ተናፋቂው የፋና ብዕር 5ተኛ ዙር የጥበብ ምሽት በአዲስ ዓመት ዋዜማ ቅዳሜ ጷጉሜ 2/13/2011 ዓ/ም አመሻሽ 11:00 ሰዓት በዝዋይ ቱሪስት ሆቴል አዳራሽ ውስጥ
በዕለቱ
ስነ-ግጥም፣ወግ፣
መነባንብ
፣ዲስኩር፣
ሙዚቃ
ከሌሎች ማራኪ ዝግቶች ጋር
አዘጋጅ ፋና ብዕር
--
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
በዕለቱ
ስነ-ግጥም፣ወግ፣
መነባንብ
፣ዲስኩር፣
ሙዚቃ
ከሌሎች ማራኪ ዝግቶች ጋር
አዘጋጅ ፋና ብዕር
--
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
ያ ማዶ!!!!!!!!!!
ይኸው ይሰማኛል፤ ከወዲያኛው መንደር፤ ወዲያ ማዶ ጋራ፤
ግራ በገባው ህዝብ ፤
የተከበበችው ግራ ገብ ሃገሬ ድረሱልኝ ብላ ጩሃ ስትጣራ ።
የገዳይ ተገዳይ ሙሾ ያልተለያት ኢትዮጲያ ሃገሬ፤
ባዘን የጎበጠች ምንዱባን ሆናለች ይኸው እስከዛሬ፤
መልሶ መላልሶ፤
ያ የደም ታሪኳ ይኮሰኩሳታል እንደ አባ ጨጓሬ ።
ከሞት መቃብር ደጅ የገዳይ አስገዳይ ታሪክ የተማረ፤
በክፋት ብላክ ቦርድ ፤
አይኑ እስኪንቦዣቦዥ ፤
አቢዮት የሚሉት የደም ጠማሽ ፅህፈት ፊደል የቆጠረ፤
ይኸው ዛሬም ቆሟል፤
ወንድሙን ሊገድል የቃየልን ሳንጃ እያገነደረ ።
በመፈክር ብዛት፤
በርእዮት ግርግር ፤
ይመስለን ነበር ሃገር የሚቀና ጎተራ ሚሞላ፤
ይሆን መስሎን ነበር ፤
በእናቸንፋለን፤
በእናሸንፋለን፤ሸለቆ ሚደፈን በአጀብ በሽለላ፤
ለካስ ተራራ አለ ፤የትላንትናውን ኮረብታ ዳገቱን ከወጡ በዃላ ።
አዎን ተራራ አለ ፤
ከግማድ ጥላው ጋር አታልፍም እያለ ዳንኪራ ሚራገጥ፤
ለካስ እዚያ ማዶ ፤
ከዚያ ባሻጋሪ፤ ሌላ ተራራ አለ ተመለስ እያለ አንተው ላይ የሚያፈጥ ።
ግን አትመለስም፤
አታፈገፍግም ይቅር ተውት ብለህ እንዳምና ካቻምና ፤
ተራራ ሚያፈርሰው፤
ዳገት የሚንደው፤ የኤልያስ ቅባት የነ ካሌብ አዋጅ ካንተ ጋር ነውና ።
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
ይኸው ይሰማኛል፤ ከወዲያኛው መንደር፤ ወዲያ ማዶ ጋራ፤
ግራ በገባው ህዝብ ፤
የተከበበችው ግራ ገብ ሃገሬ ድረሱልኝ ብላ ጩሃ ስትጣራ ።
የገዳይ ተገዳይ ሙሾ ያልተለያት ኢትዮጲያ ሃገሬ፤
ባዘን የጎበጠች ምንዱባን ሆናለች ይኸው እስከዛሬ፤
መልሶ መላልሶ፤
ያ የደም ታሪኳ ይኮሰኩሳታል እንደ አባ ጨጓሬ ።
ከሞት መቃብር ደጅ የገዳይ አስገዳይ ታሪክ የተማረ፤
በክፋት ብላክ ቦርድ ፤
አይኑ እስኪንቦዣቦዥ ፤
አቢዮት የሚሉት የደም ጠማሽ ፅህፈት ፊደል የቆጠረ፤
ይኸው ዛሬም ቆሟል፤
ወንድሙን ሊገድል የቃየልን ሳንጃ እያገነደረ ።
በመፈክር ብዛት፤
በርእዮት ግርግር ፤
ይመስለን ነበር ሃገር የሚቀና ጎተራ ሚሞላ፤
ይሆን መስሎን ነበር ፤
በእናቸንፋለን፤
በእናሸንፋለን፤ሸለቆ ሚደፈን በአጀብ በሽለላ፤
ለካስ ተራራ አለ ፤የትላንትናውን ኮረብታ ዳገቱን ከወጡ በዃላ ።
አዎን ተራራ አለ ፤
ከግማድ ጥላው ጋር አታልፍም እያለ ዳንኪራ ሚራገጥ፤
ለካስ እዚያ ማዶ ፤
ከዚያ ባሻጋሪ፤ ሌላ ተራራ አለ ተመለስ እያለ አንተው ላይ የሚያፈጥ ።
ግን አትመለስም፤
አታፈገፍግም ይቅር ተውት ብለህ እንዳምና ካቻምና ፤
ተራራ ሚያፈርሰው፤
ዳገት የሚንደው፤ የኤልያስ ቅባት የነ ካሌብ አዋጅ ካንተ ጋር ነውና ።
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
የልብ ቅርፅ
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ፍቅርን ያህል ነገር...
ተሸክሜ ስኖር ፣ በልቤ ትከሻ
"ቃል አጠረኝ" የሚል....
ቃል ካ'ፌ አይወጣም ፣ ላወድስሽ ስሻ።
........................................................
እንደውም ሳፈቅርሽ ፣ ቃል ነው የተረፈኝ
ሁሉ ያጥርብኛል.....
በልብሽ ቅርፅ ውስጥ ፣ መውደድሽ ሲያገዝፈኝ።
...............................................
