መርዝ ጠጣህ አሉኝ
በመርዝ የማይምቱ ፍጥረታት በሙላ
በውስኪና በጠጅ ባረቄ በጠላ
በካቲካላ መርዝ ሆዳቸው እየሞላ
መርዝ ጠጣህ አሉኝ
ጥዋት በማለዳ ከቤት እኩል ወጠን
እኩል ሌትር መጠን
እነሱ አስር ጣሳ ጠላቸውን ግተው
እነዛም በጠርሙስ አረቄ ተወግተው
እኔ ሁለት ጠርሙስ ፀበሉን ጠጥቼ
መርዝ ጠጣህ አሉኝ
በአፋቸው ገደሉኝ
በአልኰሉ ስካር በዞረ ናላቸው
በኮልታፋ አፋቸው
ትሞታለህ አሉኝ
ከቤት እኩል ወጠን
እኩል ሌትር መጠን
እኔ ከፀበሉ እነሱ ከጠላው በጠዋት ጠጥተን
መርዝ ጠጣህ አሉኝ መፅደቅን አልሜው
መቼስ እብዶች መሀል ጤነኛ ሰው ቢገኝ እብድ ነው ስያሜው
✍✍Dani yop
@getem
@getem
@gebriel_19
በመርዝ የማይምቱ ፍጥረታት በሙላ
በውስኪና በጠጅ ባረቄ በጠላ
በካቲካላ መርዝ ሆዳቸው እየሞላ
መርዝ ጠጣህ አሉኝ
ጥዋት በማለዳ ከቤት እኩል ወጠን
እኩል ሌትር መጠን
እነሱ አስር ጣሳ ጠላቸውን ግተው
እነዛም በጠርሙስ አረቄ ተወግተው
እኔ ሁለት ጠርሙስ ፀበሉን ጠጥቼ
መርዝ ጠጣህ አሉኝ
በአፋቸው ገደሉኝ
በአልኰሉ ስካር በዞረ ናላቸው
በኮልታፋ አፋቸው
ትሞታለህ አሉኝ
ከቤት እኩል ወጠን
እኩል ሌትር መጠን
እኔ ከፀበሉ እነሱ ከጠላው በጠዋት ጠጥተን
መርዝ ጠጣህ አሉኝ መፅደቅን አልሜው
መቼስ እብዶች መሀል ጤነኛ ሰው ቢገኝ እብድ ነው ስያሜው
✍✍Dani yop
@getem
@getem
@gebriel_19
🍺🍷ግብዣ አይናቅም
ይቺ የዉሃ ላስቲክ ወድቃ የቀጠጠች
ሳትጠጣ በፊት ሙሉ ዉሃ ነበረች
በቀን ሙሉነቷ አምራቿ ቢሸጣት
ቀኗ ደግሞ ሲጎል የተጠማ ገዝቷት
ጥጥት ቁርጥትት አርጎ
ጥሙን ቆርጦ ጣላት
እያለ በማዘን የሰከረ ጠጪ ጥሙን የቆረጠ
ከወደቁ ኮዳዎች አንድ እየመረጠ
አፍ አፏን እያየ አይዞሽ አይዞሽ ዳግም አትጠሚም
እኔ የማጠጣሽ እንደነሱ አይደለም
ከወደቀችበት ከፍ አድርጎ አንስቶ
የሱሪውን ዚፕ ዛጥ አድርጎ ከፍቶ
ቅራሪ አጠጣት ዳግም እንዳይጠማት
ካለችበት ነግቶ ቀትር ሲያገኛት
ምን ከንፈርሽ ቢያምር ሳሚ ምታገኚው
ውሃ ሽንት ሳይሆን ውሃ ስትይዢ ነው
እያለ ተርቶ
እሽግ ውሀ ገዝቶ
ዘወትር ይኖራል ጥም እስሩን ሲፈታ
ቀን ያጎደለውን እየሞላ ማታ
29/10/10
@getem
@getem
@gebriel_19
ይቺ የዉሃ ላስቲክ ወድቃ የቀጠጠች
ሳትጠጣ በፊት ሙሉ ዉሃ ነበረች
በቀን ሙሉነቷ አምራቿ ቢሸጣት
ቀኗ ደግሞ ሲጎል የተጠማ ገዝቷት
ጥጥት ቁርጥትት አርጎ
ጥሙን ቆርጦ ጣላት
እያለ በማዘን የሰከረ ጠጪ ጥሙን የቆረጠ
ከወደቁ ኮዳዎች አንድ እየመረጠ
አፍ አፏን እያየ አይዞሽ አይዞሽ ዳግም አትጠሚም
እኔ የማጠጣሽ እንደነሱ አይደለም
ከወደቀችበት ከፍ አድርጎ አንስቶ
የሱሪውን ዚፕ ዛጥ አድርጎ ከፍቶ
ቅራሪ አጠጣት ዳግም እንዳይጠማት
ካለችበት ነግቶ ቀትር ሲያገኛት
ምን ከንፈርሽ ቢያምር ሳሚ ምታገኚው
ውሃ ሽንት ሳይሆን ውሃ ስትይዢ ነው
እያለ ተርቶ
እሽግ ውሀ ገዝቶ
ዘወትር ይኖራል ጥም እስሩን ሲፈታ
ቀን ያጎደለውን እየሞላ ማታ
29/10/10
@getem
@getem
@gebriel_19
እ-ን-ድ-ረ-ሳ-ሽ(ልዑል ሀይሌ)
.
እ-ን-ድ-ረ-ሳ-ሽ
መንገድ ጥረጊልኝ
ይህቺን ብቻ አርጊልኝ!
.
ስምሽን እያነሱ
እንዳያስታውሱኝ
በሞተው ትዝታ
እንዳይቀሰቅሱኝ
ያንቺ አለመሆኔን
ዛሬ እንዳሳያቸው
ጨረቃን ፀሐይን
ምድር አውርጂያቸው
ውቅያኖስ ባህሩን
ሰማይ ስቀያቸው
.
እ-ን-ድ-ረ-ሳ-ሽ
የረገጥነው አስፋልት
የሄድንበት መንገድ
ያ ያለፈው ፍቅር
ያ ያለፈው መውደድ
ፍፁም ውሸት ብዬ
እንድሸመጥጠው
ተፈጥሮን አዛቢ
መውደዴን እንድተው
.
እ-ን-ድ-ረ-ሳ-ሽ
ገደሉን ሙዪና
ተራራውን ናጂው
ደመናን አውርደሽ
አፈሩን ውሰጂው
የረገጥሽው መሬት
አምሮ እንድታይበት
በአበባው ፋንታ
ሳማ ትከይበት
.
እ-ን-ድ-ረ-ሳ-ሽ
ያ ሁላ ቃል ኪዳን
ተበትኖ እንዲቀር
አይጥ ሀይቅ ትዋኝ
ዓሳ ሰማይ ይብረር
በህይወት ባሉት ምትክ
ሙታኖች ይነሱ
ነገስታት ይውረዱ
ባርያዎች ይንገሱ
.
