ
እየ"ተ"ገረፈ
እየ"ተ"ንገላታ
እየ"ተ"ሰቃየ
ውኃ እየ"ተ"ጠማ
እየጠጣ ሐሞት
እየ"ተ"ሰቀለ
'ኤሎሄ' እያለ
ገላው እየዛለ
መድኃኒት ለመኾን - መድኃኒት ታመመ´
ቃሉም " #ተፈፀመ "
°°°
@getem
@getem
❤50👍40😢5😱2🔥1🤩1