"ወርቅ ሲመሰጠር"
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።።።
ጭንቁ አልባስ ሆኖት ፥ ሜዳ ለወደቀ
ሆዱን እህል ናፍቆት ፥ አካሉ ላለቀ
ተስፋው ለደቀቀ!
እሳት ላደባየው ፥ ህላዌው ተማግዶ
አመዱ ለሚታይ ፥ ምጥን ስጋው ነዶ
ለዛ ምስኪን ነዳይ !
"ጌታን ካልተቀበልህ ፥ እሳት ይበላሀል"
ብለህ ስትሰብከው ፥ ቆመህ ካደባባይ
የቃል ዛቻ ቆጥሮ
ለነፍሱ ደንብሮ
ጌታውን ባይቀበል
ለምን ሳተ ? አትበል
ከሚዛን አትቅለል።
.
አንተ ባለ ስንጥር!
ቁስል ባየህ ቁጥር ፥ የ'ጅህን አትወርውር።
ይልቅ መጣፍ ግለጥ...
ድፍኑ ተስፋውን ፥ በቃል ምሳር ፍለጥ ።
ይሄ ያልኩህ ንጉስ!
የሰበክሁህ ጌታ !
እንኳን ክቡሩን ሰው ፥ መልኩን ለወረሰው
በአርያው በአምሳሉ ፥ ፈጥሮ ላበጃጀው
ተከፍቶ የቆየ ፥ ጉሮሮውን አይቶ
አሞራ ይመግባል ፥ ህብስቱን አብዝቶ።
ብለህ ተናገረው...
ተስፋውን ቀጥለው
አስፈራርተህ ሳይሆን ፥ ፍቅርን ችረህ ሳበው።
ደግሞም ይሄ ምስኪን!
ያልከው ውሉ ጠፍቶት ፥ ዳግም ከጠየቀ
ከሠሙ አንደበትህ...
ወርቁን ማወቅ ሽቶ ፥ ምናቡን ካራቀ
አሞራ የምልህ ...
አይደለም በራሪው !
አይደለም አዕዋፉ !
አሞራው እኛ ነን ፥ አዳም ባለ ክንፉ
ሁሉ ምሉዕ ሆኖ ፥ አንዳች ሳይጎልበት
በሄዱበት መክሰም ፥ 'መልመድ ልምድ ' ሆኖበት
ለመልዕክት ሲሰዱት ...
እሺ ብሎ በሮ ፥ መምጣት ያልቻለበት
ብለህ መልስለት! !
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።።።
ጭንቁ አልባስ ሆኖት ፥ ሜዳ ለወደቀ
ሆዱን እህል ናፍቆት ፥ አካሉ ላለቀ
ተስፋው ለደቀቀ!
እሳት ላደባየው ፥ ህላዌው ተማግዶ
አመዱ ለሚታይ ፥ ምጥን ስጋው ነዶ
ለዛ ምስኪን ነዳይ !
"ጌታን ካልተቀበልህ ፥ እሳት ይበላሀል"
ብለህ ስትሰብከው ፥ ቆመህ ካደባባይ
የቃል ዛቻ ቆጥሮ
ለነፍሱ ደንብሮ
ጌታውን ባይቀበል
ለምን ሳተ ? አትበል
ከሚዛን አትቅለል።
.
አንተ ባለ ስንጥር!
ቁስል ባየህ ቁጥር ፥ የ'ጅህን አትወርውር።
ይልቅ መጣፍ ግለጥ...
ድፍኑ ተስፋውን ፥ በቃል ምሳር ፍለጥ ።
ይሄ ያልኩህ ንጉስ!
የሰበክሁህ ጌታ !
እንኳን ክቡሩን ሰው ፥ መልኩን ለወረሰው
በአርያው በአምሳሉ ፥ ፈጥሮ ላበጃጀው
ተከፍቶ የቆየ ፥ ጉሮሮውን አይቶ
አሞራ ይመግባል ፥ ህብስቱን አብዝቶ።
ብለህ ተናገረው...