ይሄን ካረግሽልኝ
መውደዴን ይቅርና
መኖር አቆማለሁ
በመኖር ብረሳሽ
ባለመኖርም ውስጥ
አስታውስሻለሁ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
.
እ-ን-ድ-ረ-ሳ-ሽ
መንገድ ጥረጊልኝ
ይህቺን ብቻ አርጊልኝ!
.
ስምሽን እያነሱ
እንዳያስታውሱኝ
በሞተው ትዝታ
እንዳይቀሰቅሱኝ
ያንቺ አለመሆኔን
ዛሬ እንዳሳያቸው
ጨረቃን ፀሐይን
ምድር አውርጂያቸው
ውቅያኖስ ባህሩን
ሰማይ ስቀያቸው
.
እ-ን-ድ-ረ-ሳ-ሽ
የረገጥነው አስፋልት
የሄድንበት መንገድ
ያ ያለፈው ፍቅር
ያ ያለፈው መውደድ
ፍፁም ውሸት ብዬ
እንድሸመጥጠው
ተፈጥሮን አዛቢ
መውደዴን እንድተው
.
እ-ን-ድ-ረ-ሳ-ሽ
ገደሉን ሙዪና
ተራራውን ናጂው
ደመናን አውርደሽ
አፈሩን ውሰጂው
የረገጥሽው መሬት
አምሮ እንድታይበት
በአበባው ፋንታ
ሳማ ትከይበት
.
እ-ን-ድ-ረ-ሳ-ሽ
ያ ሁላ ቃል ኪዳን
ተበትኖ እንዲቀር
አይጥ ሀይቅ ትዋኝ
ዓሳ ሰማይ ይብረር
በህይወት ባሉት ምትክ
ሙታኖች ይነሱ
ነገስታት ይውረዱ
ባርያዎች ይንገሱ
.
ይሄን ካረግሽልኝ
መውደዴን ይቅርና
መኖር አቆማለሁ
በመኖር ብረሳሽ
ባለመኖርም ውስጥ
አስታውስሻለሁ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
ድልዙ ደብዳቤ!
'''''''፠'''''''፠'''''''
የፃፍኩልሽ ቅኔ አልኮል ሲሎኝ በርታ
ረጅሙ ጽሁፍ ብዕር ጠፍቶ ማታ
ሰርዤ ደልዤ በዱልዱሙ እርሳሴ
አይገርምም መማሌ ቆሜ "በስላሴ"?
ጠፍቶብኝ ጸጸቱ ጭፈራ ሳልወጣ
"ወለል" ብዬ ጠራው አስተናጋጅ ሳጣ!
መልዕክት እስቲ አድርስ እዛጋ ላለችው
መጠጡን ስትቀዳ ዐይን ዐይኔን እያየችው'
በፍቅሯ ጣለችኝ ወይ ወገብ መቅጠኑ
ጨፈር ልል ስነሳ ቢዘጋ ዘፈኑ!
እሷም ትወጣለች~
እሷም ትሔዳለች~
እሷ የምታውቀው ማየት ሆኖ 'ታማኝ'?
ያስተናጋጅ ፍቅር መች ይዞ ገደለኝ!
@getem
@getem
@Johny_Debx
'''''''፠'''''''፠'''''''
የፃፍኩልሽ ቅኔ አልኮል ሲሎኝ በርታ
ረጅሙ ጽሁፍ ብዕር ጠፍቶ ማታ
ሰርዤ ደልዤ በዱልዱሙ እርሳሴ
አይገርምም መማሌ ቆሜ "በስላሴ"?
ጠፍቶብኝ ጸጸቱ ጭፈራ ሳልወጣ
"ወለል" ብዬ ጠራው አስተናጋጅ ሳጣ!
መልዕክት እስቲ አድርስ እዛጋ ላለችው
መጠጡን ስትቀዳ ዐይን ዐይኔን እያየችው'
በፍቅሯ ጣለችኝ ወይ ወገብ መቅጠኑ
ጨፈር ልል ስነሳ ቢዘጋ ዘፈኑ!
እሷም ትወጣለች~
እሷም ትሔዳለች~
እሷ የምታውቀው ማየት ሆኖ 'ታማኝ'?
ያስተናጋጅ ፍቅር መች ይዞ ገደለኝ!
@getem
@getem
@Johny_Debx
Forwarded from SPACE COMPUTER
መጋቢት 24
የጥበብ ምሽት ከአንጋፋ አርቲስቶች ጋር
🔰ዕንቁላል ፋብሪካ
ከእምቢልታ ሆቴል ከፍ ብሎ በሚገኘው ገነት መናፈሻ እንድቅትዮን
(የብርሃን ዕለት) በወሩ የመጨረሻ ማክሰኞ መጋቢት ፳፬-፳፻፲፩
ዓ.ም. የጥበብ ድግሱን አሰናድቶ ይጠብቆታል.
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
@getem
የጥበብ ምሽት ከአንጋፋ አርቲስቶች ጋር
🔰ዕንቁላል ፋብሪካ
ከእምቢልታ ሆቴል ከፍ ብሎ በሚገኘው ገነት መናፈሻ እንድቅትዮን
(የብርሃን ዕለት) በወሩ የመጨረሻ ማክሰኞ መጋቢት ፳፬-፳፻፲፩
ዓ.ም. የጥበብ ድግሱን አሰናድቶ ይጠብቆታል.
