መልካም ልደት
የእናትነት በጎ ክብር ምስጢረኛ አለኝታዬ
የሕይወቴ ታላቅ ቀመር
መልካም ልደት እናትዬ
እናቴ? ………የኔ ፀጋ
በልቤ ውስጥ ያለሽ ዋጋ
፡
ዐይኔን በዐይኔ የማይብሽ
ጓደኛዬ አለችምላት
ጎዶሎየን ምሞላብሽ
የጉዞዬ ድጋፍ ምርኩዝ አንችኮ ነሽ።
፡
እማ
የኔ ስጦታ የአ ም' ላ' ክ በረከቴ
ኑሮ ይድላሽ ክፉሽን አያሳየኝ በሕይወቴ
ልመርቅሽ??
፡
ቀሪው ዘመን
ጤና ይሁን የተሟላ
እድሜሽን ያድርግልኝ ማቱሳላ
፡
የአምላክ እናት ትጠብቅሽ
ከፊት ቀድማ ከኋላሽም ተከትላ።
መልካም ልደት እናቴ
በይክቤ
@getem
@getem
@getem
የእናትነት በጎ ክብር ምስጢረኛ አለኝታዬ
የሕይወቴ ታላቅ ቀመር
መልካም ልደት እናትዬ
እናቴ? ………የኔ ፀጋ
በልቤ ውስጥ ያለሽ ዋጋ
፡
ዐይኔን በዐይኔ የማይብሽ
ጓደኛዬ አለችምላት
ጎዶሎየን ምሞላብሽ
የጉዞዬ ድጋፍ ምርኩዝ አንችኮ ነሽ።
፡
እማ
የኔ ስጦታ የአ ም' ላ' ክ በረከቴ
ኑሮ ይድላሽ ክፉሽን አያሳየኝ በሕይወቴ
ልመርቅሽ??
፡
ቀሪው ዘመን
ጤና ይሁን የተሟላ
እድሜሽን ያድርግልኝ ማቱሳላ
፡
የአምላክ እናት ትጠብቅሽ
ከፊት ቀድማ ከኋላሽም ተከትላ።
መልካም ልደት እናቴ
በይክቤ
@getem
@getem
@getem
❤57👍35🤩2🔥1
====+====
ለደግነቷ ምላሽ
ሳትጠብቅ፤
የልቧን ፍቅር
ካይኗ ሳትደብቅ፤
:
የአንጀቷን ሲቃ
ዜማ ለምቀኝ ፤
ያሳለፍኩትን
ሳትጠይቀኝ።
ፍርሃቴን አስራ
ድሌን ስትፈታ፤
አንዴም ሳትቆጥረው
እንደ ውለታ ።
:
እያሳመምኳት
እያዳነቺኝ፥
እየገፋኋት
እያቀፈቺኝ፤
እሷን የሚመስል ላላገኝ የትም፤
የሚገባትን ፡ አልሰጠዋትም!
© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
ለደግነቷ ምላሽ
ሳትጠብቅ፤
የልቧን ፍቅር
ካይኗ ሳትደብቅ፤
:
የአንጀቷን ሲቃ
ዜማ ለምቀኝ ፤
ያሳለፍኩትን
ሳትጠይቀኝ።
ፍርሃቴን አስራ
ድሌን ስትፈታ፤
አንዴም ሳትቆጥረው
እንደ ውለታ ።
:
እያሳመምኳት
እያዳነቺኝ፥
እየገፋኋት
እያቀፈቺኝ፤
እሷን የሚመስል ላላገኝ የትም፤
የሚገባትን ፡ አልሰጠዋትም!
© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
❤41👍22😢4🔥3
ዛሬ፣ ደስ! የሚል ቀን ነው። ሐዘን በወረረን ግዜ፣ እንደ ተወርዋሪ ኮከብ፣ ደስታ ብቅ ሲል ያስደስታል። ከሳምንታት በፊት፣ ለመቶ ገጣሚያን መድብል ለማዘጋጀት ጥሪ ቀርቦ ነበር፤ እነሆ፣ እኔም በዚህ ጥሪ ተሳታፊ ሆኜ፣ በዛሬው እለት ከመጀመሪያዎቹ ቅፅ-1(ክንፋም ከዋክብት መድብል )ማለትም ከ50 ገጣሚያን አንዱ መሆኔን መልዕክት ደርሶኛል። እናም እጅግ ደስ ብሎኛል!
