ግጥም ብቻ 📘
67.4K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
174 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
አንተ እንባዬ ምረጥ
ልግለጥህ?
ልዋጥህ?
ላፍንህ?
ልልቀቅህ?
ላፍስስህ
ላምቅህ?
ምን ላርግህ? ምከረኝ
ምንድነህ? ንገረኝ

እህል ትሆን ጠፊ?
ወይስ ሽል ነህ ገፊ?
በጊዜ ልወቅህ...
ላቅርብ ወይ ላርቅህ...
አጫጅ ነህ አራሚ?
ተጓዥ ነህ ከራሚ?
አላፊ ነህ ቋሚ?
ምንድነህ?
ምን ላርግህ?
ላግድህ?
ላውርድህ?
ጋርጄ ልካድምህ?
አውርጄ ልካድህ?
ቢያፍኑህ ቀሪ ነህ?
ቢለቁህ ኗሪ ነህ?

እንባዬ ምን ላድርግህ?
ላስርግህ?
ልጥረግህ?
እንዳ'ይን እንዳ'ፍንጫ
ቋሚ መገለጫ
መታወቂያ መልኬ ፡ ሆነህ ትኖራለህ?
ወይስ ላ'ንዴ ወርደህ፡ በዚያው ትቀራለህ?

አንተ እንባዬ ምረጥ
ላብስህ?
ላልብስህ?
ወይስ እንዳላየ፡
ከኔ የወጣ ሁሉ፡
የኔ አይደለም ብዬ
ልተውህ እንባዬ?

ወይስ ልገላገል?
እውነቱን ልናገር?
እንዲህ ነህ እንዲያ ነህ
እያልኩኝ ከማበል
አላውቅህም ልበል?

By #red-8

@getem
@getem
@paappii
47👍38🔥8
አንቺን ያየ ምድር አንቺን ያየ ሰማይ

ስንት ዐመት ቀጠለ በስፍር ዕድሜው ላይ?

።።።።።።።።

በጠለቅሽበት ጥግ

መውጣት ስላቅ ሆነ ፀሐይ ቀረች አፍራ

እኔም ደስታ እንዳለው

ማልቀስ ይከብደኛል በሳቅሽበት ስፍራ።

የት ቆሜ እንባ ላፍስስ የት ልበል እዬዬ

በሳቅሽ የፈካ

አይታዘበኝም ዛፍ ቅጠሉ እያዬ?

ምድር እንዳይንቀኝ

በወንዙ በሀይቁ ቀልዬ እንዳልገኝ

በነፋሱ ትዝብት እንዳላንስ ወድቄ

ለፍጥረት እይታ በሳቅ አሸብርቄ

እስቃለሁ ለጉድ እንከተከታለሁ

እንጂማ

ሳቅሽ ዳር ብፈለግ የእውነት የታለሁ?



እና የኔ ኪዳን

መቼ ልትወጪ አሰብሽ?

እንዳያፍር ምድር እንዳያፍር ሰማይ

እግዜሩም አልሠራም ጠልቆ ሚቀር ፀሐይ!

አባባይ ሆንኩልሽ የእሹሩሩ ካድሬ

ጨለማውን በሳቅ ሳባብል አድሬ

እንቅልፍ ቢወስደው ከዛለ መዳፌ

እንባ እየናፈቁ መሳቅ ሆነ ትርፌ።

እንደሰው ሲደክመው ሌቱ ሲያንቀላፋ

አማጥኩኝ ለለቅሶ እህህህ አልኩኝ ለሳጌ

ሁሌ ምገኘው ግን ከፈገግታሽ ግርጌ።

የሳቅሽን ዘቢብ

ምን መልአክ ቀመሰው ምን አማልክት አየው

የፈገግታ ጭረት ፊቴ ማይለየው?

አንቺ…

ሕይወት ክንብል አለ ቆመ ተዘቅዝቆ

ዘላለም ይሠራል አንድ ቀን ተስቆ?



ዙሪያዬን ሳቅ ከቦኝ እምን ላይ ልደገፍ

እንባዬ ያምረዋል እዚም እዛም መርገፍ።

ያሰኘኛል ዋይታ

ዕድሜዬን ማዋዛት በሀዘን ማለዘብ

ግን ትልቅ ሀጢአት ነው

ከቁርባን ፊት ቀርቦ ቁርባኑን መታዘብ።

ሜሮን ነበር ሳቅሽ ሀዳስ የሳቅ ጠበል

ፅድቅ ነበር ለሰው

ያንድ ቀን ደስታሽ ስር ዳስ ሠርቶ መጠለል።



መቼ ልትወጪ አሰብሽ?

መቼ ልትመጪ አሰብሽ?

በፍጥረት ልብ ላይ ጎጆውን ቀልሶ

ሳቅሽ አንጀት በላ እንዳራራይ ለቅሶ።

አበባው ይስቃል

ቅጠሉ ይስቃል

እሾሁ ይስቃል ድንጋዩ ይስቃል

አፈሩ፣ እሳቱ ነፋሱ ይስቃል

አንዴም ሳያነባ ሰው እንዴት ይፀድቃል?