ተስፋውን ቀጥለው
አስፈራርተህ ሳይሆን ፥ ፍቅርን ችረህ ሳበው።
ደግሞም ይሄ ምስኪን!
ያልከው ውሉ ጠፍቶት ፥ ዳግም ከጠየቀ
ከሠሙ አንደበትህ...
ወርቁን ማወቅ ሽቶ ፥ ምናቡን ካራቀ
አሞራ የምልህ ...
አይደለም በራሪው !
አይደለም አዕዋፉ !
አሞራው እኛ ነን ፥ አዳም ባለ ክንፉ
ሁሉ ምሉዕ ሆኖ ፥ አንዳች ሳይጎልበት
በሄዱበት መክሰም ፥ 'መልመድ ልምድ ' ሆኖበት
ለመልዕክት ሲሰዱት ...
እሺ ብሎ በሮ ፥ መምጣት ያልቻለበት
ብለህ መልስለት! !
@getem
@getem
@getem
:
ስጁድህን ወርደህ ገና በጅማሮ ሳትጨርስ ረ' ካ፤
እንኳንስ ጀሊሉ ፤
መለይካው ልጅ ሁኖ ያረበና እያለ ይስምሃል ለካ ።
መልካም ጁምኣ!!!💚💛❤
@getem
@getem
@balmbaras
ስጁድህን ወርደህ ገና በጅማሮ ሳትጨርስ ረ' ካ፤
እንኳንስ ጀሊሉ ፤
መለይካው ልጅ ሁኖ ያረበና እያለ ይስምሃል ለካ ።
መልካም ጁምኣ!!!💚💛❤
@getem
@getem
@balmbaras
" ልጄ "
( በአምባዬ ጌታነህ )
አንደበቱ ጣፋጭ ንግግሩ እውነት፣
ያስደስታል በጣም ልጅ ሲቦርቅ ከቤት።
ሲኮላተፍ ሲስቅ ሲራመድ ሲያወራ፣
ሲጫወት ሲያለቅስ ሲተኛ ሲፈራ፣
አለም አይደል እንዴ መኖር ከልጅ ጋራ።
፡
መረበሽ ነው እንጅ ተው ብትል አይሰማ፣
ተው ማለት አርግ ነው በልጅ ቋንቋ ዜማ።
ልጅ ቤት ሲኖር አይደል፣
ጎጆ የሚመስል፣ ከሩቅ ሆኖ ሲታይ፣
ያትረፈርፈዋል ልጅ ነው ትልቅ ሲሳይ።
፡
ሙሉ ነው ጎጆየ የለም የጎደለኝ፣
ስገባ ልጄ አለ አባየ የሚለኝ።
@amba8
@getem
@getem
@amba88
( በአምባዬ ጌታነህ )
አንደበቱ ጣፋጭ ንግግሩ እውነት፣
ያስደስታል በጣም ልጅ ሲቦርቅ ከቤት።
ሲኮላተፍ ሲስቅ ሲራመድ ሲያወራ፣
ሲጫወት ሲያለቅስ ሲተኛ ሲፈራ፣
አለም አይደል እንዴ መኖር ከልጅ ጋራ።
፡
መረበሽ ነው እንጅ ተው ብትል አይሰማ፣
ተው ማለት አርግ ነው በልጅ ቋንቋ ዜማ።
ልጅ ቤት ሲኖር አይደል፣
ጎጆ የሚመስል፣ ከሩቅ ሆኖ ሲታይ፣
ያትረፈርፈዋል ልጅ ነው ትልቅ ሲሳይ።
፡
ሙሉ ነው ጎጆየ የለም የጎደለኝ፣
ስገባ ልጄ አለ አባየ የሚለኝ።
@amba8
@getem
@getem
@amba88
ማፍቀር መታደል ነው!!!
(ቡሩክ ካሳሁን)
እኔን ከማይጥሙኝ ከማልስማማበት
አባባሎች መሃል ሊይውም በዋናነት
ስህተታዊ ሃሳብ በውስጡ የያዘው
ምንድን ነው? ብትሉኝ ‹ማፍቀር መታደል ነው›
ማፍቀር መታደል ነው አዘውትረው ሚሉ
ፍቅር ያልገባቸው አወቅን ባይ ሁሉ
ቢገባቸውማ መቼ እንዲህ ይላሉ!