ልክ ይልማ ገ/አብ የመጀመሪያ የዘፈኑ ግጥም ከሳንሱር አድራጊዎቹ አልፏል፤ ሲባል የተሰማው ደስታ ሲገልፀው:-
' በየመንገዱ በምሄድበት ግዜ ከደስታዬ ብዛት የተጣላሁትን ሰው ባገኝ የማናግር ይመስለኛል' ብሎ ነበር። እኔም፣ ያቺ ስሜት ተሰማችኝ።
በመጨረሻም ፣ የግጥም መድብሉን የመግዛት ፍላጎት ያላቹ ወዳጆቼ
በ #inbox 👇
@Samuelalemu5 አናግሩኝ።
አመሰግናለሁ🙏
@Samuelalemuu
@getem
@getem
ልክ ይልማ ገ/አብ የመጀመሪያ የዘፈኑ ግጥም ከሳንሱር አድራጊዎቹ አልፏል፤ ሲባል የተሰማው ደስታ ሲገልፀው:-
' በየመንገዱ በምሄድበት ግዜ ከደስታዬ ብዛት የተጣላሁትን ሰው ባገኝ የማናግር ይመስለኛል' ብሎ ነበር። እኔም፣ ያቺ ስሜት ተሰማችኝ።
በመጨረሻም ፣ የግጥም መድብሉን የመግዛት ፍላጎት ያላቹ ወዳጆቼ
በ #inbox 👇
@Samuelalemu5 አናግሩኝ።
አመሰግናለሁ🙏
@Samuelalemuu
@getem
@getem
👍27🤩26❤7🎉6
[ድፍን ድርሰት]
🌍
____
¹
ትልሙንና ህልሙን —···
(በመቼት በሴራ) እያጠላለፈው ፤
ወጉን ትረካውን (በቀናቶች ክፍል)
(በገፁ በአንቀፁ) እየሸራረፈው ፤
ዓለምን በቃሉ....
(በፈጠራው ቀለም) ነክሮ የነደፈው
ደራሲው ፈጣሪ (ስለሁለታችን)
ስለ እኔ ስላንቺ — ምን ይሆን የፃፈው?
²
አፈር ከሞላበት (አመድ ከለበሰው)
(ከመጣው ከሄደው) ከተመላለሰው
ከአምና ከዘንድሮ (ከዛሬ ከድሮ)
የተከመረውን (ጥራዝ እያወጡ )
(ሕይወትን ዘርግተው) ቢገልጡ ቢገልጡ ፤
የእግዜር ድፍን ድርሰት አይገኝም ጭብጡ ።
³
(“አትመጪም ወይ?” ስልሽ...)
—··· “እመጣለሁ” ብትይ ፤
(ለመንገድ የሚሆን....)
—··· ስንቅ ብታስከትይ ፤
ልብሽ ቢሰናዳ —·· እግርሽ ቢበረታ፤
(የጎዳናው ቀያሽ የመንገዱ ጌታ....)
ደራሲው ፈጣሪ — ·· የመቼት የቦታ ፤
ምን እንደሚበጥስ
ምን እንደሚቀጥል...
ማንን እያነሳ
ማንን እንደ ሚጥል....
አውቄው አላውቅም ገምቼው ቀድሜ
የታል ስለ ነገ ፍፁም ድምዳሜ?
ስንት ነው በምድር የተሰጠኝ ዕድሜ?
⁴
(ማን ይሄን አወቀ? አሁንስ ማን ያውቃል‽)
“እመነኝ” ብትይኝ አፍሽ ቢያወጣ ቃል ፤
(ጠዋት "ለምለም" ያልነው
ባመሻሽ ይደርቃል)
ስውር ደራሲያችን የላይኛው አካል
ነባሩን ቀይሮ አዲስ ይተርካል ።
ይለየን ይሆናል...
(ያርቀን ይሆናል) በጊዜ – በቦታ ፤
ከቃል የበለጠ — ጌታ ነው “ሁኔታ” ።
(ይሆኑታል እንጂ...)
ይኖሩታል እንጂ ....
“ይግባኝ” አይባልም — እንዲህ ያለ ፍርጃ
አንቺን አምንሻለሁ — እግዜሩን ግን እንጃ ።
___
🌍
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
🌍
____
¹
ትልሙንና ህልሙን —···
(በመቼት በሴራ) እያጠላለፈው ፤
ወጉን ትረካውን (በቀናቶች ክፍል)
(በገፁ በአንቀፁ) እየሸራረፈው ፤
ዓለምን በቃሉ....
(በፈጠራው ቀለም) ነክሮ የነደፈው
ደራሲው ፈጣሪ (ስለሁለታችን)
ስለ እኔ ስላንቺ — ምን ይሆን የፃፈው?