ሳቅሽ ወንጌል ሆነ ምጻት መፋረጃ

ውስጤ እንባ ደርድሬ

ለብይን ብጠራ አቋቋሜን እንጃ!

አቤት አቤት አቤት

ከአምላክ ከፍጡር ከማነው ወገኑ

ሺህ ኩነኔ መሃል ሳቅሽ መጀገኑ!

አንቺ የሳቅ ኪዳን

ሩቅ ነሽ ለህመም ቅርብ ነሽ ለመዳን

እኔ ግን ተመኘሁ

በፈገግታሽ በኩል እንባዬን ልነካ

አንቺ…

ማልቀስ በመፈለግ ሳቅ ይረክሳል ለካ።



አንድ ቀን ስቃልኝ

ስፍር ዕድሜዬ ላይ ዕድሜ መርቃልኝ

የሰማይ የምድሩን መሳቅ አስለምዳው

ልክ እንዳመጣጧ ብትጠልቅ ወዲያው

ሕይወት ድፍት አለ ቆመ ተዘቅዝቆ

ዘላለም ይሠ
ራል አንድ ቀን ተስቆ?

By yadel Tizazu

@getem
@getem
@paappii
👍4229🤩4🔥2
ድንኳን አይጥሉለት፣
ጥየቃ አያውቀው፣
ሰአቱን መጠበቅ ቀን ማወቅ አይለቀው፤
ሁሌ አብሮ አይኖር፣
ሁሌ መጪ እንግዳ፣
ሁሌ ምቾት ነሺ የሰባት ቀን እዳ፤
ሁሌ ተባበይ ባይ፣
በመጣ በታየ፣
ሁሌ የመድሎ ልጅ በጾታ የለየ፤
ሁሌ ፊት አደብዛዥ፣
የዙር አመል ከላሽ፣
ሁሌ ተጠባቂ ሁሌ መቶ ረባሽ፤
የልምላሜ መልክ፣
ከመባረክ ጓዳ፣
የሔዋን እጣ ነው ክቡር የሤት እዳ።

By @eyadermoges1

@getem
@getem
@paappii
32👍16🤩5🔥3
ባዶ እኮ ነች።
(የሞገሤ ልጅ)
መጀመርያ፣
ኑ እንፍጠር በመባባል አምላክ ራሱን ሳያማክር፣
ዘረጋግቶ፣
እውን ሆነው እስኪታዩ እስኪኖሩ ምድር ጠፈር፤
ለባዶነት፣
ያጨው ነገር ለመኖሩ ስለማናውቅ ምንም ባንል፣
ምድራችን ግን፣
ከአካሏ ተቀናንሰው ሳር ቅጠሉን እስክታበቅል፤
አሁን ጠባ፣
በቤት ላይ ቤት እንዲሰራ ሠው ወገኗን ያስገደደች፣
ዛሬ ሳንደርስ፣
ጅማሮዋን ብቸኝነት ያካረማት ባዶ እኮ ነች።
ልክ እንደሷ፣
ሃ ማለቴን አፍ ሳይሆነው ጅማሮዬን አብሮት ሳይቆም፣
አሁን መቶ፣
ሄደሽ መቶ ባዶነቴ መከበቤ ቢደመደም፤
ባዶነቴ፣
አዲሥ ሕይወት አዲሥ መንገድ እንዲያመጣ ምድር ሆኜለት፣
መከፋቴን፣
መቀየሩ ስለማይቀር ባዶነቴን ገጠምኩበት።

ገጠምኩበት..

አልወደኩም፣
ሆኖ ሲታይ ባልጣለው ፊት ላልወደቁት ሲመሰክር፣
ያሳምናል፣
የአይን አዋጅ ለሆነበት ዝናን ማድመቅ ቀሪን መቅበር።

አንድ አንዴ ግን፣
ግዳጅ ጥሎ ፎካሪ ላይ ተሽመድምዶም መዘባበት፣
ቀን ያወጣል፣
ወድያ ወዲህ ተንጎራዳጅ አምላክ ፈቅዶ ከዞረበት።

ያን እለት ግን..
ራሱን ሆኖ ከጣለው እጅ ተፍገምግሞ የተነሳ፣
ባዶነቱን፣
ምርኩዝ ስጡኝ ባላለ አፍ መተኛቱን እስኪረሳ፤
ተመርኩዞ፣
ሲደጋግፍ ቆሞ ሊታይ የራሱ ቀኝ ራሱ ሆኖ፣
ባዶነቱ፣
ኃይል ይወልዳል ብርቱ ጉልበት ከድካሙ ተሰናስኖ።

ባዶ አረግሺኝ?

እንኳንም ሆንኩ!
አንቺን ይድላሽ፣
ግን ጨርሰሽ አትራቂው ብቸኝነት ከሚጠላሽ!

ለምን አልሺኝ?