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
ሰፊ ያልሁት አለም ፣ ባንድ እርምጃ አለቀ
ሳልሄደው ሚደክመኝ...
ተራራና ጋራው ፣ ከግሬ ስር ጠለቀ።
"ሩቅ" ያልሁት ሰማይ..
ሩቅ የሚመስለኝ ፣ ነካሁት በስንዝር
ጨረቃና ፀሀይ....
ከኮከብ ያንሳሉ ፣ ከፍቅርሽ ግዝፈት ስር።
.......................................
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
ንጉስን ከዙፋን ፣ ማርከው የሚያወርዱ
የሀያላንን አቅም ፣ በጥቅሻ ሚያርዱ
ቆነጃጅት ሴቶች ...
"ቃል አጠረኝ" በሚል ቃላት የተሞሉ
ከፍቅርሽ ግዝፈት ስር..
ቃል ተገኝቶላቸው ፣ "ፋንጋዎች" ተባሉ።
.........................................
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
"ቃል አጠረኝ "በሚል...
ባፍቃሪ አንደበት ፣ ቃል ተትረፈረፈ
ሁሉን አሳንሶ...
በልቡ ቅርፅ ውስጥ ፣ ፍቅሩን አገዘፈ
አለሙን ሰርዞ ፣ ፍቅሩን ብቻ ፃፈ!!!
..........................................
ሳፈቅርሽ ይህን አልሁ...
ፍቅርን ተሸክሞ ፣ የሚኖር ልቦና
ሁሉም ከፍቅርሽ ስር ፣ መሆኑን አውቅና
አንቺን ለማወደስ .፣..እኔም ቃል ያጥረኛል
"ቃል አጠረኝ "ማለት...
ቃል እንደሆነ ግን ፣
ፍቅርሽ ይነግረኛል!!!
@getem
@getem
@getem
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ፍቅርን ያህል ነገር...
ተሸክሜ ስኖር ፣ በልቤ ትከሻ
"ቃል አጠረኝ" የሚል....
ቃል ካ'ፌ አይወጣም ፣ ላወድስሽ ስሻ።
........................................................
እንደውም ሳፈቅርሽ ፣ ቃል ነው የተረፈኝ
ሁሉ ያጥርብኛል.....
በልብሽ ቅርፅ ውስጥ ፣ መውደድሽ ሲያገዝፈኝ።
...............................................
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
ሰፊ ያልሁት አለም ፣ ባንድ እርምጃ አለቀ
ሳልሄደው ሚደክመኝ...
ተራራና ጋራው ፣ ከግሬ ስር ጠለቀ።
"ሩቅ" ያልሁት ሰማይ..
ሩቅ የሚመስለኝ ፣ ነካሁት በስንዝር
ጨረቃና ፀሀይ....
ከኮከብ ያንሳሉ ፣ ከፍቅርሽ ግዝፈት ስር።
.......................................
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
ንጉስን ከዙፋን ፣ ማርከው የሚያወርዱ
የሀያላንን አቅም ፣ በጥቅሻ ሚያርዱ
ቆነጃጅት ሴቶች ...
"ቃል አጠረኝ" በሚል ቃላት የተሞሉ
ከፍቅርሽ ግዝፈት ስር..
ቃል ተገኝቶላቸው ፣ "ፋንጋዎች" ተባሉ።
.........................................
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
"ቃል አጠረኝ "በሚል...
ባፍቃሪ አንደበት ፣ ቃል ተትረፈረፈ
ሁሉን አሳንሶ...
በልቡ ቅርፅ ውስጥ ፣ ፍቅሩን አገዘፈ
አለሙን ሰርዞ ፣ ፍቅሩን ብቻ ፃፈ!!!
..........................................
ሳፈቅርሽ ይህን አልሁ...
ፍቅርን ተሸክሞ ፣ የሚኖር ልቦና
ሁሉም ከፍቅርሽ ስር ፣ መሆኑን አውቅና
አንቺን ለማወደስ .፣..እኔም ቃል ያጥረኛል
"ቃል አጠረኝ "ማለት...
ቃል እንደሆነ ግን ፣
ፍቅርሽ ይነግረኛል!!!
@getem
@getem
@getem
❤2👍1
ለቅዳሚታችን
❤️❤️❤️
እንደ ላስታ ዳገት እንደላሊበላ ፤
ታቹን በሽምሸሃ ላዩን በብልባላ ፤
ልቤን ሰረቀችው፤
ላስታ ከበሩ ላይ ፤ አሸንድየ ብላ ።
ከቤተስኪያን ዳር ነው የልጅቱ ቤት ፤
አላፊና አግዳሚው ከሚያረግድበት ፤
እኔ ልሞት ሆነ ሁሉ እየሳማት ።
ከቄስ ጎበዜ አገር፤
ገነተ ማርያም ላይ፤ ልሳለም ወርጄ ፤
ላስታ ንግስ ቀረሁ፤
ቤዛ ኩሉ አለፈኝ ሸጋ ልጅ ወድጄ ።
እንደ ነአኩተላብ እንደላሊበላ ፤
ቤት ሰራች ይሉኛል ዲንጋዩን ፈልፍላ ፤
ዲንጋዩን ፈልፍላ የሰራችው ቤት ፤
አልባብ አልባብ ይላል፤ ማርያም ገብታበት ፤