²
አፈር ከሞላበት (አመድ ከለበሰው)
(ከመጣው ከሄደው) ከተመላለሰው
ከአምና ከዘንድሮ (ከዛሬ ከድሮ)
የተከመረውን (ጥራዝ እያወጡ )
(ሕይወትን ዘርግተው) ቢገልጡ ቢገልጡ ፤
የእግዜር ድፍን ድርሰት አይገኝም ጭብጡ ።
³
(“አትመጪም ወይ?” ስልሽ...)
—··· “እመጣለሁ” ብትይ ፤
(ለመንገድ የሚሆን....)
—··· ስንቅ ብታስከትይ ፤
ልብሽ ቢሰናዳ —·· እግርሽ ቢበረታ፤
(የጎዳናው ቀያሽ የመንገዱ ጌታ....)
ደራሲው ፈጣሪ — ·· የመቼት የቦታ ፤
ምን እንደሚበጥስ
ምን እንደሚቀጥል...
ማንን እያነሳ
ማንን እንደ ሚጥል....
አውቄው አላውቅም ገምቼው ቀድሜ
የታል ስለ ነገ ፍፁም ድምዳሜ?
ስንት ነው በምድር የተሰጠኝ ዕድሜ?
⁴
(ማን ይሄን አወቀ? አሁንስ ማን ያውቃል‽)
“እመነኝ” ብትይኝ አፍሽ ቢያወጣ ቃል ፤
(ጠዋት "ለምለም" ያልነው
ባመሻሽ ይደርቃል)
ስውር ደራሲያችን የላይኛው አካል
ነባሩን ቀይሮ አዲስ ይተርካል ።
ይለየን ይሆናል...
(ያርቀን ይሆናል) በጊዜ – በቦታ ፤
ከቃል የበለጠ — ጌታ ነው “ሁኔታ” ።
(ይሆኑታል እንጂ...)
ይኖሩታል እንጂ ....
“ይግባኝ” አይባልም — እንዲህ ያለ ፍርጃ
አንቺን አምንሻለሁ — እግዜሩን ግን እንጃ ።
___
🌍
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
👍50❤6🔥2😢1
⌚️ በቀጣይ List የሚደረጉ ፕሮጀክቶች 👇👇👇 ትንሽ ጊዜ ነው ያላችሁ!
1, MAJOR ⭐ https://tttttt.me/major/start?startapp=366765955
2, BLUM🤢
https://tttttt.me/blum/app?startapp=ref_4AQg09PDzR
2,CATS 🐈
t.me/catsgang_bot/join?startapp=dMdTmv--6IkmR-lKi1dWy
3, X-EMPIRE 🔥
https://tttttt.me/empirebot/game?startapp=hero454803628
5,HAMSTER COMBAT 🐀
https://tttttt.me/hamster_Kombat_bot/start?startapp=kentId454803628
6,HRUMME 💥
t.me/hrummebot/game?startapp=ref454803628
ለሌሎችም ያጋሩ!
1, MAJOR ⭐ https://tttttt.me/major/start?startapp=366765955
2, BLUM🤢
https://tttttt.me/blum/app?startapp=ref_4AQg09PDzR
2,CATS 🐈
t.me/catsgang_bot/join?startapp=dMdTmv--6IkmR-lKi1dWy
3, X-EMPIRE 🔥
https://tttttt.me/empirebot/game?startapp=hero454803628
5,HAMSTER COMBAT 🐀
https://tttttt.me/hamster_Kombat_bot/start?startapp=kentId454803628
6,HRUMME 💥
t.me/hrummebot/game?startapp=ref454803628
ለሌሎችም ያጋሩ!
Telegram
Major
Become a Major of Telegram. Climb higher in rating based on your balance. Play Games and earn points.
👍6❤1
Forwarded from Sami Alemu
ጧሪ ያጣ አሜን
(ሳሙኤል አለሙ)
ለቁርሱ---ለምሳው---ለእራቱ
አፋችን ባይነቅዝም
"ካ'መት ዓመት ያድረሰን"
ሲባል ጭጭ!
ሲባል ዝም!
"እ'ዲሁ እንዳለን አይለየን"
ሲባል ጭጭ!
ሲባል ዝም!
ዕድሜያችን አጠረ ፥ ዝምታው ሲረዝም።
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@Getem
@Getem
(ሳሙኤል አለሙ)
ለቁርሱ---ለምሳው---ለእራቱ
አፋችን ባይነቅዝም
"ካ'መት ዓመት ያድረሰን"
ሲባል ጭጭ!
ሲባል ዝም!
"እ'ዲሁ እንዳለን አይለየን"
ሲባል ጭጭ!
ሲባል ዝም!