ካልሺኝ እማ..
ምንም መሆን ምንም ነው፣
ለባዶነት ልኩ ያንሳል፣
አለመኖር ካጣ ፍጥረት ጉድለት ሞልቶት በዝቅታው ሺ ይብሳል።

ባዶነት ግን..
እርቃን መሆን ሸክሙ ከብዶ፣
ቋጠሮውን ለማላላት፣
አዲስ መንገድ ይፈልጋል፣
አዲሥ ነገር ለማሳየት።

By @eyadermoges1

@getem
@getem
@paappii
👍3216😱3🤩2😢1
ፍቅርን ፈራን
(ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን)

ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነት ለመድን

“ፈራን”
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን

“ናቅን”
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን

“ናቅን”
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን

“ጠላን”
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ

“ራቅን”
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን

@getem
@getem
@paappii
64👍34🔥3😱3
ብቻህን
(የሞገሤ ልጅ)
ያለማንም ፍቃድ ባገኘሃት ሃገር፣
ያሰኘህን ስራ፣
ያሻህን ተናገር!

እሪ በል!
ኡኡ በል!
እሪ እሚያስብል ካለ፣
ድምጽህ ከታፈነ፣
ክብርህ ከጎደለ።

በራስህ አካሄድ፣
በሃቅህ ጎዳና፣
ሰሚ የታባቱ፣
ምን ይጠቅምህ እና!

ብቻህን ተናገር፣
ብቻህን ዝም በል,
ብቻህን አግዘህ፣
ብቻህን ተገልገል!

ስላለችህ እውነት፣
ብቻህን ተሰለፍ,
ከጓዳህ አቅራቢያ፣
ከኩሽናህ ደጅ_አፍ።

ታዲያ ሞኚ እንዳትሆን!

ጥፋት እንደሚቆም፣
ፍርድ እንደሚቀየር,
በደል እንደሚያከትም፣
ጉዳት እንደማይኖር;
አስበህ ኣትጓጓ፣
የሩቁን አትጎምጅ፣
እራስህ ስለሆንክ፣
የእራስህ ወዳጅ።
ደራሽ በማሰስህ፣
ድራሽህ ሊጠፋ፣
በማጣትህ ማግጠህ፣
ጉዳትህ ሊከፋ፤
አማረህ ላታገኝ፣
ጮኸህ ልትቀማ፣
ልብህ ቢነሳሳ፣
ለሁከት ለአድማ፤
ታግለህ ላታሸንፍ፣
ጥለህ ላትሻገር፣
ኖሮ ካላገዘህ፣
ማመልከት መናገር፤
ድካምህ ቢቀንስ፣
ሠው ከምትጣራ፣
ያለአንደበትህ፣
ልብህ ለዐምላክ ያውራ!

ደግሞስ ለምን ከፋህ?

ግዜ ካልፈቀደ፣
እንዳሻህ እንድትኖር፣
እንደተባልህ መሆን፣
ማድረግ ብትቸገር፤
ፊት የነሳህ እለት፣
ፊቱን እስኪመልስ፣
መሽቶ እስኪነጋ፣
ነገን ብትታገስ፤
በላብህ ብትበላ፣
በደምህ ብትኖር፣
ለአንተ የተባለው፣
ባልቀረብህ ነበር።

By @eyadermoges1

@getem
@getem
@getem
👍3018🔥2
"ያ ባሏ ፈታት አሉ...ወስልታበት"
"አየህ አይደል ለክፉ ክፉ ሲያዝበት?"
"ኧረ ከሷ ውጭ ሴት አያውቅም ነበር"
"ሚስትህ ነግራኝ ባይሆን አላምንህም ነበር"


ዘማርቆስ

@getem
@getem
@getem
😁5917👍14🤩5👎3😱3
እንዲገባሽ!
(የሞገሤ ልጅ)
ከመከፋት ያልፋል፣
ሃዘኔ ሃዘን ነው ይከምራል አጭዶ፣
ላላልቅ ያነደኛል፣
ከሃሳብ ወላፈን ናፍቆት እሳት ማግዶ።

ባታውቂ ነው እንጂ..
አልመጣም ማለትሽ በናፍቆት ያስምጣል፣
ከሰመመን ዘፍቆ ከቅዠት ያሰምጣል፣
ከራስ ስጋ አጣልቶ ከመንፈሥ ያርቃል፣
ሠው ማጣትም ከብዶ ሠው ማግኘት ይጨንቃል፣
ስሜት እንደ ጥይት ድንገት ይባርቃል፣
ያልበላን ሠውነት ረሃብ ያጠረቃል፣
የእስከአሁኑ እንዲህ ነው ነገንስ ማን ያውቃል?

ህ!
ህ!
እህህ!