ማርያም የገባችለት ፤ ስለቴ ሰመረ ፤
እንግዲህ መባዘን ፤ መንከራተት ቀረ ።
አሸንድየ አበባ ፤ አዝሎ መጣልሽ ፤
በዚህ ቀጭን ወገብ፤ በሚያምረው ባትሽ ፤
ላስታ ከበሩ ላይ ስትምነሸነሺ ፤
ድስትሽ ጦም አደረ ሳሳ ሞሰብሽ ፤
ባዶ ድስት ጥደሽ፤ ባዶ ቤት ይዘሽ ፤
ማነው የሚያገባሽ፤ ማነው የሚያጭሽ፤
የላስታው ጊወርጊስ፤
እሱ ይድረስልሽ እሱ ያግዝሽ።
በአመት አንድ ጊዜ፤
ሻደይ አገልድሜ ፤ አምሮብኝ ስወጣ ፤
እንኳንስ አባቴ ማርያም አትቆጣ ፤
ለሷ ነው እስክሳው ለሷ ነው ማርገዴ ፤
እመቤቴ ሳለች ምን ግዴ ምን ግዴ ።
ሻደይ ሻደይ ብየ ፤ ከቤቴ ገባሁኝ ፤
የማርያም ሙጌራ፤ ተጋግሮ አገኘሁኝ ፤
ያነን እየበላሁ ከቆላ እስከ ደጋ ፤
ክረምቱም አለፈ አዲስ አመት ነጋ ።
(( ጃ ኖ ))💚💛❤️
ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!💚
@getem
@getem
@balmbaras
❤️❤️❤️
እንደ ላስታ ዳገት እንደላሊበላ ፤
ታቹን በሽምሸሃ ላዩን በብልባላ ፤
ልቤን ሰረቀችው፤
ላስታ ከበሩ ላይ ፤ አሸንድየ ብላ ።
ከቤተስኪያን ዳር ነው የልጅቱ ቤት ፤
አላፊና አግዳሚው ከሚያረግድበት ፤
እኔ ልሞት ሆነ ሁሉ እየሳማት ።
ከቄስ ጎበዜ አገር፤
ገነተ ማርያም ላይ፤ ልሳለም ወርጄ ፤
ላስታ ንግስ ቀረሁ፤
ቤዛ ኩሉ አለፈኝ ሸጋ ልጅ ወድጄ ።
እንደ ነአኩተላብ እንደላሊበላ ፤
ቤት ሰራች ይሉኛል ዲንጋዩን ፈልፍላ ፤
ዲንጋዩን ፈልፍላ የሰራችው ቤት ፤
አልባብ አልባብ ይላል፤ ማርያም ገብታበት ፤
ማርያም የገባችለት ፤ ስለቴ ሰመረ ፤
እንግዲህ መባዘን ፤ መንከራተት ቀረ ።
አሸንድየ አበባ ፤ አዝሎ መጣልሽ ፤
በዚህ ቀጭን ወገብ፤ በሚያምረው ባትሽ ፤
ላስታ ከበሩ ላይ ስትምነሸነሺ ፤
ድስትሽ ጦም አደረ ሳሳ ሞሰብሽ ፤
ባዶ ድስት ጥደሽ፤ ባዶ ቤት ይዘሽ ፤
ማነው የሚያገባሽ፤ ማነው የሚያጭሽ፤
የላስታው ጊወርጊስ፤
እሱ ይድረስልሽ እሱ ያግዝሽ።
በአመት አንድ ጊዜ፤
ሻደይ አገልድሜ ፤ አምሮብኝ ስወጣ ፤
እንኳንስ አባቴ ማርያም አትቆጣ ፤
ለሷ ነው እስክሳው ለሷ ነው ማርገዴ ፤
እመቤቴ ሳለች ምን ግዴ ምን ግዴ ።
ሻደይ ሻደይ ብየ ፤ ከቤቴ ገባሁኝ ፤
የማርያም ሙጌራ፤ ተጋግሮ አገኘሁኝ ፤
ያነን እየበላሁ ከቆላ እስከ ደጋ ፤
ክረምቱም አለፈ አዲስ አመት ነጋ ።
(( ጃ ኖ ))💚💛❤️
ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!💚
@getem
@getem
@balmbaras
እንከን ላጣሽብኝ
----------------
በሰፌድ ላይ ቀመር
በ.....…ላሜዳ* ባየር
ግብሬን አበጥሮ ፥ ልብሽ እንዲቀጥረኝ
ሙያዬን መዝኖ ፥ አይንሽም እንዲያየኝ
ሽርጥ አገልድሜ ፥ እጅጉን ብለፋ
ጋገርራ ገብቼ ፥ ...ቡኮ ሊጥ ባሰፋ
እስቲበስል ብዬ
በትዝታ ቅርቃር ፥ አንገቴን ብደፋ
ተኝቶ ነው ብለሽ
የምጣዴን ክዳን ፥ ያለጊዜው ከፍተሽ
አይኑ የፈዘዘ ፥ …አፍለኛን አውጥተሽ
እኔን ለማባረር…
ምህኛት ብታጪ፥የእንጀራ'ይን ቆጠርሽ
ይሁና ከበጀሽ…
በማይመስል ህጸፅ ፥ መንገድ ከከጀለሽ
ከማይሳሳቱ
መላእክት ሰባእቱ
...ምስለ አሐዱን ከሆንሽ
እንግዲስ እኔው ነኝ…
እንደ ቀትር ጋኔል ፥ አንቺን ሳይ የምሸሽ
ይብላኝልኝና እኔ ምን ተዳዬ
የነጣ ነውና ፥ የራስ ቅል ጓዳዬ
የወጣ እንዳይገባ…
በአሚን መቀነት ፥ ታስሯል ህሊናዬ
፡፡፡፡፡፡፡
ካንቺ ዘንድ ከዋለው
ጅል መስሎ ጥበብን ፥ ከጉያሽ ካለበው
ውስጡ ሳይታወቅ ፥ ብክር ከተናቀው
ከጭምቱ ራሴ ፥ ከሰላው ሀሳቤ
ከ'ሊናዬ እልፍኝ ፥ በትረ ሙሴን ስቤ
እንደ ቀዩ ባህር…
እከፍልበታለው ፥ ..…ልብሽን ከልቤ
እንግዲስ ዳግማይ ፥ እጉያሽ መጥቼ
የተከለከለ እርምሽን ነክቼ
እንደ ብሉይ አካን፥እንዳይመታኝ ቅስፈት
ልቤን አስሪያለው
ኢያሱን ባስነባች ፥ ....በያሪኮ ግዝት
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
አሁን አቦልሽን
ቶና በረካሽን
ጨርሼ አከተምኩት
አዝመራው ሀሳቤን ፥ ውድማ በተንኩት
የሰላውን ማጭድ ፥ ከሰገባ ሳብኩት
እንደ ቅጠል በጣሽ…
ከልብሽ ቅርንጫፍ፥ተስፋዬን ቆረጥኩት
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ቢሆንም ቢሆንም...