የእውነት ላፈቀረ ማፍቀር ስህተት ነው
የፍቅሩን ጥልቅነት ዝምብሎ ሲያጤነው
ከራሱ አብልጦ ለሌላው ማሰቡ
መጨነቁ ሁሉ አብዝቶ ከልቡ
ስህተት ሆነበት ሲያስበው ሲያስበው
ምክንያቱ ምንድን ነው?
ፍቅሩ የእውነት ነው!!!
ማፍቀር መታደል ነው እነማነው ሚሉት?
የናንተን እኔንጃ እስኪ የኔን ስሙት
እኔን የሚመስለኝ ወይ የተፈቀሩ
አለበለዚያ ግን የውሸት ያፈቀሩ።
ስለምን ይላሉ እነዚ ሁለቱ
የተመረጡበት ምንድን ነው ምክንያቱ?
ፍቅር በዚህ አለም ባይኖረውም ፍቺ
ተመጣጣኝ ሚሆን ለመግለጽ አመቺ
ላስተዋለው ሰው ግን ሳይሆን ከላይ ከላይ
ፍ.ቅርን ይለዋል ደስ የሚል ስቃይ
ከዚህ ተነስታቹ የፍቅርን ፍቺ ትርጉም ስትባሉ
ምንም ሳታቅማሙ ስቃይ ለምትሉ
‹ይህን ስቃይ በዝች አለም
የሚገልጸው ቃላት የለም›
እንዳለው ዘፋኙ
እውነቱን ነውና በሉ አተሞኙ
ስቃይ ፍቺው ባይሆን ባይተጉመውም
ግን ተጠቀሙበት እንደ ተውላጠ ስም
ታዲያ ለምንድን ነው አዘውትረው ሚሉት
የተፈቀሩና የውሸት ያፈቀሩት
ምንስ አገዳቸው እንዲህ እንዳይሉ?
የእውነት አፍቅረው ፍቅርን ስላላዩ
የእውነት አፍቅረው ስቃይ ስላላዩ
ለዚህ ነው ማይጥመኝ ስሰማው ሚቀፈኝ
ለሽንገላ ቃላት ቦታ ስለሌለኝ
ማፍቀርን በራሱ ካሉ መታደል ነው
መፈቀርስ ደሞ ኸረ እስኪ ምንድን ነው?
ይልቁንስ ማፍቀር መታደል ሚሆነው
ያፈቀሩትን ሰው ከእጆ ካስገቡ ነው
ከእጃቸው ያስገቡ አባባሉን ቢሉ
ለትንሽ ትልቁ ለጠየቁ ሁሉ
ብላቹ አታስቡ የውነት ከልባቸው ስላላፈቀሩ
መሆኑ ነው እንጂ በተዘዋዋሪ ስለተፈቀሩ፡፡
24/10/2006
ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል ለመቀላቀል👇
@burukassahunc
@getem
@getem
@getem
(ቡሩክ ካሳሁን)
እኔን ከማይጥሙኝ ከማልስማማበት
አባባሎች መሃል ሊይውም በዋናነት
ስህተታዊ ሃሳብ በውስጡ የያዘው
ምንድን ነው? ብትሉኝ ‹ማፍቀር መታደል ነው›
ማፍቀር መታደል ነው አዘውትረው ሚሉ
ፍቅር ያልገባቸው አወቅን ባይ ሁሉ
ቢገባቸውማ መቼ እንዲህ ይላሉ!
የእውነት ላፈቀረ ማፍቀር ስህተት ነው
የፍቅሩን ጥልቅነት ዝምብሎ ሲያጤነው
ከራሱ አብልጦ ለሌላው ማሰቡ
መጨነቁ ሁሉ አብዝቶ ከልቡ
ስህተት ሆነበት ሲያስበው ሲያስበው
ምክንያቱ ምንድን ነው?
ፍቅሩ የእውነት ነው!!!
ማፍቀር መታደል ነው እነማነው ሚሉት?