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
@getem
የምሳር እንጨት
የምሳሩ እንጨት መቁርጫ ብረት የተሸከመ
በምሳር ተቆርጦ ለመቁረጫነት የተሸለመ
በመቆረጡ ተናዶ ከቆራጮቹ የተዛመደ
እንጨት ሆኖ ተፈጥሮ እንጨት የጎመደ
በመቆረጥ ብሶት ቆራጭ ሆኖ ያረፈ
በ ለም’ን ተነካው እብሪት ወገኑን ያረገፈ
ምሳርስ እንጨት ነው የቅርንጫፍ ስባሪ
የሞትን መርዝ በአናቱ ትሸክሞ ዟሪ
ግና እንጨቱማ ከህያዋን ነው ፍጥረቱ
ብረቱን ሲሸክም ነው የጀመረ ገዳይነቱ
ባይገባው ነው እንጂ የተፈጠረበት ምሥጢር
አፈርነቱ ነበር በአፈር ያደገ ሲሞትም ወ’ዳፈር
ሲኖር ለሰው እስትንፋስ ሲሞት የወገኖቹ እንገር
አፈርነቱ ነበር ሞቶ የሚያኖረው ለሌላው በመኖር
ልንገርህ የምሳር እንጨት ሆይ እህ ብለህ ስማ
በመሰበርህ ተናደህ ከብረት ጉያ መሽገህ ብታደማ
ብታቆስል ብትቆርጥ የወገንህን ህልም ብትቀማ
መውለቅህ አይቀርም አረጀህ ተሰነጠቅህ ብሎ
ቆራጩ ብረቱ ላንተም ይቆራርጥሀል ጫፉን አስሎ
መጨረሻህም አመድነት ነው በእሳት ተቃጥሎ
እናም ሀገሬ ለምለም ሆና ለማማር እኛን ብታበቅል
በጉያዋ ተሸክማ ከአውሎ ነፋስና እሳት ብትከልል
እንደምሳሩ እንጨት ገዳይነትን ከአናታችን ተሸክመን
ወገናችንን ምናደማ ምናቆስል በብረቱ ተሸጉጠን
ተፈጥሯችን ከህያዋን ግብራችን ከምሳር እንጨት
እድገታችን ከንጹሐን ፍፃሜያችን ከገዳይነት
…
፲፯/፯/፳፻፲፩ ዓ.ም
፨አክሱማዊት፨
@getem
@getem
@gebriel_19
የምሳሩ እንጨት መቁርጫ ብረት የተሸከመ
በምሳር ተቆርጦ ለመቁረጫነት የተሸለመ
በመቆረጡ ተናዶ ከቆራጮቹ የተዛመደ
እንጨት ሆኖ ተፈጥሮ እንጨት የጎመደ
በመቆረጥ ብሶት ቆራጭ ሆኖ ያረፈ
በ ለም’ን ተነካው እብሪት ወገኑን ያረገፈ
ምሳርስ እንጨት ነው የቅርንጫፍ ስባሪ
የሞትን መርዝ በአናቱ ትሸክሞ ዟሪ
ግና እንጨቱማ ከህያዋን ነው ፍጥረቱ
ብረቱን ሲሸክም ነው የጀመረ ገዳይነቱ
ባይገባው ነው እንጂ የተፈጠረበት ምሥጢር
አፈርነቱ ነበር በአፈር ያደገ ሲሞትም ወ’ዳፈር
ሲኖር ለሰው እስትንፋስ ሲሞት የወገኖቹ እንገር
አፈርነቱ ነበር ሞቶ የሚያኖረው ለሌላው በመኖር
ልንገርህ የምሳር እንጨት ሆይ እህ ብለህ ስማ
በመሰበርህ ተናደህ ከብረት ጉያ መሽገህ ብታደማ
ብታቆስል ብትቆርጥ የወገንህን ህልም ብትቀማ
መውለቅህ አይቀርም አረጀህ ተሰነጠቅህ ብሎ
ቆራጩ ብረቱ ላንተም ይቆራርጥሀል ጫፉን አስሎ
መጨረሻህም አመድነት ነው በእሳት ተቃጥሎ
እናም ሀገሬ ለምለም ሆና ለማማር እኛን ብታበቅል
በጉያዋ ተሸክማ ከአውሎ ነፋስና እሳት ብትከልል
እንደምሳሩ እንጨት ገዳይነትን ከአናታችን ተሸክመን
ወገናችንን ምናደማ ምናቆስል በብረቱ ተሸጉጠን
ተፈጥሯችን ከህያዋን ግብራችን ከምሳር እንጨት
እድገታችን ከንጹሐን ፍፃሜያችን ከገዳይነት
…
፲፯/፯/፳፻፲፩ ዓ.ም
፨አክሱማዊት፨
@getem
@getem
@gebriel_19
#አትረፍ_ቢለኝ
ገርሞኝ ሳያበቃ
የአንድ እሷ ናፍቆት የሄደች ለት ርቃኝ
ጭራሽ ይባስ ብላ
ጉዴን አባሰችው እስከባሏ ናፍቃኝ
✍ኢዛና መስፍን
@getem
@getem
@lula_al_greeko
ገርሞኝ ሳያበቃ
የአንድ እሷ ናፍቆት የሄደች ለት ርቃኝ
ጭራሽ ይባስ ብላ
ጉዴን አባሰችው እስከባሏ ናፍቃኝ
✍ኢዛና መስፍን
@getem
@getem
@lula_al_greeko
መርዝ ጠጣህ አሉኝ
በመርዝ የማይምቱ ፍጥረታት በሙላ
በውስኪና በጠጅ ባረቄ በጠላ
በካቲካላ መርዝ ሆዳቸው እየሞላ
መርዝ ጠጣህ አሉኝ
ጥዋት በማለዳ ከቤት እኩል ወጠን
እኩል ሌትር መጠን
እነሱ አስር ጣሳ ጠላቸውን ግተው
እነዛም በጠርሙስ አረቄ ተወግተው
እኔ ሁለት ጠርሙስ ፀበሉን ጠጥቼ
መርዝ ጠጣህ አሉኝ
በአፋቸው ገደሉኝ
በአልኰሉ ስካር በዞረ ናላቸው
በኮልታፋ አፋቸው
ትሞታለህ አሉኝ
ከቤት እኩል ወጠን
እኩል ሌትር መጠን
እኔ ከፀበሉ እነሱ ከጠላው በጠዋት ጠጥተን
መርዝ ጠጣህ አሉኝ መፅደቅን አልሜው
መቼስ እብዶች መሀል ጤነኛ ሰው ቢገኝ እብድ ነው ስያሜው
✍✍Dani yop
@getem
@getem
@gebriel_19
በመርዝ የማይምቱ ፍጥረታት በሙላ
በውስኪና በጠጅ ባረቄ በጠላ
በካቲካላ መርዝ ሆዳቸው እየሞላ
መርዝ ጠጣህ አሉኝ
ጥዋት በማለዳ ከቤት እኩል ወጠን
እኩል ሌትር መጠን
እነሱ አስር ጣሳ ጠላቸውን ግተው
እነዛም በጠርሙስ አረቄ ተወግተው
እኔ ሁለት ጠርሙስ ፀበሉን ጠጥቼ
መርዝ ጠጣህ አሉኝ
በአፋቸው ገደሉኝ
በአልኰሉ ስካር በዞረ ናላቸው
በኮልታፋ አፋቸው
ትሞታለህ አሉኝ
ከቤት እኩል ወጠን
እኩል ሌትር መጠን