ሆነሽኛልና ቆንጥጦ መካሪ
ላመስግንሽ እቱ ፥ እልፍ አመትን ኑሪ
ዮናስን በሆዱ…
ሦስት ቀን እንዳቆየ ፥ የተርሴስ አ'ንበሪ
አ'ርገሽዋልና…
ልቤን እንደልብሽ ፥ ተፍቶ አስተማሪ
.
« ሚኪ እንዳለ» @MMIKU
@getem
@getem
@getem
----------------
በሰፌድ ላይ ቀመር
በ.....…ላሜዳ* ባየር
ግብሬን አበጥሮ ፥ ልብሽ እንዲቀጥረኝ
ሙያዬን መዝኖ ፥ አይንሽም እንዲያየኝ
ሽርጥ አገልድሜ ፥ እጅጉን ብለፋ
ጋገርራ ገብቼ ፥ ...ቡኮ ሊጥ ባሰፋ
እስቲበስል ብዬ
በትዝታ ቅርቃር ፥ አንገቴን ብደፋ
ተኝቶ ነው ብለሽ
የምጣዴን ክዳን ፥ ያለጊዜው ከፍተሽ
አይኑ የፈዘዘ ፥ …አፍለኛን አውጥተሽ
እኔን ለማባረር…
ምህኛት ብታጪ፥የእንጀራ'ይን ቆጠርሽ
ይሁና ከበጀሽ…
በማይመስል ህጸፅ ፥ መንገድ ከከጀለሽ
ከማይሳሳቱ
መላእክት ሰባእቱ
...ምስለ አሐዱን ከሆንሽ
እንግዲስ እኔው ነኝ…
እንደ ቀትር ጋኔል ፥ አንቺን ሳይ የምሸሽ
ይብላኝልኝና እኔ ምን ተዳዬ
የነጣ ነውና ፥ የራስ ቅል ጓዳዬ
የወጣ እንዳይገባ…
በአሚን መቀነት ፥ ታስሯል ህሊናዬ
፡፡፡፡፡፡፡
ካንቺ ዘንድ ከዋለው
ጅል መስሎ ጥበብን ፥ ከጉያሽ ካለበው
ውስጡ ሳይታወቅ ፥ ብክር ከተናቀው
ከጭምቱ ራሴ ፥ ከሰላው ሀሳቤ
ከ'ሊናዬ እልፍኝ ፥ በትረ ሙሴን ስቤ
እንደ ቀዩ ባህር…
እከፍልበታለው ፥ ..…ልብሽን ከልቤ
እንግዲስ ዳግማይ ፥ እጉያሽ መጥቼ
የተከለከለ እርምሽን ነክቼ
እንደ ብሉይ አካን፥እንዳይመታኝ ቅስፈት
ልቤን አስሪያለው
ኢያሱን ባስነባች ፥ ....በያሪኮ ግዝት
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
አሁን አቦልሽን
ቶና በረካሽን
ጨርሼ አከተምኩት
አዝመራው ሀሳቤን ፥ ውድማ በተንኩት
የሰላውን ማጭድ ፥ ከሰገባ ሳብኩት
እንደ ቅጠል በጣሽ…
ከልብሽ ቅርንጫፍ፥ተስፋዬን ቆረጥኩት
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ቢሆንም ቢሆንም...
ሆነሽኛልና ቆንጥጦ መካሪ
ላመስግንሽ እቱ ፥ እልፍ አመትን ኑሪ
ዮናስን በሆዱ…
ሦስት ቀን እንዳቆየ ፥ የተርሴስ አ'ንበሪ
አ'ርገሽዋልና…
ልቤን እንደልብሽ ፥ ተፍቶ አስተማሪ
.
« ሚኪ እንዳለ» @MMIKU
@getem
@getem
@getem
👍3
አላማጣ ውየ መልሼ አላማጣ
በበሽታየ ላይ በሽታ ላመጣ።
ራያ ሜዳ ላይ፥
ጀምዓ ቀበሌ ሰደቃ አይታጣም
ላንቺ ይብላኝ እንጂ እኔስ ሸጋ አላጣም።
ላንቺ ይብላኝ እንጂ
ግባ ብሎ ለማኝ ዋጃ ላይ አላጣም።
ወሎ-ነገረ-ብዙ!!
@getem
@getem
@balmbaras
በበሽታየ ላይ በሽታ ላመጣ።
ራያ ሜዳ ላይ፥
ጀምዓ ቀበሌ ሰደቃ አይታጣም
ላንቺ ይብላኝ እንጂ እኔስ ሸጋ አላጣም።
ላንቺ ይብላኝ እንጂ
ግባ ብሎ ለማኝ ዋጃ ላይ አላጣም።
ወሎ-ነገረ-ብዙ!!
@getem
@getem
@balmbaras
ዝምታ እና ጨኸት✍
በዝምታ ውስጥ ሆነህ፤
ጩኸት እንዳለ፣ ለጉያህ መስክር፤
ዝምታ በራሱ…
ጩኸት እንደሆነ፣ በአፅኖት አስተውል፡፡
የዝምን ትርጉም፤
የጪጭን ሚስጥር፤
የረጭን ቅኔ፤
ከሌላው ነጥሎ ፣አሻቅቦ ላየ፤
እውነትን አጢኖ፣ በልክ ላስተዋለ፤
ዝምታ ይደመጣል!
ዝምታ ይሰማል!
ዝምታ ያወራል!
ዝምታ ያነባል!
ዝምታ ዝም ይላል!
ዝምታ ይጮሀል!
ከጩኸት ያለፈ ፣እሩቅ ያስተጋባል፤
ከዛ ከላይ ማዶ፣ ከአቀበቱ ግርጌ፤
…….ሁለት ቤቶች አሉ
በደራሲው ምናብ፣ ብዕር የተሳሉ፤
አንድ ደራሲ መትሮ፣ እሱ ያፀናቸው፤
ሁለት ቤቶች አሉ፣ ቀለም ሚለያቸው፤
እናም አንደኛው ቤት….