የናንተን እኔንጃ እስኪ የኔን ስሙት
እኔን የሚመስለኝ ወይ የተፈቀሩ
አለበለዚያ ግን የውሸት ያፈቀሩ።
ስለምን ይላሉ እነዚ ሁለቱ
የተመረጡበት ምንድን ነው ምክንያቱ?
ፍቅር በዚህ አለም ባይኖረውም ፍቺ
ተመጣጣኝ ሚሆን ለመግለጽ አመቺ
ላስተዋለው ሰው ግን ሳይሆን ከላይ ከላይ
ፍ.ቅርን ይለዋል ደስ የሚል ስቃይ
ከዚህ ተነስታቹ የፍቅርን ፍቺ ትርጉም ስትባሉ
ምንም ሳታቅማሙ ስቃይ ለምትሉ
‹ይህን ስቃይ በዝች አለም
የሚገልጸው ቃላት የለም›
እንዳለው ዘፋኙ
እውነቱን ነውና በሉ አተሞኙ
ስቃይ ፍቺው ባይሆን ባይተጉመውም
ግን ተጠቀሙበት እንደ ተውላጠ ስም
ታዲያ ለምንድን ነው አዘውትረው ሚሉት
የተፈቀሩና የውሸት ያፈቀሩት
ምንስ አገዳቸው እንዲህ እንዳይሉ?
የእውነት አፍቅረው ፍቅርን ስላላዩ
የእውነት አፍቅረው ስቃይ ስላላዩ
ለዚህ ነው ማይጥመኝ ስሰማው ሚቀፈኝ
ለሽንገላ ቃላት ቦታ ስለሌለኝ
ማፍቀርን በራሱ ካሉ መታደል ነው
መፈቀርስ ደሞ ኸረ እስኪ ምንድን ነው?
ይልቁንስ ማፍቀር መታደል ሚሆነው
ያፈቀሩትን ሰው ከእጆ ካስገቡ ነው
ከእጃቸው ያስገቡ አባባሉን ቢሉ
ለትንሽ ትልቁ ለጠየቁ ሁሉ
ብላቹ አታስቡ የውነት ከልባቸው ስላላፈቀሩ
መሆኑ ነው እንጂ በተዘዋዋሪ ስለተፈቀሩ፡፡
24/10/2006
ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል ለመቀላቀል👇
@burukassahunc
@getem
@getem
@getem
#የናቴ~ልጅ~እኔ
፡
ከፊትሽ ገፅ ላይ
ቁጭት አነባለሁ
ማየትን የጠላ ማንነት እረክሶ
ጥርስሽ ይናገራል
የልብሽን ሚስጥር ከንፈርሽን ነክሶ
፡
ጠይም ወዘናሽም
ሀበሻዊነቱን ማርጀትሽ ሳይነጥቀው
የግንባርሽ ሽብሽብ
ያ'ይኖችሽን ብሌን እይታ ሳይሰርቀው
፡
ባገር ተመስሎ
እልፍ አንቺነትሽን በግልፅ እያወጋኝ
የዛሬው እኛነት
ካንቺ ሲነፃፀር ብርታቴ አሰጋኝ፡፡
፡
ግና ተስፋ አልቆርጥም
የደምሽ ውጤት ነኝ ካንቺው የተቀዳው
ለዚህ ነው እምዬ
ሺ ዘመን ቢቀየር
በ'ናትና ባ'ገር የማላወላዳው፡፡
ልብ አልባው ገጣሚ
@getem
@getem
@getem
፡
ከፊትሽ ገፅ ላይ
ቁጭት አነባለሁ
ማየትን የጠላ ማንነት እረክሶ
ጥርስሽ ይናገራል
የልብሽን ሚስጥር ከንፈርሽን ነክሶ
፡
ጠይም ወዘናሽም
ሀበሻዊነቱን ማርጀትሽ ሳይነጥቀው
የግንባርሽ ሽብሽብ