እኔ ከፀበሉ እነሱ ከጠላው በጠዋት ጠጥተን
መርዝ ጠጣህ አሉኝ መፅደቅን አልሜው
መቼስ እብዶች መሀል ጤነኛ ሰው ቢገኝ እብድ ነው ስያሜው
✍✍Dani yop
@getem
@getem
@gebriel_19
Forwarded from Melkam74 Digital Magazine
Melkam74 ቅፅ ፩ ቁጥር 4.pdf
4.5 MB
📠 Melkam74 ቅፅ 1 ቁጥር 4
💰 ፓኬጅ ከገዙ በብር 1.27 ብቻ 💰
💰 ፓኬጅ ከገዙ በብር 1.27 ብቻ 💰
ሃሳብና ቁስል
✍ ብሩኬ(የወይን ፍሬ)
_____________
አንድ ስግር ሃሳብ ይወዘዉዘኛል
ከአፈር ከድንጋዩ ጥሎ ያዛምዳል
ከአንቺነትሽ ጥርጊያ ወስዶ ይጥለኛል
መወዝወዝ ከንቱ ነዉ አቋመ ቢስ መሆን
ከጥላ የረገፉ ጥላ አልቦነት ማግነን
ከመጠረግ ሳንኳ ቀልብ አጥቶ መማሰን
ዲዳ ነዉ ሃሳቤ መናገር አይሻ
ቀዉላላ ቅዠቴን ወሮታል ጥቀርሻ
ሌላ ስግር ሃሳብ ከፈረስ ላይ ጣለኝ
ኮርቻ የሌለዉ እኔነቱ ነዳኝ
ቼ ቼ ቼ ………ቼ ፈረሴ
ልኑር ለኔነቴ ልኑር ለመንፈሴ
ብሎ ያሽሟጥጣል መከረኛዉ ነብሴ
ሌላ ስግር ሃሳብ ከታንኳ ላይ ጣለኝ
ጨዋማ ዉሃ ላይ ትዝታ አተከነኝ
የልጅነት ዘመን ኩኩሉ ኩኩሉ
የአፍላነት ፍቅር ብልቃጥ መኮልኮሉ
የለጋነት እድሜ በታንኳ ሲንጋሸሽ
ያላረጀች ጀንበር ጥላኝ ከኔ ስትሸሽ
እሱንም አያለሁ በመንታ ትዝታ እብሰከሰካለሁ
የኗሪዎች አስቀኒ አዉራ ሟች ሆኛለሁ
ሌላ ስግር ሃሳብ ጨረቃ ላይ ጣለኝ
ለብዙ አፍቃሪዎች ትዕይንት አደረገኝ
ከትዝታ በፊት ትዝታ ሳይመጣ
እንዲህ እንደ ዛሬ ፍቅር ሳይቀናጣ
ጨረቃ እያየችን ከንፈር ተሳሳምን
ኮከብ እየቆጠርን ኮከብ ተሰጣጠን
የአንድ ምሽት ፍቅር ዘመን አሻገረን
የቅናቱ ንጋት ዳግም አካካደን
ትዝታ ፈረሱን ልጓሙን ያዝኩና
ያለያየንን ጀንበር ልርገም እንደገና
እኔ ጨረቃ ላይ አንቺ ከመሬቱ
ከሌላ ወንድ ጋር ከንፈር መጓተቱ
ኮከብ ስትቆጥሩ ስትከፋፈሉ
የአንድ ምሽት ግምጫ ፍቅር ነዉ አትበሉ
ያ ስግር ሃሳቤ ብሽቅጥቅጥ አለና
ፈረሱም ከገደል ታንኳዉም ሰመጠና
እኔም ከጨረቃ ተፈነገልኩና
ስግሩን ሃሳቤን ሻርኩት ቆሰልኩና
ከበፊቱ በፊት ሃዘን ከሰዉ ቢበልጥ
መዝለል ነዉ ትዝታን ቁስሉን ባለመላጥ።
መጋቢት 22-2011ዓ.ም
እሁድ 10:30 d/b
@getem
@getem
@gebriel_19
✍ ብሩኬ(የወይን ፍሬ)
_____________
አንድ ስግር ሃሳብ ይወዘዉዘኛል
ከአፈር ከድንጋዩ ጥሎ ያዛምዳል
ከአንቺነትሽ ጥርጊያ ወስዶ ይጥለኛል
መወዝወዝ ከንቱ ነዉ አቋመ ቢስ መሆን
ከጥላ የረገፉ ጥላ አልቦነት ማግነን
ከመጠረግ ሳንኳ ቀልብ አጥቶ መማሰን
ዲዳ ነዉ ሃሳቤ መናገር አይሻ
ቀዉላላ ቅዠቴን ወሮታል ጥቀርሻ
ሌላ ስግር ሃሳብ ከፈረስ ላይ ጣለኝ
ኮርቻ የሌለዉ እኔነቱ ነዳኝ
ቼ ቼ ቼ ………ቼ ፈረሴ
ልኑር ለኔነቴ ልኑር ለመንፈሴ
ብሎ ያሽሟጥጣል መከረኛዉ ነብሴ
ሌላ ስግር ሃሳብ ከታንኳ ላይ ጣለኝ
ጨዋማ ዉሃ ላይ ትዝታ አተከነኝ
የልጅነት ዘመን ኩኩሉ ኩኩሉ
የአፍላነት ፍቅር ብልቃጥ መኮልኮሉ
የለጋነት እድሜ በታንኳ ሲንጋሸሽ
ያላረጀች ጀንበር ጥላኝ ከኔ ስትሸሽ
እሱንም አያለሁ በመንታ ትዝታ እብሰከሰካለሁ
የኗሪዎች አስቀኒ አዉራ ሟች ሆኛለሁ
ሌላ ስግር ሃሳብ ጨረቃ ላይ ጣለኝ
ለብዙ አፍቃሪዎች ትዕይንት አደረገኝ
ከትዝታ በፊት ትዝታ ሳይመጣ
እንዲህ እንደ ዛሬ ፍቅር ሳይቀናጣ
ጨረቃ እያየችን ከንፈር ተሳሳምን
ኮከብ እየቆጠርን ኮከብ ተሰጣጠን
የአንድ ምሽት ፍቅር ዘመን አሻገረን
የቅናቱ ንጋት ዳግም አካካደን
ትዝታ ፈረሱን ልጓሙን ያዝኩና
ያለያየንን ጀንበር ልርገም እንደገና
እኔ ጨረቃ ላይ አንቺ ከመሬቱ
ከሌላ ወንድ ጋር ከንፈር መጓተቱ
ኮከብ ስትቆጥሩ ስትከፋፈሉ
የአንድ ምሽት ግምጫ ፍቅር ነዉ አትበሉ
ያ ስግር ሃሳቤ ብሽቅጥቅጥ አለና
ፈረሱም ከገደል ታንኳዉም ሰመጠና
እኔም ከጨረቃ ተፈነገልኩና
ስግሩን ሃሳቤን ሻርኩት ቆሰልኩና
ከበፊቱ በፊት ሃዘን ከሰዉ ቢበልጥ
መዝለል ነዉ ትዝታን ቁስሉን ባለመላጥ።
መጋቢት 22-2011ዓ.ም
እሁድ 10:30 d/b
@getem
@getem
@gebriel_19
አንድ ሎሚ ግጥም
።።።።።።።።።።።።።።
አልገባኝም ነው ያልሽው?
"ሀምሳ ሎሚ ለመልቀም ሀምሳ ዛፍ አይተከልም
ሀምሳ እግር ወይን ተክሎ አንድ ሎሚ ማግኘት አይቀልም!"
ይኼ ምኑ ይከብዳል
"አንዴ የተከልሽው ሎሚ ዛፍ እልፍ ሎሚዎች ይወልዳል!"
ይኼ ምኑ ይከብዳል?
፣
ሎሚ እኮ መድኃኒት ነው፣ ምንሽን ነበር ያመመሽ?
ሆምጣጤ ሻጩ በሙሉ ልጣጭ አብልቶ ያከመሽ?
የተከልሽው ሀምሳ እግር ወይን፣ ምኑ ላይ ምን አበቀለ?