ሄድኩ መጣው በሚል፣ መብራት አሸብርቋል፤
የሙዚቃው ድምፀት፣ ሰላምን ይነሳል፤
እናም በዚች ቤት፤
ሰላማቸው ጠፍቶ፣ ሰላም ሚፈልጉ፤
ደስታን የተሳኑ ፣ፈገግታ ሚናፍቁ፤
ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ሁሉም ተሰብስበዋል፤
አንደኛው ብርጭቆውን፣ ከሌላው ያጋጫል፤
ልክ በሌለው አፍ ፣ላንቃውን ይከፍታል፤
ከሙዚቃው ቅኝት ፣በሚወጣው ዜማ፤
ይነጉዳል ብዙ ሰው፣ ልቡን እየሰማ፤
ዘላዩ ብዙ ነው፣ ወንበር ሰባሪ፤
ለራሱ ሚኖር ፣የጩኸት አዝማሪ፡፡
እናም በዚች ቤት…
የጨርቅ ብጣሽ ፣አገልድመው ካሉ፤
እርቃን ገላቸውን፣ ደምቀው ከሚታዩ፤
ከዉብ እንስቶች፣ ይሰማል ጫጫታ ፤
ቅምጥ ካበጃጁ፣ ይወጣል ሁካታ፤
እናም በዚች ቤት….
ጩኸት ከፍ ብሎ፣ ወሰን አልባ ሆኗል፤
ሰላም እየነሳ፣ ሰላምንም ሰቷል፡፡
ሁለተኛው ቤት ፣ደራሲው የሳለው፤
ቀለሙን ነክሮበተ፣ እራሱ የሰራው፤
ሁለተኛይቷ ይህች፣ ትንሽ ቤት፤
ዝምታ ዉጧታል ፤
ደጀን መሰሶዋን ፣ፀጥታ ረቧታል፡፡
በቤቱ ጥጋት፣ በመስኮቱ ትይዩ፤
ብዙ ሰዎች አሉ፤
ዝም ዝም ያሉ፡፡
ሁሉ ጨልሞበት፣ በድንግዝግዝ ያለ፤
ብቻውን የሚታይ፣ አንድ ወጣት አለ፤
እናም ይሄ ወጣት…
እናም የዚህ ወጣት፤
ልብሱ ተቀዳዷል
ሰው ሆኖ ፣ሰው አጥቷል፤
ሲጋራውን ይምጋል፤
ከሲጋራው ምገት ፣የሚወጣው ጭስ፤
አንዳች ሹክ ይለዋል፣ ለራሱ በሎሆሳስ፤
የጪሱን ፍኖት፣ እየተከተለ፤
በሀሳብ ዳክሮ፣ ላይ ታች እያለ፤
በቁሙ ያነባል፤
የሁለት እጆቹ ፣የመዳፉ መስመር ፤
ተቋጥሮ ሚፈታው፣ የግንባሩ ሸንተረር፤
ጥያቄ እንዳዘለ፣ ከሩቅ ያሳብቃል፤
እንኳን ለወዳጁ ፣ለባዳም ይታያል፤
የአይኑ መዝዉር ፣ፈጣሪን ይከሳል፤
የከንፈሩ መድረቅ፣ ሄዋንን ይወቅሳል፤
ደረት መደቃቱ ፣ብዙ የጎደለዉ፤
መልስ ያጣ ጥያቄ፣ ነፍሱን የጠፈረዉ፤
የደራሲዉ ዉጤት፤
እናም ይሄ ወጣት፤
ከሰው ተነጥሎ፤
በፊናዉ ዘምኖ፤
ዝም ብሎ ፣ዝም ማለት ተስኖት፤
የራሱ ማንነት ፣ጩኸትን ለግሶት፤
ከራሱ ተጣልቶ፣ ህልዉናዉ በኖ፤
እየጮኸ ይኖራል ፣በዝምታ ዉስጥ ሆኖ፡፡
እናም በዚች ቤት…..
ዝምታ ንጉስ ነዉ፤
ሁሉም ሚቀበለዉ፤
ቤቱ ያነገሰዉ፤
ፉት ፉት እያሉ፣ የሀሳብን መጠጥ፤
ዝምታን ተችረዉ ፣አርገውት ዘውድ እና ጌጥ፤
እኮ በዚች ቤት ፣የሚያወራ የለም፤ መለፈፍ ሚፈልግ፣ ከቶ አይታም፤
ግን…..
የውስጥ ጩኸት አለ፣ ከሁሉ ሚወጣ፤
ዝምታን ሸልሞ፣ ደስታን ያሳጣ፤
እናልህ ዘመዴ….
ዝምታ ይደመጣል፤
ዝምታ ይሰማል፤
ዝምታ ያወራል፤
ዝምታ ያነባል፤
ዝምታ ይጮሀል!
ከጩኸት ያለፈ፣ እሩቅ ያስተጋባል!!
በበዛብህ ብርሃኑ ከ የይሁዳ ገመድ ላይ የተሸመተ✍✍✍²
@getem
@getem
@getem
በዝምታ ውስጥ ሆነህ፤
ጩኸት እንዳለ፣ ለጉያህ መስክር፤
ዝምታ በራሱ…
ጩኸት እንደሆነ፣ በአፅኖት አስተውል፡፡
የዝምን ትርጉም፤
የጪጭን ሚስጥር፤
የረጭን ቅኔ፤
ከሌላው ነጥሎ ፣አሻቅቦ ላየ፤
እውነትን አጢኖ፣ በልክ ላስተዋለ፤
ዝምታ ይደመጣል!
ዝምታ ይሰማል!
ዝምታ ያወራል!
ዝምታ ያነባል!
ዝምታ ዝም ይላል!
ዝምታ ይጮሀል!