ያ'ይኖችሽን ብሌን እይታ ሳይሰርቀው
፡
ባገር ተመስሎ
እልፍ አንቺነትሽን በግልፅ እያወጋኝ
የዛሬው እኛነት
ካንቺ ሲነፃፀር ብርታቴ አሰጋኝ፡፡
፡
ግና ተስፋ አልቆርጥም
የደምሽ ውጤት ነኝ ካንቺው የተቀዳው
ለዚህ ነው እምዬ
ሺ ዘመን ቢቀየር
በ'ናትና ባ'ገር የማላወላዳው፡፡
ልብ አልባው ገጣሚ
@getem
@getem
@getem
ብላችሁን እንጅ፤
ነግራችሁን እንጅ፤
ጎጆአችን ፈራርሶ በትልቅ አዳራሽ እንተካው ብላችሁ ፤
ምነው በስተማታ ፤
ተሰርቶ ሲያበቃ አናስገባም የሚል ነገር አመጣችሁ ፤
አደራ እንዳትረሱ ፤ ፤
የክብሪት ዘመዶች፤
ዛሬም ማንደጃውን በገል ተሸክመን አለን በቤታችሁ ።
(( ጃ ኖ ))💚💛❤
@balmbaras
@getem
@getem
ነግራችሁን እንጅ፤
ጎጆአችን ፈራርሶ በትልቅ አዳራሽ እንተካው ብላችሁ ፤
ምነው በስተማታ ፤
ተሰርቶ ሲያበቃ አናስገባም የሚል ነገር አመጣችሁ ፤
አደራ እንዳትረሱ ፤ ፤
የክብሪት ዘመዶች፤
ዛሬም ማንደጃውን በገል ተሸክመን አለን በቤታችሁ ።
(( ጃ ኖ ))💚💛❤
@balmbaras
@getem
@getem
ከሙፍቲ ኡመር ቤት እሁድ ሆጤ ዝለቅ!!!"
በሸጋ ሙሃባ በኢልምና ኢማን የተሽሞነሞኑ ፤
በዚህ በኛ ሪጋ በላይኛው ገታ በታችኛው ቃሉ፤
ደባትይ ዛውያው፤
ዳና ከጎራው ዘንድ አደብና ኪታብ አንድ ላይ የቀሩ ፤
በዱኣ በቱፍታው በኑር በከራማ የተሽቀረቀሩ ፤
ጥላ ሚሆኑልን ፤
የሰው ዛፍ ዋርካዎች ዛሬም በዚህ አሉ ።
ትከጅል እንደሆን ፤
የበረካ ትንፋሽ ካሰኘህ እንደኔ ፤
እሁድ ሆጤ ዝለቅ ፤
ወሎን ያሽሩታል በሰውኛ ለዛ ሸህ ኡመር ቦረኔ ።
ሰውነት ምሰሶ ሰውነት ማገሩ ፤
ሰው መሆን መነሻው ሰው መሆን ድንበሩ ፤
ሆጤ ከሜዳው ላይ ፤
አርሂቡ ብሎሃል የሙፍቲ ኡመር ቤት ወሎ ገራገሩ ።
ሸጋው ቅዳሜ!!💚💛❤
@balmbaras
@getem
@getem
በሸጋ ሙሃባ በኢልምና ኢማን የተሽሞነሞኑ ፤
በዚህ በኛ ሪጋ በላይኛው ገታ በታችኛው ቃሉ፤
ደባትይ ዛውያው፤
ዳና ከጎራው ዘንድ አደብና ኪታብ አንድ ላይ የቀሩ ፤
በዱኣ በቱፍታው በኑር በከራማ የተሽቀረቀሩ ፤
ጥላ ሚሆኑልን ፤
የሰው ዛፍ ዋርካዎች ዛሬም በዚህ አሉ ።
ትከጅል እንደሆን ፤
የበረካ ትንፋሽ ካሰኘህ እንደኔ ፤
እሁድ ሆጤ ዝለቅ ፤
ወሎን ያሽሩታል በሰውኛ ለዛ ሸህ ኡመር ቦረኔ ።
ሰውነት ምሰሶ ሰውነት ማገሩ ፤