ዕድሜያችን አጠረ ፥ ዝምታው ሲረዝም።
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@Getem
@Getem
❤34👍14😢10
ብንላመድ ተቀራርበን ብናወራ እጅግ በጣም፤
ብንስማም እንደአንድ ወግ ጨዋታን ብናበዛም፤
ቢያስደስተኝ ካንቺ መዋል ሳቅ ጨዋታሽ ቢገዛኝም።
ብትጠጊኝ ከቆምሽበት አንድ እርምጃ ወደ'ኔ፤
ብትማትሪም ከልቤ ላይ የፍቅርን ቃል ሆነሽ ጎኔ።
ብለምድሽም እንደራሴ ብትወጅኝም አንቺ በጣም፤
እኔ መቼ ታድዬልሽ ለማጣጣም የፍቅርን ጣ'ም።
እኔ መቼ ልረ'ዳልሽ መች ሊገባው የልቤን በር፤
ፍራት አስሮ እየናጠኝ መች ልከትም ከፍቅር መንደር።
መች ልደርስ ከደጃፉ የት አውቄ ልቀበልሽ?፤
በየት ጎዳና ባንቺ ስሜት እንዴት ሄጄ ልከተልሽ?።
ላልጨርሰው ጀማምሬ ከምጎዳሽ በአጉል ተስፋ፤
ልቤ ደርሶ ከልብሽ ላይ በፍቅር ክር ላይሰፋ።
የተዘጋው የልቤ በር አይከፈት እኔ አውቃለሁ፤
ፍቅር ነው አትበይኝ እኔ ፍቅር እፈራለሁ።
✍ ጦቢያ
...............................
@getem
@getem
@getem
ብንስማም እንደአንድ ወግ ጨዋታን ብናበዛም፤
ቢያስደስተኝ ካንቺ መዋል ሳቅ ጨዋታሽ ቢገዛኝም።
ብትጠጊኝ ከቆምሽበት አንድ እርምጃ ወደ'ኔ፤
ብትማትሪም ከልቤ ላይ የፍቅርን ቃል ሆነሽ ጎኔ።
ብለምድሽም እንደራሴ ብትወጅኝም አንቺ በጣም፤
እኔ መቼ ታድዬልሽ ለማጣጣም የፍቅርን ጣ'ም።
እኔ መቼ ልረ'ዳልሽ መች ሊገባው የልቤን በር፤
ፍራት አስሮ እየናጠኝ መች ልከትም ከፍቅር መንደር።
መች ልደርስ ከደጃፉ የት አውቄ ልቀበልሽ?፤
በየት ጎዳና ባንቺ ስሜት እንዴት ሄጄ ልከተልሽ?።
ላልጨርሰው ጀማምሬ ከምጎዳሽ በአጉል ተስፋ፤
ልቤ ደርሶ ከልብሽ ላይ በፍቅር ክር ላይሰፋ።
የተዘጋው የልቤ በር አይከፈት እኔ አውቃለሁ፤
ፍቅር ነው አትበይኝ እኔ ፍቅር እፈራለሁ።
✍ ጦቢያ
...............................
@getem
@getem
@getem
❤48👍31😢19👎2🔥2
———————- ደረሰ ——————
ሰሞኑን በአዲስ ዓመት ዋዜማ ከምንጠብቃቸው የጥበብ ድግሶች አንዱ የሆነው ብዙ አንጋፋ እና ወጣት የጥበብ ሰዎች የተሳተፉበት የደራሲ እና ኢንጅነር ሚካእኤል አስጨናቂ መፅሀፍ ምርቃት ነገ ዕለተ አርብ አራት ኪሎ ከቱሪስት ሆቴል ጀርባ በሚገኘው ኢ ክላስ ህንፃ ዋልያ መፅሀፍት አዳራሽ ሞቅ ደመቅ ባለ ፕሮግራሞቹ ታጅቦ ደምቆ የሚውል ይሆናል ።
👉🏿 ይሄ ከ 10 ሰዓት ተኩል አንስቶ የሚቀርበው የአዕጋረ ፀሀይ መፅሀፍ ምረቃ
> ግጥምን በጃዝ ፣
> ሙዚቃ ፣
> ስዕል እና የመፅሀፏ ዳሰሳዎች የሚስተናገዱበት መድረክ ይሆናል ።
👉🏿 መሶብ ባንዶች በዓሉን ያደምቁታል ።
በሀገራችን ወግ እና ባህል መሰረት ቡናው ፣ ፋንዲሻው ፏ ብሎ የአዲስ ዓመት መምጣትን የሚያበስር ነገሪት ይጎስማል።