ደሞ ያልነገርኩሽ..
ክርሥቶሥ የኛ ሺ ለሱ አንድ እለት፣
ለኔ ስትቀሪ..
አልመጣም ማለትሽ ቀኔን አርጎት ሳምንት፣
ባልነግርሽ ነው እንጂ..
ስላላወቅሽልኝ መምጣት የምትረሺው፣
ብነግርሽ ኖሮ እማ..
ባትመጪም እንኳን ከመቅረትሽ ጀርባ ጉዳቴን ባየሺው።

ደሞ የረሳሁት..
በአንድ የቀን ጉዱ አንቺነትሽ ወርሶኝ፣
እኩል እኔን ላንቺ ለማካፈል ቆርሶኝ፤
ድሮም አንድ አጥንቴ አንቺ ዘንድ ቀርቶ፣
እሱን እንደማግኘት መከፈሌ በዝቶ፤
ወይ ይዘሽ አልያዝሽው ደጅ ጥናት ጎዳው፣
ወይ ለኔ አልሆነ ራሴን ራሴ ከዳው፤
አንቺም ለመምጣትሽ አጠረኝ ማስረጃ፣
ሁለት አድርገሽኝ ሠው መሆኔን እንጃ።

እባክሽ መውደዴን ችለሽ አታኩርፊው፣
ልቤ ቆሞ ደክሟል ራርተሽ አሳርፊው፤
የኔ ብቻ ሁኚ የኔ ብቻ አለም፣
መድከሜ ላይቋጭ ላያልቅ አይርዘም፤
የኔ ብቻ ሁኚ ካምላክሽ ቀጥሎ፣
ላንቺም ግፍ ነው ማለፍ ታማሚሽን ጥሎ፤
ስለዕመቤቴ እሩሩዋ እናት፣
ቢጤሽን መጽውቺኝ ልብሽን ልመጽወት።

ያኔ እድናለሁ፣
እጠነክራለሁ አላለቃቅስም፣
አሁን ላይ ግን ከኔ፣
ማጥፋቴ ስም ሊያሰጥ አይነቃቀስም።

ተረዳሽኝ አይደል?

አዎ ተረድተሻል።
እንጂ እማ ወዳጁን፣
ካልታመመ በቀር ማስከፋት ማን ይሻል?

አዎ ተረድተሻል!

ይበልጥ እንዲገባሽ..
ምን ከቤት ቢገፋ፣
ባልለመደው ንፋስ ሊገረፍ ቢሰጥም፣
ያበደ ውሻ እንጂ፣
ያልታመመ ውሻ የጌታውን እግር ሊጎዳ አይነክስም።

አሁን ዘልቆ ገባሽ?
አዎ ተረድተሻል!
ስለዚህ እብድ ውሻሽ ለነከሰሽ ሊክስ ጤነኛ እንዲሆን ይቅርታሽን ይሻል።

By @eyadermoges1

@getem
@getem
@paappii
👍4917😢9
ግጥምና አበባ

በርግጥም በርግጥም
አትጨክኚም አይደል በአበባ በግጥም
ትወጃለሽ አይደል?
ሀቅን በቃል መግደል ?
ትፈቅጃለሽ አይደል ?
በስንኝ መደለል?

( እንግዲህ... )

እውነት እንኪገባሽ
ፍቅር በአፍሽ ጥላ
መውደድ በዓይንሽ ጥላ
ናፍቆት እንዲያረቅሽ
ህይወት በአንቺ ገላ
እስከዚያ ግን ድረስ
ተስፋ ተሞልቼ...
ባዶ እጄን ልመለስ
እየከፋኝ ልግባ
እስክሰጥሽ ድረስ ግጥምና አበባ!

By Sirak Wondemu

@getem
@getem
@paappii
👍2515🎉3😱2🔥1🤩1
ይድረሰ:- ለኩርፊያ
(ሳሙኤል አለሙ)
°
°
የሻማው ብርሃን ደብዝዞ
የንፋስ ሽውታ ጠረገው፤
አፋችኑ ቃላት አርግዞ
አምጦ መውለድ አቃተው፤
ዝም...ዝም...ዝም
ጭልም-ልም-ልም
ገዘፈ ድቅድቁ ጨለማው፤
ቃላችንን ሾተላይ ቀማው።
°
°
እንደ'ኔና እንደ እሷ
ጀምበሩ ሳይነጋ
መሰሎቻችን ጋ
አፋቸውን ሊያዘጋ
ጥድፍ-ድፍ-ድፍ...ሲል
ርብት-ብት-ብት...ሲል
ደርሶ አፋችንን ቆልፎበት።
ደጃፉ ላይ ፥ ስደርስበት።
°
°
ቀኝህን ለሚመታ
ግራውን ስጡት እንዳለው ጌታ
ሳትነፍገው የእግዜሩን ሰላምታ
እንደ ዲዳ ዝም ካለህ
ላፍታም... ላፍታም.... ሳታመንታ
ኩርፊያን <እንኳን ደስ አለህ!>
በልልኝ!
°
°
ይኸው እኔና እሷ
ሰርክ ኩርፍ ኩ-ርፍ-ርፍ
ሰርክ እቅፍ እ-ቅፍ-ቅፍ
ይኸው እኔና እሷ
እንደ ቄጤማው ፥ እንደ አውዳመቱ፤
ድንገት ካየኸው ፥ የኩርፊያን ፊቱ፤
ትላንቱ ለምልሞ ፥ ዛሬ ክስመቱ።
°
°
እንደ ጳጉሜ ሶስት ዕለቱ
ዕንባውን አዘነብነው።
የሩፋኤል ፀበል አይደል
ክፋቱን አያድነው።
ከጫጫታው አልፈን
ነጎድጓዱን አክለነው።
ጭቅጭቁን አድ'ምጦ
በዜማ አቀነቀነው።
°
°
ተወው በክረምቱ ፥ ይርገጥ ዳንኪራ
ተወው በዕንባችን ፥ ይስከር ያሽካካ
በፀደዩ ብርሃን ፥ እንደምንፈካ
ዘንግቶታናልና!
°
°
የዛሬዋን ዕድል
ከቆጠረው ከድል
ትርኢት ያዘጋጅ
እንግዳም ይጥራ ፥ ድግሱንም ይደግሰው
እንደ ንጉስ አይዙር ፥ ግማሽ ቀኑን የሚነግሰው
ተወው!

ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu

@getem
@getem
👍3010🔥1
ማዘን በኛ ይበቃ
ፎቶዋ ይከልከል
እሷን ያየ ሁሉ
በፍቅር አይበከል

ዮኒ
     ኣታን @yonatoz

ንሸጣ: ገጣሚ እንደልቡ

@getem
@getem
@getem
👍2611😁5👎4🔥1
የመሃን መሓላ
(የሞገሤ ልጅ)
ከጠበልተኞች ደጅ፣
ደጅ ጠኚ መሃል፣
ሱባኤ ሳትይዝ ሰርክ ሳትጠበል፤
መታመሟን አውቃ፣
ላለመዳን አምና፣
ከእምነቷ ሳስታ አለመቻል ታጥና፤
ቅናትን ስራ አርጋ፣
ብቸኝነት ወርሷት፣
ሠው መሃል ሠው አታ ሠው መፈለግ ታክቷት፤
ዐይኗን አደራርቃ፣
በልቧ እያነባች፣
ድካሟ ደግፏት ጽናቷን እያጣች፤
ከጠበልተኞች ደጅ፣
ስለት ደርሶ ልታይ፣
ንግሥ ኪዳን ሳትል ከደጀሠላም ዋይ፤
ተሥፋ የገረፋት፣
ማግኘቷን አርቆ፣
ማሕጸን ለማርጠብ እልፍ አስጠብቆ፤
ያሰለቸ ተሥፋ፣
ሚራዡ ምትሓት፣
ልጄን ይንሳኝ የሚል መሓላ አስለመዳት።

ብትዋሽ ሟች የለ፣
አይመሰክር ቆሞ፣
ጠፊም መጪም ሳይኖር ቃልኪዳን ታትሞ፤
ልጄን ይንሳኝ ፍርሚያ፣
ዋጋ ያላገኘ፣
ተሥፋን ባጣች መሃን አንደበት የዋኘ፤
ቢዋሽ ጉዳት አልባ፣
ባይዋሽም ምንም፣
የሌሎች ዶግማ ቃል ለመሃን አይከብድም።
የሌላት አይሞትም፣
የሌላት አይመጣ፣
ናፍቆት ቅናት በልቷት ከተሥፋ ተቋርጣ፤
ልክ እንደወለዱት፣
መሆን እያማራት፣
ልጅ አፏን እንዳይሸሽ መሃላዋ ይዞት፤
ዋሽታም “ልጄን ይንሳኝ”፣
ለእውነትም “ይንሳኝ”፣
ልማድ ሆኖባታል ላታጣም ላታገኝ።

By @eyadermoges1

@getem
@getem
@paappii
👍4011😢10🔥1
የናፈቀኝ ነገር
ያልኖርኩበት ሃገር!
ማንም ሰው ሳያውቀኝ÷ ከዜሮ መጀመር
ጠዋት የምሰማው
የማላውቃትን ወፍ፣ አዲስ አዘማመር።

የፈለግሁት ነገር
መኖሪያ መቀየር
ልብሴንም መቀየር
ለየት ቢልልኝ
የምጠጣው ውሃ÷ የምስበው አየር።

መራመድ የሚያምረኝ
በአዲስ ጎዳና ላይ ÷ በኔ እግር የነቃ
ባገኝ አዲስ ሃሳብ
አዲስ አይነት እውነት ÷ ወይም አዲስ ቋንቋ።

ማየት የምመኘው ÷ያልራቀ ወደላይ
ሰማያዊ ሳይሆን ÷አዲስ አይነት ሰማይ
በማላውቀው ቀለም ÷ አዲስ አይነት ፀሃይ።
.
.
.
የማውቀውን ሁሉ
መተካት በመሻት
ወደማይታወቅ
ህይወቴን ብሸሻት
የማልሰለቸውን ÷ አጣሁት ፈልጌው
(ስገምት ችግሩን)
አዲሱን የሚያስረጅ ÷ እኔ ነኝ አሮጌው።

በርግጥ እንኳን ማርጀት ÷ መኖር ይለመዳል?
መሰልቸትን መቻል÷ ከናፍቆት ይከብዳል?

በማውቀው አኗኗር÷ መኖር ከከበደኝ
ወደማይታወቅ ÷ ልቤ ካሰደደኝ
እኔ የሌለሁበት ÷ ማንስ በወሰደኝ?
ወላጅ ባገኘሁኝ
በሆነ አይነት ታምር÷ ዳግም በወለደኝ??