ሰው መሆን መነሻው ሰው መሆን ድንበሩ ፤
ሆጤ ከሜዳው ላይ ፤
አርሂቡ ብሎሃል የሙፍቲ ኡመር ቤት ወሎ ገራገሩ ።
ሸጋው ቅዳሜ!!💚💛❤
@balmbaras
@getem
@getem
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ጭንቄን ተን-ፈስ
""""""""""""""""""""
አሰይ ፈሳሁ
ኡፈይ ፈሳሁ
እንኳን ፈሳሁ
ነገር መውጫ ሲያጣ መዳኒት ነው ለካ ፈስ
የሀሳብ ምጥን ላረገዘ
ያደርገዋል ለካ ተንፈስ
ምስጢር ሰው እንዳይሰማ በትንሹ በቀስ በቀስ
-ፕስስስስስ-
(አልያም)
ከፈለገም ሰው ይስማው
በፈለገው ይተርጉመው
ከድምፁ ቢጎድል ከጠረኑ ላያመልጥ
እና እኔ ምንተዳዬ ቢጋለጥ- ባይጋለጥ
-ዘረጥጥጥጥ-
ታዘብኩሽ ቂጤን ላልላት
በሰው ፊት ብታዋርደኝ
ጭንቅላቴን ነው የታዘብኩት
በአፍ ማውራትን ቢያሳቅቀኝ
በፍራቻ መረብ ሰቅዞ
ሀሳብ ነፃነቴን ቢቀማኝ
እሱን ነው የታዘብኩት
ሌላውማ ምን አረገኝ?
***
ይሳቁ ያልገባቸው
የሆድ ነገር ጭንቀት ምሱ
ተገላብጦ መውጫ ሲያጣ
የሀሳብ መንገድ ግሳንግሱ
አፍ ተለጉሞ ሲያዝ
ባይናገር በምላሱ
ነገር በታች እያላሉ
እፎይ ማለት ግድ ነው ሳይሳቀቁ በፈሱ
የሆድ ባህር ጭቃው መንገድ
እንዲጣራ ድፍርስርሱ።
(በትንሹ በትንሹ)
ወይ ዘረጥ ----ይለይለት
ወይ ቱስስስስ--- በቀስ በቀስ
****
ሳቁ እናንተ ልፈሳ ነው
አይገባችሁም ነገሬ
ግን ሆዳችሁ ነገር አዝሏል
ሳያችሁ በትኩረት አንክሬ
እኔ ግን ልፈሳ ነው
አፍኖኛል ጭንቅ አጅሬ!!!
ከሳቃችሁ ግን-እሰይ ፈሳሁ
ኡፈይ ፈሳሁ
እንኳን ፈ
ሳ
ሁ።
አብርሃም
@Run_Viva_Run
@getem
@getem
@getem
""""""""""""""""""""
አሰይ ፈሳሁ
ኡፈይ ፈሳሁ
እንኳን ፈሳሁ
ነገር መውጫ ሲያጣ መዳኒት ነው ለካ ፈስ
የሀሳብ ምጥን ላረገዘ
ያደርገዋል ለካ ተንፈስ
ምስጢር ሰው እንዳይሰማ በትንሹ በቀስ በቀስ
-ፕስስስስስ-
(አልያም)
ከፈለገም ሰው ይስማው
በፈለገው ይተርጉመው
ከድምፁ ቢጎድል ከጠረኑ ላያመልጥ
እና እኔ ምንተዳዬ ቢጋለጥ- ባይጋለጥ
-ዘረጥጥጥጥ-
ታዘብኩሽ ቂጤን ላልላት
በሰው ፊት ብታዋርደኝ
ጭንቅላቴን ነው የታዘብኩት
በአፍ ማውራትን ቢያሳቅቀኝ
በፍራቻ መረብ ሰቅዞ
ሀሳብ ነፃነቴን ቢቀማኝ
እሱን ነው የታዘብኩት
ሌላውማ ምን አረገኝ?