የቻሌንጅ አሸናፊዎች ደጎስ ያለ ሽልማታቸውን ይቀበላሉ። ጥበባዊ ለዛ ያለው ድባብ ይኖራል ።
👉🏿 መግቢያው ፍቅር እና መውጫው ክብር የሆነበት የማይቀርበት ድግስ እነሆ ለእናንተ ተብላችኋል ቤተሰቦች።
@getem
@getem
@getem
ሰሞኑን በአዲስ ዓመት ዋዜማ ከምንጠብቃቸው የጥበብ ድግሶች አንዱ የሆነው ብዙ አንጋፋ እና ወጣት የጥበብ ሰዎች የተሳተፉበት የደራሲ እና ኢንጅነር ሚካእኤል አስጨናቂ መፅሀፍ ምርቃት ነገ ዕለተ አርብ አራት ኪሎ ከቱሪስት ሆቴል ጀርባ በሚገኘው ኢ ክላስ ህንፃ ዋልያ መፅሀፍት አዳራሽ ሞቅ ደመቅ ባለ ፕሮግራሞቹ ታጅቦ ደምቆ የሚውል ይሆናል ።
👉🏿 ይሄ ከ 10 ሰዓት ተኩል አንስቶ የሚቀርበው የአዕጋረ ፀሀይ መፅሀፍ ምረቃ
> ግጥምን በጃዝ ፣
> ሙዚቃ ፣
> ስዕል እና የመፅሀፏ ዳሰሳዎች የሚስተናገዱበት መድረክ ይሆናል ።
👉🏿 መሶብ ባንዶች በዓሉን ያደምቁታል ።
በሀገራችን ወግ እና ባህል መሰረት ቡናው ፣ ፋንዲሻው ፏ ብሎ የአዲስ ዓመት መምጣትን የሚያበስር ነገሪት ይጎስማል።
የቻሌንጅ አሸናፊዎች ደጎስ ያለ ሽልማታቸውን ይቀበላሉ። ጥበባዊ ለዛ ያለው ድባብ ይኖራል ።
👉🏿 መግቢያው ፍቅር እና መውጫው ክብር የሆነበት የማይቀርበት ድግስ እነሆ ለእናንተ ተብላችኋል ቤተሰቦች።
@getem
@getem
@getem
👍20🎉15❤4🔥3👎1
"ትንሽ ቦታ"
ስሜታዊ ሆኖ ለተናገረን ፣ ሊረዳን ፈልጎ ለሳተ ፣ ኑሮ አስክሮት ለገፋን ፣ ንዴት ገፍቶት ላጠፋ ፣ ግዜ አጣሁ ብሎ ላልጎበኘን ፣ ስናሸንፍ ላላጨበጨበ፣ ስንወድቅ ላላነሳን ፣ ስናስብለት ላልተረዳን ፣ ማደጋችንን ላላየ ፦
"ትንሽ ቦታ ለይቅርታ" አኑረናል
አማረልን ብለን ላሳዘንን ፣ አጉል ተስፋ ለሰጠነው ፣ ውድቀት ላይ ለሳቅነው ፣ ብልግናን ላጎላናው ፣ ድድብናን ላነፈስነው ፣ ማድረግ ችለን ላላደረግነው ፣ ችለን ለተጣመምነው ።
ለራሳችን ይቅርታ አደርገናል...
ቺርስ ለአዲስ ዘመን
ቺርስ ለተስፋችን
ቺርስ❤🙏.
By Adhanom Mitiku
@getem
@getem
@paappii
ስሜታዊ ሆኖ ለተናገረን ፣ ሊረዳን ፈልጎ ለሳተ ፣ ኑሮ አስክሮት ለገፋን ፣ ንዴት ገፍቶት ላጠፋ ፣ ግዜ አጣሁ ብሎ ላልጎበኘን ፣ ስናሸንፍ ላላጨበጨበ፣ ስንወድቅ ላላነሳን ፣ ስናስብለት ላልተረዳን ፣ ማደጋችንን ላላየ ፦
"ትንሽ ቦታ ለይቅርታ" አኑረናል
አማረልን ብለን ላሳዘንን ፣ አጉል ተስፋ ለሰጠነው ፣ ውድቀት ላይ ለሳቅነው ፣ ብልግናን ላጎላናው ፣ ድድብናን ላነፈስነው ፣ ማድረግ ችለን ላላደረግነው ፣ ችለን ለተጣመምነው ።
ለራሳችን ይቅርታ አደርገናል...
ቺርስ ለአዲስ ዘመን
ቺርስ ለተስፋችን
ቺርስ❤🙏.
By Adhanom Mitiku
@getem
@getem
@paappii
❤41👍27🔥1