ሀምሳ ዛፍ የያዘው መሬት፣ ለሎሚ ምነው ቀለለ?
ጥያቄ በዛብሽ መሰል¡
ከተከልሽው ሀምሳ እግር ወይን፣ ስንቱን እንደጠጣሽ ባላውቅም
(ቅርጫቱን ወደሻል አሉ)
የያዝሽው የሎሚ ቅርጫት፣ እመኚኝ ከሎሚ አይልቅም።
እንደው በራሳችን ሞት
በመቶ ሚቆጠር ሎሚ የሚይዝ ቅርጫት ታቅፎ
ተሸካሚውን ባፍጢሙ ድንጋይ ቢደፋው አንቅፎ
ከተሸከመው ቅርጫትና ቅርጫቱ ከያዘው ሎሚ
የቱ ነው ፈውስ የሚሆነው?
"..." ይበቃል መልስ አትድገሚ።
፣
የሰማይን ደጃፍ አንኳኪ ያለምም ጫፍ ድረስ ሂጂ
ስለዋጋ ምንም አይከብርም ስለያዘው ዐላማ እንጂ።
ግጥም ርካሽ ነው አልሽ???
ጣትሽን ያንሻፈፉቱ ሙጃሌውና ሰንኮፉ
አልቅሰው ደም እየረጩ ተነቅለው የተራገፉ
ንገሪኝ በምን ነበረ
"በሰላሳ ሳንቲም መርፌ!"
ካንቺ ጋ ከምከራከር ግጥሜን ብጽፍስ አርፌ።
ቆይ አንዴ...
፣
ሎሚውን ስለመርከሱ ስለዋጋው እያቃለሉ
በየማሳቸው መካከል አብዝተው ወይን የተከሉ
የሚሸከሙት ሸክማቸው ባዶ ቅርጫት ነው አሉ።
(መቼም አንቺም አታጪው
የሸክም ትርጉም ለጠፋው ሸክም ሸክምን ይወልዳል
በቃ ሀቁን አፍርጪው
ባዶነት ከባዶ ስም ጋር ይቀላል ወይስ ይከብዳል?)
ሺህ ጊዜ ወይን ቢወደድ ሺህ ጊዜ ቢናፈቅ ስካር
"ወይን ለልብ አይሆንም" የሚልሽ ታጫለሽ መካር?
፣
ግጥም ርካሽ ነው አልሽ???
ዘመኑ የሚሉበት ነው ሁሉ ይባላል በቀላል
ከፍ የሚል ከክብሩ ወርዶ ዝቅ የሚል ላይ ይሰቀላል።
በሽታው ከቶ ላልገባው ፈልጎ ላልደረሰበት
ህመሙን ላራከሰ ነው መድኃኒት የሚረክስበት።
በቅድሚ ህመምሽን ለዪ!
ከዛ ግን አክብረሽ ያዢው እንደ ወይን እንደ አበባው
የመድኃኒቱ ዋጋ ላይ ያኔ ነው የምንግባባው።
አሁንስ አልገባሽም ወይ? ነው ወይስ ሽንፈት ያስፈራል?
አየሽው የግጥም አቅም
በስካር ሳይወላከፍ አደባባይ ላይ ይደፍራል።
፣
ወይንሽን የተካፈለሽ ከስካር ጦስ ስላልዳነ
ማንም ሰው ደፍሮ አልነገረሽ ቅርጫትሽ ባዶ እንደሆነ።
@getem
@getem
@paappii
Yedil tizazu
።።።።።።።።።።።።።።
አልገባኝም ነው ያልሽው?
"ሀምሳ ሎሚ ለመልቀም ሀምሳ ዛፍ አይተከልም
ሀምሳ እግር ወይን ተክሎ አንድ ሎሚ ማግኘት አይቀልም!"
ይኼ ምኑ ይከብዳል
"አንዴ የተከልሽው ሎሚ ዛፍ እልፍ ሎሚዎች ይወልዳል!"
ይኼ ምኑ ይከብዳል?
፣
ሎሚ እኮ መድኃኒት ነው፣ ምንሽን ነበር ያመመሽ?
ሆምጣጤ ሻጩ በሙሉ ልጣጭ አብልቶ ያከመሽ?
የተከልሽው ሀምሳ እግር ወይን፣ ምኑ ላይ ምን አበቀለ?
ሀምሳ ዛፍ የያዘው መሬት፣ ለሎሚ ምነው ቀለለ?
ጥያቄ በዛብሽ መሰል¡
ከተከልሽው ሀምሳ እግር ወይን፣ ስንቱን እንደጠጣሽ ባላውቅም
(ቅርጫቱን ወደሻል አሉ)
የያዝሽው የሎሚ ቅርጫት፣ እመኚኝ ከሎሚ አይልቅም።
እንደው በራሳችን ሞት
በመቶ ሚቆጠር ሎሚ የሚይዝ ቅርጫት ታቅፎ
ተሸካሚውን ባፍጢሙ ድንጋይ ቢደፋው አንቅፎ
ከተሸከመው ቅርጫትና ቅርጫቱ ከያዘው ሎሚ
የቱ ነው ፈውስ የሚሆነው?
"..." ይበቃል መልስ አትድገሚ።
፣
የሰማይን ደጃፍ አንኳኪ ያለምም ጫፍ ድረስ ሂጂ
ስለዋጋ ምንም አይከብርም ስለያዘው ዐላማ እንጂ።
ግጥም ርካሽ ነው አልሽ???
ጣትሽን ያንሻፈፉቱ ሙጃሌውና ሰንኮፉ
አልቅሰው ደም እየረጩ ተነቅለው የተራገፉ
ንገሪኝ በምን ነበረ
"በሰላሳ ሳንቲም መርፌ!"
ካንቺ ጋ ከምከራከር ግጥሜን ብጽፍስ አርፌ።
ቆይ አንዴ...
፣
ሎሚውን ስለመርከሱ ስለዋጋው እያቃለሉ
በየማሳቸው መካከል አብዝተው ወይን የተከሉ
የሚሸከሙት ሸክማቸው ባዶ ቅርጫት ነው አሉ።
(መቼም አንቺም አታጪው
የሸክም ትርጉም ለጠፋው ሸክም ሸክምን ይወልዳል
በቃ ሀቁን አፍርጪው
ባዶነት ከባዶ ስም ጋር ይቀላል ወይስ ይከብዳል?)
ሺህ ጊዜ ወይን ቢወደድ ሺህ ጊዜ ቢናፈቅ ስካር
"ወይን ለልብ አይሆንም" የሚልሽ ታጫለሽ መካር?
፣
ግጥም ርካሽ ነው አልሽ???
ዘመኑ የሚሉበት ነው ሁሉ ይባላል በቀላል
ከፍ የሚል ከክብሩ ወርዶ ዝቅ የሚል ላይ ይሰቀላል።
በሽታው ከቶ ላልገባው ፈልጎ ላልደረሰበት
ህመሙን ላራከሰ ነው መድኃኒት የሚረክስበት።
በቅድሚ ህመምሽን ለዪ!