By Haileleleul Aph

@getem
@getem
@getem
👍5842😱4🔥3😢3
ጥለሺኝ እየሄድሽ
.....
መንገዷን ጨርቅ አርገው፣
ህይወቷንም ቀና፤
የምል አይነት እንከፍ,
የምል አይነት ጀዝባ ፡ አይደለውምና፦

ኋላ አደናቅፎኝ
ከፎቅ ላይ ብጥልሽ
ስለምትጎጂ፤
ከተፋታን ወዲህ
መንገዱ ያሰጋል
ተጠንቅቀሽ ሂጂ።

© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
😁70👍2111🔥10🤩3👎1
ባለቅኔ ነበርኩ
ባለኝ ሰዓት ቅኔ
ያ...ኔ!

ቅኔ ይሏት እርግብ
አፍኜ ስመግብ
ስታዜም ስሰማት
መዝሙሯን ስቀማት
ቀምቼ ሳፏጨው
የሷን እየቀዳሁ፡ አድማስ ላይ ስረጨው፤
የሰማ ታማሚ፡ መስሎት የፈለቀኝ
ወደኔ እየመጣ፡ ፈውስ ሲጠይቀኝ፤
እሷ የምትለውን፡ ስሰማ ሳቀብል
ከሷ የሚፈሰውን፡ ስቀዳ ሳፀብል
የዳነው መስካሪ፡ ታምሬን ሲነዛ
ደጄን የሚናፍቅ፡ አማኝ እየበዛ
ለፀጋ ለስሜ፡ ሲመታለት ድቤ
በድንገት አምልጣኝ፡ በረረች እርግቤ።

ሄደች ከነድምጿ፡ በስም አስቀርታኝ
ሄደች ከነፈውሷ፡ ከገድሌ ጋር ትታኝ
የምበትንላት፡ ጥሬ ቀርቶኝ ከጄ
ቢረክስም በዜማ የፀደቀው ደጄ
በፈውስ ናፋቂ፡ ሰርክ ይጨናነቃል
ምስኪን! ኪን እርግቤ
እንኳንስ መሄዷን ፡መኖሯን ማን ያውቃል?

ብቻዬን አዘልኩት፡ አግኝቶ ማጣቱን
ጸጋው የተቀማ ፡ስም ሆኖ መቅረቱን
ማቃቴን አፍኜ፡ ብቻዬን ታመምኩት
በነበር ስወደስ ፡መቻልን ቃተትኩት፥

ግን አልሆነልኝም
አልጮህ ድምፅ የለኝም
ያድናቂዬ ድቤ፡ ዜማው ይበልጠኛል
አልጠፋ እንደርግቤ ማን ክንፍ ይሰጠኛል?
ታዲያ ከዚህ ስቃይ፡ ማን ያስመልጠኛል?

እውነት!

ባለቅኔ ነበርኩ፡ ያ...ኔ!
ቅኔ ይሏት እርግብ፡ እያለች ከጎኔ
ዜማዋ ሲያደምቀኝ ትንፋሿ ሲሞቀኝ
አርፎ እንደማጣጣም፡ እየቀዳሁ ስቀኝ
ያየ ሲያጨበጭብ፡ የሰማ ሲያደንቀኝ
ስጨምቃት ተጨንቃ የምታስጨንቀኝ
አንድ እርግብ ነበረች፤
አሁን ግን የለችም!
ለጠየቀኝ ሁሉ ፡እሺ ስል በርራለች።

ልክ እንደዛ ተረት፡ የልጅ መጫወቻ

ባለቅኔ ነበርኩ፡ አሁን ግን ፍራቻ
ሁሉን ነገር ላጣው፡ የቀረኝ ስም ብቻ።

By Red-8

@getem
@getem
@paappii
36👍32🔥15😢2
በነጭ ምዕመናን ታቦቷ ታጀበ
ዲያቆኑ ተነሳ ሊቃችን ወረበ

ጭብጫቦ እልልታው
     ዝማሬው ይበልጣል
ማርያም ማርያም ሲባል
      ስምሽ ይጣፍጣል።

ማርያም

ዮኒ
    ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
179👍25👎7🔥7🤩7😁3
ነይ


በሰማያዊ ሰማዩ ላይ አንሳፈፍ
በፍቅራችን ምናብ እንበል እና ከፍ
መኖር ውልክፍክፉ ሳያደናቅፈን
ነይ ሀሴት እናድርግ
በመውደድ ተቃቅፈን
ነይ አብረን እንብረር
ይህ መኖር ሳይጠልፈን

በህይወት ውበቷ የመኖርን ክርታስ
ሰብረን እንጣለው መኖርን አናስታውስ

በአብሮነታችን አለምን እንራሳ
ለኛ አይገባንም ያለም ግሳንግሷ
መኖርን እንካድ
ፍቅርን እናሳድ
እግዜር ይቀዬመን ሀጥያታችን ይብዛ
አብረን እንጥፋ እና አለምን እንግዛ

ነይ

መዓት ይውረድብን ሀጥያታችን በዝቶ
አንድ አንቺ ካለሺኝ ምን ሊጎድለኝ ከቶ
ነይ....................



by kerim

@getem
@getem
@getem
23👍16👎11😱4
...............