***
ይሳቁ ያልገባቸው
የሆድ ነገር ጭንቀት ምሱ
ተገላብጦ መውጫ ሲያጣ
የሀሳብ መንገድ ግሳንግሱ
አፍ ተለጉሞ ሲያዝ
ባይናገር በምላሱ
ነገር በታች እያላሉ
እፎይ ማለት ግድ ነው ሳይሳቀቁ በፈሱ
የሆድ ባህር ጭቃው መንገድ
እንዲጣራ ድፍርስርሱ።
(በትንሹ በትንሹ)
ወይ ዘረጥ ----ይለይለት
ወይ ቱስስስስ--- በቀስ በቀስ
****
ሳቁ እናንተ ልፈሳ ነው
አይገባችሁም ነገሬ
ግን ሆዳችሁ ነገር አዝሏል
ሳያችሁ በትኩረት አንክሬ
እኔ ግን ልፈሳ ነው
አፍኖኛል ጭንቅ አጅሬ!!!
ከሳቃችሁ ግን-እሰይ ፈሳሁ
ኡፈይ ፈሳሁ
እንኳን ፈ
ሳ
ሁ።
አብርሃም
@Run_Viva_Run
@getem
@getem
@getem
እኔም ቁስል አለኝ
እኔም ቁስል አለኝ ያንተን የሚመስል
ልክ ያንተ ሲነካ የኔም የሚቆስል
እንደ ፈላ ውሀ፤
እንደ ሰደድ እሳት እጅግ የሚያቃጥል
እኔም ቁስል አለኝ ያንተን የሚመስል
አንተም እንደኔ ሰው ፤እኔም እንዳንተ ሰው
ማወቅ አልፈልግም ዘርህን ወደዛው
ወንድምህን ስታጣ አንጀትህ ሲቆስል
በዱላ ተተልትሎ ጀርባህም ቢቆስል
በእግዜር እምላለው ምንም ሳላስመስል
እኔም ቁስል አለኝ፤ ያንተን የሚመስል
@Leulewnetu
@getem
@getem
@getem
እኔም ቁስል አለኝ ያንተን የሚመስል
ልክ ያንተ ሲነካ የኔም የሚቆስል
እንደ ፈላ ውሀ፤
እንደ ሰደድ እሳት እጅግ የሚያቃጥል
እኔም ቁስል አለኝ ያንተን የሚመስል
አንተም እንደኔ ሰው ፤እኔም እንዳንተ ሰው
ማወቅ አልፈልግም ዘርህን ወደዛው
ወንድምህን ስታጣ አንጀትህ ሲቆስል
በዱላ ተተልትሎ ጀርባህም ቢቆስል
በእግዜር እምላለው ምንም ሳላስመስል
እኔም ቁስል አለኝ፤ ያንተን የሚመስል
@Leulewnetu
@getem
@getem
@getem
#ህልሜና ~ትርታሽ
፡
በሰመመን ጉዞ
እርቄ ከትሜ ውን አለሜን ትቼ
ከመዳፍሽ እቅፍ
በጡችሽ መሀል ልብሽ ላይ ተኝቼ
ለምን እንደው እንጃ
በትርታሽ ምናብ እቁነጠነጣለሁ
ከሀሳብሽ ሞገድ
ግራ የተጋቡ ቃላት አደምጣለሁ፡፡
፡
መሄድ ነው ውጥንሽ
ከ'ኔነቴ መራቅ መልመድ ከሌላ ሰው
ታዲያ በምን አቅሜ
ከ'ንቅልፌ ነቅቼ ህልምሽን ላፍረሰው?
፡
አልችልም ታውቂያለሽ
የማፍቀሬ ጣራ ነፃነት ነው ጥጉ
መሻትሽ ቢያመኝም
ከጉዞ አይገታሽም አንቺን መፈለጉ
፡
እናም በሃሳብሽ
እርቀሻል ብዬ አልነቃም ከ'ንቅልፌ
ነግቶ እስክትለይኝ
በእጆችሽ ላይ ልደር እቅፍሽ ነው ትርፌ፡፡
(ልብ አልባው ገጣሚ)
@getem
@Getem
@gebriel_19
፡
በሰመመን ጉዞ
እርቄ ከትሜ ውን አለሜን ትቼ
ከመዳፍሽ እቅፍ
በጡችሽ መሀል ልብሽ ላይ ተኝቼ
ለምን እንደው እንጃ
በትርታሽ ምናብ እቁነጠነጣለሁ
ከሀሳብሽ ሞገድ
ግራ የተጋቡ ቃላት አደምጣለሁ፡፡
፡
መሄድ ነው ውጥንሽ
ከ'ኔነቴ መራቅ መልመድ ከሌላ ሰው
ታዲያ በምን አቅሜ
ከ'ንቅልፌ ነቅቼ ህልምሽን ላፍረሰው?