ከጩኸት ያለፈ ፣እሩቅ ያስተጋባል፤
ከዛ ከላይ ማዶ፣ ከአቀበቱ ግርጌ፤
…….ሁለት ቤቶች አሉ
በደራሲው ምናብ፣ ብዕር የተሳሉ፤
አንድ ደራሲ መትሮ፣ እሱ ያፀናቸው፤
ሁለት ቤቶች አሉ፣ ቀለም ሚለያቸው፤
እናም አንደኛው ቤት….
ሄድኩ መጣው በሚል፣ መብራት አሸብርቋል፤
የሙዚቃው ድምፀት፣ ሰላምን ይነሳል፤
እናም በዚች ቤት፤
ሰላማቸው ጠፍቶ፣ ሰላም ሚፈልጉ፤
ደስታን የተሳኑ ፣ፈገግታ ሚናፍቁ፤
ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ሁሉም ተሰብስበዋል፤
አንደኛው ብርጭቆውን፣ ከሌላው ያጋጫል፤
ልክ በሌለው አፍ ፣ላንቃውን ይከፍታል፤
ከሙዚቃው ቅኝት ፣በሚወጣው ዜማ፤
ይነጉዳል ብዙ ሰው፣ ልቡን እየሰማ፤
ዘላዩ ብዙ ነው፣ ወንበር ሰባሪ፤
ለራሱ ሚኖር ፣የጩኸት አዝማሪ፡፡
እናም በዚች ቤት…
የጨርቅ ብጣሽ ፣አገልድመው ካሉ፤
እርቃን ገላቸውን፣ ደምቀው ከሚታዩ፤
ከዉብ እንስቶች፣ ይሰማል ጫጫታ ፤
ቅምጥ ካበጃጁ፣ ይወጣል ሁካታ፤
እናም በዚች ቤት….
ጩኸት ከፍ ብሎ፣ ወሰን አልባ ሆኗል፤
ሰላም እየነሳ፣ ሰላምንም ሰቷል፡፡
ሁለተኛው ቤት ፣ደራሲው የሳለው፤
ቀለሙን ነክሮበተ፣ እራሱ የሰራው፤
ሁለተኛይቷ ይህች፣ ትንሽ ቤት፤
ዝምታ ዉጧታል ፤
ደጀን መሰሶዋን ፣ፀጥታ ረቧታል፡፡
በቤቱ ጥጋት፣ በመስኮቱ ትይዩ፤
ብዙ ሰዎች አሉ፤
ዝም ዝም ያሉ፡፡
ሁሉ ጨልሞበት፣ በድንግዝግዝ ያለ፤
ብቻውን የሚታይ፣ አንድ ወጣት አለ፤
እናም ይሄ ወጣት…
እናም የዚህ ወጣት፤
ልብሱ ተቀዳዷል
ሰው ሆኖ ፣ሰው አጥቷል፤
ሲጋራውን ይምጋል፤
ከሲጋራው ምገት ፣የሚወጣው ጭስ፤
አንዳች ሹክ ይለዋል፣ ለራሱ በሎሆሳስ፤
የጪሱን ፍኖት፣ እየተከተለ፤
በሀሳብ ዳክሮ፣ ላይ ታች እያለ፤
በቁሙ ያነባል፤
የሁለት እጆቹ ፣የመዳፉ መስመር ፤
ተቋጥሮ ሚፈታው፣ የግንባሩ ሸንተረር፤
ጥያቄ እንዳዘለ፣ ከሩቅ ያሳብቃል፤
እንኳን ለወዳጁ ፣ለባዳም ይታያል፤
የአይኑ መዝዉር ፣ፈጣሪን ይከሳል፤
የከንፈሩ መድረቅ፣ ሄዋንን ይወቅሳል፤
ደረት መደቃቱ ፣ብዙ የጎደለዉ፤
መልስ ያጣ ጥያቄ፣ ነፍሱን የጠፈረዉ፤
የደራሲዉ ዉጤት፤
እናም ይሄ ወጣት፤
ከሰው ተነጥሎ፤
በፊናዉ ዘምኖ፤
ዝም ብሎ ፣ዝም ማለት ተስኖት፤
የራሱ ማንነት ፣ጩኸትን ለግሶት፤
ከራሱ ተጣልቶ፣ ህልዉናዉ በኖ፤
እየጮኸ ይኖራል ፣በዝምታ ዉስጥ ሆኖ፡፡
እናም በዚች ቤት…..
ዝምታ ንጉስ ነዉ፤
ሁሉም ሚቀበለዉ፤
ቤቱ ያነገሰዉ፤
ፉት ፉት እያሉ፣ የሀሳብን መጠጥ፤
ዝምታን ተችረዉ ፣አርገውት ዘውድ እና ጌጥ፤
እኮ በዚች ቤት ፣የሚያወራ የለም፤ መለፈፍ ሚፈልግ፣ ከቶ አይታም፤
ግን…..
የውስጥ ጩኸት አለ፣ ከሁሉ ሚወጣ፤
ዝምታን ሸልሞ፣ ደስታን ያሳጣ፤
እናልህ ዘመዴ….
ዝምታ ይደመጣል፤
ዝምታ ይሰማል፤
ዝምታ ያወራል፤
ዝምታ ያነባል፤
ዝምታ ይጮሀል!
ከጩኸት ያለፈ፣ እሩቅ ያስተጋባል!!