ሰአሊው በሸራው ዕርቃን መሳል ከለመደ
ጸሀፊውም በብዕሩ ዳሌና ጭን ከወደደ
አትሸፍኝው ከአደባባይ
ተጸየፊው ጨርቅሽን ጣይ
ጥበብ ይሆን የአምላክ ስእል
ዕርቃን መቆም ከአደባባይ
ስጋና ነፍስ ከአንድ አስራ
ለዘሞተች ገሀድ አለም
ውቡ ገላሽ ውበት ይሁን
የተፈጥሮ ንጽህ ቀለም
ምክንያት አሽቶ ቢመኝሽም
ዕርቃኗን ነች በሚል ቀመር
ልባስ የወሲብ ሽፋን ቢሆን
እንስሳ እንስን ቢደፍር ነበር
የለም የለም
አንቺን አይቶ ዝሙት የለም
እልፍ ብጥይ ጥለት ገፈፈሽ በሸራው
ተዳራሽ በብዕር በገሀድ በሰራው
ውል ለሌለው ሀሳብ የገፈፉት ገላ
አደባባይ ስትቀርብ ጥበብ ነች ተብላ
ጣይና ጨርቅሽን
ሁኚው የገሀድ ቀለም
የለም የለም
አንቺ አይቶ ዝሙት የለም

By @mad12titan

@getem
@getem
@getem
👍327👎5
አበባዬ ነበርክ የትንፋሼ ፊደል
የመኖሬ ምክንያት የነፍሴ መታደል
መጨከን የምችል አይመስለኝም ነበር
እስክትቃወመው የመውደዴን ነገር
ምንም ብታፈቅረኝ ውበቴን ብታደንቅ
ትችል አልነበር ወይ ህጎቼን መጠበቅ
አሁን ስናፍቅህ ከፍቶህ ስትጨነቅ
በቀረ ትል ይሆን ምናል ብጠነቀቅ

እራሴን እንደምን አረኩት ብቸኛ
መልካም ሰው ያገኘች ነበርኩ እድለኛ
ወራት አልፈው ነበር ብዙ ሳትጠጋ
ድንገት ተቀበልኩህ አንድ ሆንኩኝ ካንተጋ
የለሰለሰችው የልጅነትህ ፀሀይ
ለመሆን መረጥኩኝ የፍቅርህ ተከታይ

ይቅርታህም በዛ የከበደህ ሲቀል
እኔም ተበዳይ ሆንኩ በራስ የመታለል
እንዳልተማመንኩኝ እንደማልጎዳ
ያ ምቹ እቅፍህ ሆነብኝ እንግዳ
አይንይህም ከአይኖቼ በድንገት ተለየ
ያልከውን ለመሆን እጅጉን ዘገየህ

ይቅር እንደምልህ የተማመንክበት
ምን ይሆን ያሸሸህ ከሰጠሁህ ገነት
ምንድነው ያስናቀህ የጠለቀ ፍቅሬን
ለምን አልበቃህም ስትስም ከንፈሬን
እኮ እንዴት ችለህ እንዳልሳሳህልኝ
ጭንቀቴን አበዛህ እንዴት ጨከንክብኝ

እንደምን ልርሳልህ ያን የውሸት እንባ
ሀሳቤን ስትቀይር ሆዴን ስታባባ
እኔም ተንደርድሬ ከአእቅፍህ ስገባ
ቃልህ ተሰበረ ሆንክ የእምነት ሌባ
እኔስ ተሞኝቼ ከልቤ አፍቅሬ
እፊትህ ማለቅሰው ነበረ የምሬን

ለማትስተካከል ላትቀየር ነገር
እኔንም ስታገኝ ከሰነፎች ሀገር
ድካሜን ሳሳይህ አክመኧኝ ነበር
የተጠገነ ልብ ዳግመኛ ሊሰበር
እጆችህን ይዤ አይኖቼን ጨፈንኩ
መራኧኝ ወዳንተ ከራሴም ራቅኩ

ተደበቄ ሳለሁ ካንተ ተለጥፌ
ሙቀትህን ስሰርቅ ስዳስ በመዳፌ
አበባና ሻማው በድንገት ተረሳ
መልክህ ተለወጠ እጅህም ተነሳ
ልቤም ደነገጠ እየጠረጠረ
ለማመን ከበደው ልክ እንዳልነበረ
ያደረከው ነገር ሰበቡን ባቶስድም
አስለመደኧኛል ስህተት መደጋገም
ፍቅሬን ያቆሸሽከው ሳታውቅ አልነበረም