ከዛ ግን አክብረሽ ያዢው እንደ ወይን እንደ አበባው
የመድኃኒቱ ዋጋ ላይ ያኔ ነው የምንግባባው።
አሁንስ አልገባሽም ወይ? ነው ወይስ ሽንፈት ያስፈራል?
አየሽው የግጥም አቅም
በስካር ሳይወላከፍ አደባባይ ላይ ይደፍራል።
፣
ወይንሽን የተካፈለሽ ከስካር ጦስ ስላልዳነ
ማንም ሰው ደፍሮ አልነገረሽ ቅርጫትሽ ባዶ እንደሆነ።
@getem
@getem
@paappii
Yedil tizazu
Fight autism✔ home teacher for autistic children በኦቲዝም ለታመሙ ልጆች ብቻ:
በኦቲዝም ለተጠቃ/ች ልጅ ድጋፍ፣ ክትትል እና የቤት ዉስጥ ትምህርት ይፈልጋሉ?
ኦቲዝም ምንድን ነው?
ኦቲዝም በህፃናት/ልጆች የነርቭና የእድገት ሂደት ላይ ውስንነትን በማስከተል ልጆቹ ከሰዉ ጋር የሚኖራቸውን ግንኙነትና የመግባባት ክህሎት እንዲሁም የመረዳት ችሎታ የሚጎዳ/የሚቀንስ ህመም ነዉ።
ኦቲዝም ለሁለንተናዊ የህፃናት/የልጆች እድገት አስፈላጊ የሆኑ ማህበራዊ ግንኙነቶችን እንዲሁም የልጆቹን ግለሰባዊ ባህሪያቶች ይጎዳል።
መፍትሄው ምንድን ነው?
ምንም እንኳ እስከ አሁን ድረስ ኦቲዝምን ፈፅሞ ሊያድን የሚችል ህክምና ባይኖርም ልጅዎ ላይ የሚታዩትን የህመም ምልክቶች በመቀነስ የልጅዎን እድገትና የትምህርት አቀባበል ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል።
ይህንንም የልጁ/ቷን ማህበረዊ፣ የመግባባት ክህሎትና ባህሪ ላይ አትኩረው በሚሰሩ ባለሙያዎች በሚተገበሩ ተከታታይ እና የተዋጣላቸዉ መርሃግብሮች ማሳካት ይቻላል።
ከምንሰጣቸው ድጋፍ፣ ክትትል እና ትምህርት መካከል፦
የመግባባት ክህሎት፦ የኦቲዝም ተጠቂ ልጅን የማህበራዊ እና የቋንቋ ችግሮች ላይ በመሥራት የመግባባት ክህሎትን ማጎልበት።
የባህሪ ለዉጥ፡- የኦቲዝም ተጠቂ ልጅ ሊኖሩት/ዋት የሚችሉትን አስቸጋሪ ባህሪያትን በመቀነስ እና መልካም ሥነምግባርን በማስረፅ ተፈላጊ የባህሪ ለዉጥ ማምጣት።
ትምህርት፡- ኦቲዝም ላለባቸዉ ህፃናት በጥናት በተቀረፀ የትምህርት መርኃግብር እና ለዚሁ አላማ በተዘጋጁ የትምህርት መርጃ መሳርያዎች በመታገዝ የቤት ውስጥ ተጨማሪ ትምህርት በመስጠት የልጆቹን የትምህርት አቀባበል ማሳደግ።
ቤተሰብ ተኮር ድጋፍ፡- ወላጆችና ሌሎች የቤተሰቡ አባላት የኦቲዝም ተጠቂ ልጅን የመግባባት ክህሎት እና ችግሮችን የመፍታት ችሎታ ለማዳበር በምን መልኩ መቅረብ እና አብረዉ መጫወት እንዳላባቸው ማስተማር።
ለበለጠ መረጃ በሚከተሉት የስልክ ቁጥሮች ይደውሉ፦
0913011134
0910916602
@wegoch
@gebriel_19
በኦቲዝም ለተጠቃ/ች ልጅ ድጋፍ፣ ክትትል እና የቤት ዉስጥ ትምህርት ይፈልጋሉ?
ኦቲዝም ምንድን ነው?
ኦቲዝም በህፃናት/ልጆች የነርቭና የእድገት ሂደት ላይ ውስንነትን በማስከተል ልጆቹ ከሰዉ ጋር የሚኖራቸውን ግንኙነትና የመግባባት ክህሎት እንዲሁም የመረዳት ችሎታ የሚጎዳ/የሚቀንስ ህመም ነዉ።
ኦቲዝም ለሁለንተናዊ የህፃናት/የልጆች እድገት አስፈላጊ የሆኑ ማህበራዊ ግንኙነቶችን እንዲሁም የልጆቹን ግለሰባዊ ባህሪያቶች ይጎዳል።
መፍትሄው ምንድን ነው?
ምንም እንኳ እስከ አሁን ድረስ ኦቲዝምን ፈፅሞ ሊያድን የሚችል ህክምና ባይኖርም ልጅዎ ላይ የሚታዩትን የህመም ምልክቶች በመቀነስ የልጅዎን እድገትና የትምህርት አቀባበል ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል።
ይህንንም የልጁ/ቷን ማህበረዊ፣ የመግባባት ክህሎትና ባህሪ ላይ አትኩረው በሚሰሩ ባለሙያዎች በሚተገበሩ ተከታታይ እና የተዋጣላቸዉ መርሃግብሮች ማሳካት ይቻላል።
ከምንሰጣቸው ድጋፍ፣ ክትትል እና ትምህርት መካከል፦
የመግባባት ክህሎት፦ የኦቲዝም ተጠቂ ልጅን የማህበራዊ እና የቋንቋ ችግሮች ላይ በመሥራት የመግባባት ክህሎትን ማጎልበት።
የባህሪ ለዉጥ፡- የኦቲዝም ተጠቂ ልጅ ሊኖሩት/ዋት የሚችሉትን አስቸጋሪ ባህሪያትን በመቀነስ እና መልካም ሥነምግባርን በማስረፅ ተፈላጊ የባህሪ ለዉጥ ማምጣት።
ትምህርት፡- ኦቲዝም ላለባቸዉ ህፃናት በጥናት በተቀረፀ የትምህርት መርኃግብር እና ለዚሁ አላማ በተዘጋጁ የትምህርት መርጃ መሳርያዎች በመታገዝ የቤት ውስጥ ተጨማሪ ትምህርት በመስጠት የልጆቹን የትምህርት አቀባበል ማሳደግ።
ቤተሰብ ተኮር ድጋፍ፡- ወላጆችና ሌሎች የቤተሰቡ አባላት የኦቲዝም ተጠቂ ልጅን የመግባባት ክህሎት እና ችግሮችን የመፍታት ችሎታ ለማዳበር በምን መልኩ መቅረብ እና አብረዉ መጫወት እንዳላባቸው ማስተማር።
ለበለጠ መረጃ በሚከተሉት የስልክ ቁጥሮች ይደውሉ፦
0913011134
0910916602
@wegoch
@gebriel_19
Belay Bekele Weya
"እእፓ"(እኛው እንታረቅ ፓርቲ)
(በላይ በቀለ ወያ) # ሼር ይደረግ!