፡
አልችልም ታውቂያለሽ
የማፍቀሬ ጣራ ነፃነት ነው ጥጉ
መሻትሽ ቢያመኝም
ከጉዞ አይገታሽም አንቺን መፈለጉ
፡
እናም በሃሳብሽ
እርቀሻል ብዬ አልነቃም ከ'ንቅልፌ
ነግቶ እስክትለይኝ
በእጆችሽ ላይ ልደር እቅፍሽ ነው ትርፌ፡፡
(ልብ አልባው ገጣሚ)
@getem
@Getem
@gebriel_19
©©ሳይፀልዩ ማደር☜☜
የተራበ ነብር ከሩቅ ተመልክታ
ሚዳቋዋ ፀለየች አውጣኝ አውጣኝ አለች ለፈጠራት ጌታ
ነብሩም ተርቦ ወደ አምላኩ ቀርቦ
አንጀቱ ከሆዱ እንደተጣበቀ ሚዳቋዋን አይቶ
ፈቅዶ እንዲሰጠው አምላኩን ጠየቀ
የሁለቱም አምላክ የሁላችን ሰሪ
ፀሎታቸውን ሠማቸው ፈጣሪ
አምላክም በድምፁ ሚዳቆዋን አላት
እሩጠሽ አምልጪ ከበረታ ጠላት
ነብሩንም አለው እሩጥ ተከተላት ምግብ አርገክ ብላት
ሚዳቆዋም ስትሮጥ ከነብሩ ለማምለጥ
ነብሩም ሢከተላት ሆዱን ሊሞላባት
ቋጥኙን ስትዘል እግሯ ተሥፈንጥሮ
ሆዱን ብትረግጠው የተኛ ከርከሮ
ከንቅልፉ ሲነቃ ልክ ሲደነብር
ጉሮሮውን ያዘው የፀለየው ነብር
አውጣኝ ያለው ወቶ አበላኝ ያለው በላ
ሳይፀልይ ያደረው ከርከሮ ተበላ
☞☞☞☞ በረከት በላይነህ☜☜☜☜
@lula_al_greeko
@getem
@getem
የተራበ ነብር ከሩቅ ተመልክታ
ሚዳቋዋ ፀለየች አውጣኝ አውጣኝ አለች ለፈጠራት ጌታ
ነብሩም ተርቦ ወደ አምላኩ ቀርቦ
አንጀቱ ከሆዱ እንደተጣበቀ ሚዳቋዋን አይቶ
ፈቅዶ እንዲሰጠው አምላኩን ጠየቀ
የሁለቱም አምላክ የሁላችን ሰሪ
ፀሎታቸውን ሠማቸው ፈጣሪ
አምላክም በድምፁ ሚዳቆዋን አላት
እሩጠሽ አምልጪ ከበረታ ጠላት
ነብሩንም አለው እሩጥ ተከተላት ምግብ አርገክ ብላት
ሚዳቆዋም ስትሮጥ ከነብሩ ለማምለጥ
ነብሩም ሢከተላት ሆዱን ሊሞላባት
ቋጥኙን ስትዘል እግሯ ተሥፈንጥሮ
ሆዱን ብትረግጠው የተኛ ከርከሮ
ከንቅልፉ ሲነቃ ልክ ሲደነብር
ጉሮሮውን ያዘው የፀለየው ነብር
አውጣኝ ያለው ወቶ አበላኝ ያለው በላ
ሳይፀልይ ያደረው ከርከሮ ተበላ
☞☞☞☞ በረከት በላይነህ☜☜☜☜
@lula_al_greeko
@getem
@getem