By - @mondalit

@getem
@getem
@paappii
👍2621😢10😱2
#ሩብ_አንድ_ሌሊት

መነሻ ሀሳብ
ስብሃት /እግዚአብሔር
(
ሌቱም አይነጋልኝ 1993 / )
.
.
እቱ፤
ይቅር ምናባቱ፣
አይነጋ ሌሊቱ።
ይለፍ እንደዘበት፤
ይጠቅለል ዐመቱ።
ሀሳብ እንደረሳ፤
እንደ ግልገል ሞሳ፤
'ቅፍሽ ስር ልክረም።
ሀሳቤን ሰብስቤ፤
በለዛሽ ተስቤ፤
ከልብሽ ማዕጠንት
ሰግጄ ቆርቤ፡፡
በጨዋታሽ ስጥም፣
ሎሚ ጉንጭሽን ሳም፤
ልዛል እንደገና
በመዓዛሽ ድክምም፣
ባለንጋ ጣቶችሽ
እሽት አከም አከም፤
እወገቤ ግድም፤
ቧጠሺኝ ደም በደም፣
ከዛ.....
ጡትሽ መሃል ጋደምምም።

በአይኖችሽ ስበት፤
በንግስናሽ ውበት፣
በትንፋሽሽ ሙቀት፤
በእጆችሽ ዳበሳ፣
በከንፈር ቀመሳ።
በጣት መነካካት፣
አፍንጫ መለካት።
ከዛ ደሞ መሳቅ፣
ከአይኔ ለመራቅ።
ከዛ ደሞ ማፈር፣
ሽጉጥ አንገቴ ስር።
በፍቅርሽ ........ም፣
እል.............................ም፣
እል.............................ም፣
እል.............................ም፣
ወዲያ ወደ ጥልቁ ወደ ፍቅርሽ አለም፡፡

እሰ...............ይ፤
እሰ...............ይ፤
እሰ...............ይ፤
ሽንቅጥቅጥ ዘመናይ፣
ቁጥብ አሳ መሳይ፤
አደብ አስገዢልኝ
ሽርክቱ አመሌን፣
እንደ ፀደይ ልፍካ
ደባብሺው አካሌን፡፡
ያድነኝ የሰራሽ
ከነፍስሽ ላይ ቆርሶ፣
ልጠግን መንፈሴን
ካንቺ ላይ ተገምሶ፡፡

እኔ.......፤
በስሉስ ተክኜ፤
ለሳቅሽ መንኜ፤
ዳማ ፈረስ ጭኜ፤
ሽምጥ መጋለብ፣
ሳቢ ደረትሽ ላይ፤
ድንግል መሬትሽ ላይ፤
ሰንደቄን ማውለብለብ፡፡

ግልብ
ጋለብ
ብትን
ስብስብ
ያዝ
ለቀቅ
ጋለል
ንቅንቅ
ልጓም
ንጥቅ
ጦሬን
ነቅነቅ
እልም
ውርውር
አንገት
ስብር
ናጥ
በጥበጥ
እፍር
ቅብጥ
ጨምቅ
ቁንጥጥ
እሽት
ጭብጥ
እቅፍ
ቧጠጥ
ስንን
ሰክን
ስፍስፍ
ጥንን
ፍትት
ጥግን
ፈንቀል
ጀነን
በላብ
ስጥም
ሳቋ
ሲጥም
.
.
ሳም
ንክስ
ብትን
ቅስስ
ጭልጥ
መለስ፣
ሳብ
ግፍትር
ለስለስ
ግትር፡፡
ጎንበስ
ቀና
ፍርት
ዘና
ከዛ ተንፈስ
ሻጥ መለስ
እንደገና፡፡
.
.
የእግዜር መና።

አይይይ ቁንጅና!

አቤት ውበት፤
ሴት የሆነ የሴት ገላ፣
የሚመጠጥ ማር ወለላ።
መቃ መሳይ ያንገት ማኛ፣
መለስለሷ ማያስተኛ።
በየት በኩል በየት ገና፣
አንገቱዋ ስር ትኩስ ዳና።
ደረቱዋ ላይ መጋል ፍሬ፣
ነዳፊ ንብ ጥርኝ አውሬ፣
ትላንት ናፍቆት ምን ነሽ ዛሬ?

መጠንሰሻ የዳማ ምንጭ፣
የመሰንበት የመኖር ፍንጭ፣
ጡቷ ግድም ጥቁር ነጥብ፣
ፍም ትንፋሽዋ የሚያስጥም።
ሴት አካሏ ምትሃተኛ፣
መልኳ ድርብ የመልከኛ።
ልዝብ ሳቋ የሚደረጅ፣
መዓዛዋም የደብር ደጅ።

እይት
ሰረቅ
ዳሌ
ነቅነቅ
ጥርስ
ገለጥ
ጥብብ
መሰጥ
ከላይ
ረጋ
ከታች
ጠጋ
አይን
ጭፍን
ድርብ
ሽፍን
ብትን
ብትን
ደሞ
ስብስብ
እቅፍ
እስብ
ትንፋሽ
ስርቅ
ልብ
ድልቅ
ጉስም
ጉስም
ግርሽት
ድፍርስ
ፀጉር
ነስነስ
.
.
"ኸረ ቀስ"
"ኸረ ቀስ"
.
.
ሶስቴ
መሄድ
ለመመለስ።
.
.
ዘራፍ ወንዱ......!!!


✍️ ዓቢይ ( @abiye12 )


@getem
@getem
@getem
👍5820🔥18😱9🤩7👎2