.
.
ከኛ ካልቀደሙ ፣ ምንከተላቸው
ለኛ ካላሰቡ ፣ ምሁር ምንላቸው
ከኛ የተሻለ
ማየትን ካልቻሉ ፣ እኛን የሚመሩን
ለእርቅ ያጨናቸው ፣ በፀብ ካቃቃሩን
አንድ አርጉን ያልናቸው
በብሔር ፣ በክልል ፣ ከፋፍለው ካጠሩን
ህልውናችንን
አምነን ምንሰጣቸው ፣ ለኛ ካለሰቡ
እኛን እንደማስፋት ፣ ቀድመው ከጠበቡ
ትውልድን ከትውልድ ፣ ካላቀራረቡ
አንድ ሀገር አፍርሰው ፣ መንደር ሳይገነቡ
በእኛ ላብ ሳይወዙ ፣ በኛ ደም ሳይሰቡ
እኛው እንታረቅ !
።።።
አክቲቪስቶቻችን ፣ አክቲቮች ካልሆኑ
የጎበጠን ትውልድ ፣ ጎብጠው ካላቀኑ
ለሀገር ካልቆሙ ፣
ሚከተላቸውን ፣ ወድቀው ካላፀኑ
እኛ አለንላቹ ፣ እሚሉን ከሌሉ
እንድንጠፋፋ ፣ ነገር ከፈተሉ
ቂም የቋጠረውን ፣ ማስታረቅ ካልቻሉ
ያለፈን ጠባሳ ፣ ነቅሰው ካልኳሉ
ለተቋሰልን እኛ ፣ ከኛ ካልተሻሉ
ቁስልን እንደማከም ፣ ቁስልን ከነካኩ
ሰላም እንደመስጠት ፣ በፀብ ከተመኩ
በኛ ላብ ሳይወዙ ፣ በኛ ደም ሳይረኩ
እኛው እንታረቅ።
።።።።
ነፃ አውጪ ነን ባዩ ፣ ጭቆናን ካመነ
ነፃነት ከነሳን ፣ በውሀ ቀጠነ
በታመሙ ህዝቦች
ለታመች ሀገር ፣ መድሐኒት ካልሆነ
ፈውስ መሆን ሲችል ፣ መርዝ ከቀመመ
ለመረዙት ትውልድ ፣ መርዝ ሆኖ ከቆመ
ስላም ለናፈቀው ፣ ሽብር ከሸለመ
ከኛ የተሻለው ፣ ለእኛ ካልጠቀመ
ለእኛ የታገለው ፣ ለእኛ ካልተገዛ
በሀገር ፍቅር ፈንታ
በሀገር ላይ ጥላቻ ፣ አትሞ ካባዛ
በእኛ ደም ሳይረካ ፣ በኛ ላብ ሳይወዛ
እኛው እንታረቅ።
።።።
የፖርቲዎች ብዛት ፣ ሀገር ካላፀና
ለሚነታረክ ህዝብ ፣ ካልሰጠ ፅሞና
ከኛ የተሻሉ ፣ ለእኛ ተደራጅተው
ከእኛ ቁጥር በላይ ፣ ፓርቲዎች መስርተው
ካላስተቃቀፉን ፣ በሀሳብ ተጣልተው
እኛን ሚወክሉ
ከእኛ ካልተሻሉ
ሸክም ሳይሆኑብን ፣ ሸክም የሚያቃልሉ
በእኛ ደም ሳይፈኩ ፣ በእኛ ደም ሳይጎሉ
እኛ የኢትዮጵያ ህዝቦች ፣ ያለ አንዳች ውከላ
"እእፓ" ሚል ፓርቲ ፣ መስርተን በመላ
እኛው እንታረቅ! ፣ እኛው ስንጣላ።
@getem
@getem
@getem
"እእፓ"(እኛው እንታረቅ ፓርቲ)
(በላይ በቀለ ወያ) # ሼር ይደረግ!
.
.
ከኛ ካልቀደሙ ፣ ምንከተላቸው
ለኛ ካላሰቡ ፣ ምሁር ምንላቸው
ከኛ የተሻለ
ማየትን ካልቻሉ ፣ እኛን የሚመሩን
ለእርቅ ያጨናቸው ፣ በፀብ ካቃቃሩን
አንድ አርጉን ያልናቸው
በብሔር ፣ በክልል ፣ ከፋፍለው ካጠሩን
ህልውናችንን
አምነን ምንሰጣቸው ፣ ለኛ ካለሰቡ
እኛን እንደማስፋት ፣ ቀድመው ከጠበቡ
ትውልድን ከትውልድ ፣ ካላቀራረቡ
አንድ ሀገር አፍርሰው ፣ መንደር ሳይገነቡ
በእኛ ላብ ሳይወዙ ፣ በኛ ደም ሳይሰቡ
እኛው እንታረቅ !