በበዛብህ ብርሃኑ ከ የይሁዳ ገመድ ላይ የተሸመተ✍✍✍²
@getem
@getem
@getem
👍1
ካድሚኝ አለሜ
ከቡና ገበታ
ሥኒ ከሞላው
ጆሮ ማንጠልጠያ
ሎቲ ከቀረው
አልያም በድፍኑ
ማድመጫ አልባው
ጨው ከስኳር ጋራ
በአይነት ቀርበው
የወሎ ጢስ 'ባይነት
በከሠል አፍኖ ጢስ ከሚያሥነባው
ከቡናሽ ማጀት ስር
ዱካ ላይ ቁጭ ብዬ
የፈካ ፈንድሻ
ይዤ በጉያዬ
እግሬ ካረፈበት
ለምለሙ ቄጠማ
እጄ ከሰደደው
የዳቦ አውድማ
በጣቴ ቆንጥሬ
ሥልከው ከአፌ
በድንገት ባነንኩኝ
ጣት ጣቴን ቀርጥፌ
እናማ
እናማ ከአቦሉ
ከቶና በረካ
የጠጣሁት ቡና
ልብን የሚያረካ
ነበርና ውዴ
ጥዑም አፈላልሽ
ይሁን አሚን በይኝ
እኔም ልመርቅሽ
በይ ጀባ ልበልሽ
ው ሠጅ ምርቃቴን
እንደሼሁ ባልችል
ባይመስል የቄሡን
አሜን በይ አለሜ
ልዘይርሽና ይብዛልኝ ሰላሜ
የመካ'ን ዛውያ
ያድርገው እድሜሽን
ኢማን ይሙላሽ ኣቦ
ያድርግሽ በረካ
ወሥዶ ይመልሥሽ
መዲናና መካ
አንቺም በይ መረባ
ከነ ሙሉ ሲኒሽ ከነ ግሳንግሱ
ሀጃ እንዲያወጣ
እንዳይበርድ ድግሱ
በፀባዖት 12/12/2011
@getem
@getem
@getem
ከቡና ገበታ
ሥኒ ከሞላው
ጆሮ ማንጠልጠያ
ሎቲ ከቀረው
አልያም በድፍኑ
ማድመጫ አልባው
ጨው ከስኳር ጋራ
በአይነት ቀርበው
የወሎ ጢስ 'ባይነት
በከሠል አፍኖ ጢስ ከሚያሥነባው
ከቡናሽ ማጀት ስር
ዱካ ላይ ቁጭ ብዬ
የፈካ ፈንድሻ
ይዤ በጉያዬ
እግሬ ካረፈበት
ለምለሙ ቄጠማ
እጄ ከሰደደው
የዳቦ አውድማ
በጣቴ ቆንጥሬ
ሥልከው ከአፌ
በድንገት ባነንኩኝ
ጣት ጣቴን ቀርጥፌ
እናማ
እናማ ከአቦሉ
ከቶና በረካ
የጠጣሁት ቡና
ልብን የሚያረካ
ነበርና ውዴ
ጥዑም አፈላልሽ
ይሁን አሚን በይኝ
እኔም ልመርቅሽ
በይ ጀባ ልበልሽ
ው ሠጅ ምርቃቴን
እንደሼሁ ባልችል
ባይመስል የቄሡን
አሜን በይ አለሜ
ልዘይርሽና ይብዛልኝ ሰላሜ
የመካ'ን ዛውያ
ያድርገው እድሜሽን
ኢማን ይሙላሽ ኣቦ
ያድርግሽ በረካ
ወሥዶ ይመልሥሽ
መዲናና መካ
አንቺም በይ መረባ
ከነ ሙሉ ሲኒሽ ከነ ግሳንግሱ
ሀጃ እንዲያወጣ
እንዳይበርድ ድግሱ
በፀባዖት 12/12/2011
@getem
@getem
@getem
👍1
አረዳድ 18+(ልዑል ሃይሌ)
ስለፍቅር ሲባል 'ሄዳለሁ ያለበት፤
ደከመኝ አልልም
አንቺን ለማስረዳት የለም ማልገባበት፤
ብቻ ምን አለፋሽ
ይሆናል ያሰብሽው፤
አስታውሠዋለሁ
አንቺም እንዳትረሽው፤
.
ይኸው ላንቺ ስል ነው...
ፍቅሬ ለመሆንሽ ምስክር ፍለጋ፤
ሄጄ ልመጣ ነው ሌላዋ ሚስቴ ጋ፤
ድንገት እንደው ድንገት
አልጋ ላይ ሌላ ሴት አቅፌ ብታይኝ፤
ሌላ ነገር መስሎሽ እንዳትጠረጥሪኝ፤
ይልቅ እስክጨርስ ዝም ብለሽ እዪኝ፤
እዪኝ!
.
እዪኝ!
.
እዪኝ!
.
አየሽው አይደለ
የምትጠረጥሪው እንዳልተፈጠረ፤
ፍቅር ዕውር ሆኖ ባንቺ እንዳላደረ፤
እሱን ላሳይሽ ነው ይህ ሁሉ ድካሜ፤
ካልገባሽ ንገሪኝ ላሳይሽ ደግሜ፤
እንዳንቺ አይነት ሰዎች
ዓይናማውን ፍቅር እውር እያደረጉ፤
እኛን ለምሳሌ
እያደከሙን ነው ከሌላ እያስጠጉ፤
ይኸው አንቺም ደግሞ...
ፍቅር ይጋርዳል እውር ነው ብለሺኝ፤
ሌላ ሴት ጋ ስሄድ ታዲያ እንዴት አየሽኝ?፤
.
ኩኩሉ!
.
18-12-2011 ዓ.ም.
@getem
@getem
@getem
ስለፍቅር ሲባል 'ሄዳለሁ ያለበት፤
ደከመኝ አልልም
አንቺን ለማስረዳት የለም ማልገባበት፤
ብቻ ምን አለፋሽ
ይሆናል ያሰብሽው፤
አስታውሠዋለሁ
አንቺም እንዳትረሽው፤
.
ይኸው ላንቺ ስል ነው...
ፍቅሬ ለመሆንሽ ምስክር ፍለጋ፤
ሄጄ ልመጣ ነው ሌላዋ ሚስቴ ጋ፤
ድንገት እንደው ድንገት
አልጋ ላይ ሌላ ሴት አቅፌ ብታይኝ፤
ሌላ ነገር መስሎሽ እንዳትጠረጥሪኝ፤
ይልቅ እስክጨርስ ዝም ብለሽ እዪኝ፤
እዪኝ!
.
እዪኝ!
.
እዪኝ!
.