።።።
አክቲቪስቶቻችን ፣ አክቲቮች ካልሆኑ
የጎበጠን ትውልድ ፣ ጎብጠው ካላቀኑ
ለሀገር ካልቆሙ ፣
ሚከተላቸውን ፣ ወድቀው ካላፀኑ
እኛ አለንላቹ ፣ እሚሉን ከሌሉ
እንድንጠፋፋ ፣ ነገር ከፈተሉ
ቂም የቋጠረውን ፣ ማስታረቅ ካልቻሉ
ያለፈን ጠባሳ ፣ ነቅሰው ካልኳሉ
ለተቋሰልን እኛ ፣ ከኛ ካልተሻሉ
ቁስልን እንደማከም ፣ ቁስልን ከነካኩ
ሰላም እንደመስጠት ፣ በፀብ ከተመኩ
በኛ ላብ ሳይወዙ ፣ በኛ ደም ሳይረኩ
እኛው እንታረቅ።
።።።።
ነፃ አውጪ ነን ባዩ ፣ ጭቆናን ካመነ
ነፃነት ከነሳን ፣ በውሀ ቀጠነ
በታመሙ ህዝቦች
ለታመች ሀገር ፣ መድሐኒት ካልሆነ
ፈውስ መሆን ሲችል ፣ መርዝ ከቀመመ
ለመረዙት ትውልድ ፣ መርዝ ሆኖ ከቆመ
ስላም ለናፈቀው ፣ ሽብር ከሸለመ
ከኛ የተሻለው ፣ ለእኛ ካልጠቀመ
ለእኛ የታገለው ፣ ለእኛ ካልተገዛ
በሀገር ፍቅር ፈንታ
በሀገር ላይ ጥላቻ ፣ አትሞ ካባዛ
በእኛ ደም ሳይረካ ፣ በኛ ላብ ሳይወዛ
እኛው እንታረቅ።
።።።
የፖርቲዎች ብዛት ፣ ሀገር ካላፀና
ለሚነታረክ ህዝብ ፣ ካልሰጠ ፅሞና
ከኛ የተሻሉ ፣ ለእኛ ተደራጅተው
ከእኛ ቁጥር በላይ ፣ ፓርቲዎች መስርተው
ካላስተቃቀፉን ፣ በሀሳብ ተጣልተው
እኛን ሚወክሉ
ከእኛ ካልተሻሉ
ሸክም ሳይሆኑብን ፣ ሸክም የሚያቃልሉ
በእኛ ደም ሳይፈኩ ፣ በእኛ ደም ሳይጎሉ
እኛ የኢትዮጵያ ህዝቦች ፣ ያለ አንዳች ውከላ
"እእፓ" ሚል ፓርቲ ፣ መስርተን በመላ
እኛው እንታረቅ! ፣ እኛው ስንጣላ።
@getem
@getem
@getem
👍1
*ሰዎች ይገርመኛል*
ልቡን ከአባይ ማዶ በረሀ በልቶበት
ከቀዝቃዛው ከኛ መንደር ተቅበዘበዘት
በአርምሞ ብቃኘው ለኔ ያለው ፍቅር አናት
የበኩር ፍቅሩ ትዝታዋ አለበት
ወይ አለመታደል
ፀጉር በሌለበት ለሚዶ መጋደል፡፡
ብሌን አሰላ
@Getem
@getem
@gebriel_19
ልቡን ከአባይ ማዶ በረሀ በልቶበት
ከቀዝቃዛው ከኛ መንደር ተቅበዘበዘት
በአርምሞ ብቃኘው ለኔ ያለው ፍቅር አናት
የበኩር ፍቅሩ ትዝታዋ አለበት
ወይ አለመታደል
ፀጉር በሌለበት ለሚዶ መጋደል፡፡
ብሌን አሰላ
@Getem
@getem
@gebriel_19
**** እኔ አንተን ስወድህ****
ልክ እንደ ጠዋት እንቅልፍ
ሰመመን የቃጣው
በአእዋፍ ዜማ የታጀበው
የካህናት ወረብ
ፅናፅል የሞላው
ልክ እንደ ሰማይ ጥግ
ፈክቶ እንደሚበራው
እንደ ምስራቅ
ሰማይ ጨረር የጋረደው
እንደ አዲስ ተስፋ
፣፣፣እኔ አንተን ስወድህ፣፣፣
እንደ ቀትር ፀሀይ
ውሎ እንደሚጣፍጥ
የማለዳ ጀምበር
ለመምሸት የሚያምጥ
እንደ ምሳ ሰአት
ደግሞም እንደ መቅሰስ
አንድ ላይ አጣምሮ
ጉራሽ እንደመቅመስ
ልክ እንደዛ ምሳ
ፍቅር እንደሞላው
የአብይ ፆም ውሎ
አስሮ እንዳሰቃየው
።።።እኔ አንተን ስወድህ።።።
አብረን እንደመሳቅ
ደግሞም እንደማልቀስ
የአንድነት ዋዜማን
አብረን እንደመቁረስ
ምሽት ላይ ተጋግዘን
ዘመን እንደመድረስ
በእሳት በውሀ
በባህር መዋኘት
በውህደት አለም
ባንድ መገናኘት
ምድር ስትሞሸር
ፅሀይ ስትዘቀዝቅ
ኮከቦችን ማየት
ጨረቃንም ማድነቅ
እኔ አንተን ስወድህ
ጠዋትና ማታ ሁሌ ማስታውስህ
ምሽት4:25 አ አ
✍✍Jerry dimple✍✍
@getem
@getem
@gebriel_19
ልክ እንደ ጠዋት እንቅልፍ
ሰመመን የቃጣው
በአእዋፍ ዜማ የታጀበው
የካህናት ወረብ
ፅናፅል የሞላው
ልክ እንደ ሰማይ ጥግ
ፈክቶ እንደሚበራው
እንደ ምስራቅ
ሰማይ ጨረር የጋረደው
እንደ አዲስ ተስፋ
፣፣፣እኔ አንተን ስወድህ፣፣፣
እንደ ቀትር ፀሀይ
ውሎ እንደሚጣፍጥ
የማለዳ ጀምበር
ለመምሸት የሚያምጥ
እንደ ምሳ ሰአት
ደግሞም እንደ መቅሰስ
አንድ ላይ አጣምሮ
ጉራሽ እንደመቅመስ
ልክ እንደዛ ምሳ
ፍቅር እንደሞላው
የአብይ ፆም ውሎ
አስሮ እንዳሰቃየው
።።።እኔ አንተን ስወድህ።።።
አብረን እንደመሳቅ
ደግሞም እንደማልቀስ
የአንድነት ዋዜማን
አብረን እንደመቁረስ
ምሽት ላይ ተጋግዘን
ዘመን እንደመድረስ
በእሳት በውሀ
በባህር መዋኘት
በውህደት አለም
ባንድ መገናኘት
ምድር ስትሞሸር
ፅሀይ ስትዘቀዝቅ
ኮከቦችን ማየት
ጨረቃንም ማድነቅ
እኔ አንተን ስወድህ
ጠዋትና ማታ ሁሌ ማስታውስህ
ምሽት4:25 አ አ
✍✍Jerry dimple✍✍
@getem
@getem
@gebriel_19
ስትሻኝ ነይ በለኝ
ስትሻኝ ነይ በለኝ
ያንተው ከርታታ ነኝ
እዚህ ነይ እዚያ ነይ
ብትለኝ እኔ አለው
ሁሌም ካንተ ውጭ
ማን አለኝ እላለው፡፡
አገልጋይህ አርገኝ
ከእግርህ ስር አጎንባሽ
እህሉን ከአፍህ
እኔ ልሁን አጉራሽ፡፡
ውሀውን በተራ
በኔ እጅ ተጎንጨው፡፡
ያንተ እጅ አይንካ
ምንም አያምርበት ፡፡
ይልቅስ ባንተ እጅ እኔን እቀፍበት
ያንተ እጅ አይንካ
ምንም አትስራበት እኔን እቀፍበት፡፡
#ሄርሜላ_ውብሸት
@getem
@getem
@gebriel_19
ስትሻኝ ነይ በለኝ
ያንተው ከርታታ ነኝ
እዚህ ነይ እዚያ ነይ
ብትለኝ እኔ አለው
ሁሌም ካንተ ውጭ
ማን አለኝ እላለው፡፡
አገልጋይህ አርገኝ
ከእግርህ ስር አጎንባሽ
እህሉን ከአፍህ
እኔ ልሁን አጉራሽ፡፡
ውሀውን በተራ
በኔ እጅ ተጎንጨው፡፡
ያንተ እጅ አይንካ
ምንም አያምርበት ፡፡
ይልቅስ ባንተ እጅ እኔን እቀፍበት
ያንተ እጅ አይንካ
ምንም አትስራበት እኔን እቀፍበት፡፡
#ሄርሜላ_ውብሸት
@getem
@getem
@gebriel_19