አየሽው አይደለ
የምትጠረጥሪው እንዳልተፈጠረ፤
ፍቅር ዕውር ሆኖ ባንቺ እንዳላደረ፤
እሱን ላሳይሽ ነው ይህ ሁሉ ድካሜ፤
ካልገባሽ ንገሪኝ ላሳይሽ ደግሜ፤
እንዳንቺ አይነት ሰዎች
ዓይናማውን ፍቅር እውር እያደረጉ፤
እኛን ለምሳሌ
እያደከሙን ነው ከሌላ እያስጠጉ፤
ይኸው አንቺም ደግሞ...
ፍቅር ይጋርዳል እውር ነው ብለሺኝ፤
ሌላ ሴት ጋ ስሄድ ታዲያ እንዴት አየሽኝ?፤
.
ኩኩሉ!
.
18-12-2011 ዓ.ም.
@getem
@getem
@getem
❤1
*የቃልሽ ፍሬ*
ልበ ስውር ነበርኩ
ውስጤ የታጠረ ባለማመን ክምር
ቀልቤ የሸፈተ
አካሌ ደንዳና የማይበላው አፈር
ብቻ ሆድ ይፍጀው
መንፈሴን በትኜ ከዚ አለም የጠፋው
ስውር ነበርኩ ያኔ
ውስጤ ማይፈታ እንደ ጌታው ቅኔ
እና ዛሬ እና ዛሬ
እህል ተዘርቶብኝ ማላፈራ ፍሬ
አሁን ለማው መሰል
አሁን ሳሳው መሰል
በከንፈርሽ ውሃ
በከንፈርሽ ዝና ረጠብኩኝ መሰል
እናም እናም
ካፍሽ የሚወጣው ያ መልካሙ ፍሬ
ካካሌ ላይ ወድቆ አፈራሁኝ ዛሬ
ይስሐቅ አሰፋ ( izak)
@getem
@getem
@gebriel_19
ልበ ስውር ነበርኩ
ውስጤ የታጠረ ባለማመን ክምር
ቀልቤ የሸፈተ
አካሌ ደንዳና የማይበላው አፈር
ብቻ ሆድ ይፍጀው
መንፈሴን በትኜ ከዚ አለም የጠፋው
ስውር ነበርኩ ያኔ
ውስጤ ማይፈታ እንደ ጌታው ቅኔ
እና ዛሬ እና ዛሬ
እህል ተዘርቶብኝ ማላፈራ ፍሬ
አሁን ለማው መሰል
አሁን ሳሳው መሰል
በከንፈርሽ ውሃ
በከንፈርሽ ዝና ረጠብኩኝ መሰል
እናም እናም
ካፍሽ የሚወጣው ያ መልካሙ ፍሬ
ካካሌ ላይ ወድቆ አፈራሁኝ ዛሬ
ይስሐቅ አሰፋ ( izak)
@getem
@getem
@gebriel_19
👍1
#የጨካኝ_ሰው_ጥበብ
-
ለለስላሳው እግሬ ፥ አለት አፍራሽ ጫማ
ለወስዋሳው ልቤ ፥ አፅናኝ ፋጨት ዜማ፣
ስበት ህጉን ሽሬ ፥ ባየር እስክንሳፈፍ
ሸ..ከ..ተ..ፍ! ....... ሸ..ከ..ተ..ፍ!!...
-
እንዲያ ሁኜ ስነጉድ ፥ ከራስ ጋ ውድድር
ከሩቅ ሲሮጥ ታየኝ ፥ አንዱ በባዶ እግር!
..... ወ.ይ.ኔ ... ሲ..ያ..ሳ..ዝ..ን!!
-
ወየው! .... ኧረ ወየው!
መከራን በመፍራት ፥ መከራ ገበየሁ
. እኔ እሱን እያየሁ!!
-
ካሁን አሁን እያልኩ ፥ ስሳቀቅ ስሰጋው
ድንጋይ እንዳይልጠው ፥ እሾህ እንዳይወጋው፣ ...
... ምፅ!
ለሟች ከንፈር መጣጭ ፥ ወዮልኝ ለራሴ
ከጉድጓድ ወድቄ ፥ ተ..ለ..ቀ..መ ጥርሴ!!!
-
-
ያኔ ነው የገባኝ
ምስጢር የተረዳኝ!
-
ከሩህሩሁ ይልቅ ፥ ጨካኝ መሰንበቱ
አለመራመጃው ፥ ሌላ አለማየቱ ፨
----------------//---------------
(በርናባስ ከበደ)
@getem
@getem
@getem
-
ለለስላሳው እግሬ ፥ አለት አፍራሽ ጫማ
ለወስዋሳው ልቤ ፥ አፅናኝ ፋጨት ዜማ፣
ስበት ህጉን ሽሬ ፥ ባየር እስክንሳፈፍ
ሸ..ከ..ተ..ፍ! ....... ሸ..ከ..ተ..ፍ!!...
-
እንዲያ ሁኜ ስነጉድ ፥ ከራስ ጋ ውድድር
ከሩቅ ሲሮጥ ታየኝ ፥ አንዱ በባዶ እግር!
..... ወ.ይ.ኔ ... ሲ..ያ..ሳ..ዝ..ን!!
-
ወየው! .... ኧረ ወየው!
መከራን በመፍራት ፥ መከራ ገበየሁ
. እኔ እሱን እያየሁ!!
-
ካሁን አሁን እያልኩ ፥ ስሳቀቅ ስሰጋው
ድንጋይ እንዳይልጠው ፥ እሾህ እንዳይወጋው፣ ...
... ምፅ!
ለሟች ከንፈር መጣጭ ፥ ወዮልኝ ለራሴ
ከጉድጓድ ወድቄ ፥ ተ..ለ..ቀ..መ ጥርሴ!!!
-
-
ያኔ ነው የገባኝ
ምስጢር የተረዳኝ!
-
ከሩህሩሁ ይልቅ ፥ ጨካኝ መሰንበቱ
አለመራመጃው ፥ ሌላ አለማየቱ ፨
----------------//---------------
(በርናባስ ከበደ)
@getem
@getem
@getem
👍1
👍1