ግጥም ብቻ 📘
67.3K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
175 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
ላያኖሩህ ሲንጫጩብህ
ጆሮ ሰተህ አትስማቸው
በፀጥታ ተጓዝ ገስግስ
ያቆማሉ ሲደክማቸው
.
በሰው ኑሮ ሲያንቧችሩ
የራሳቸው የጠፋቸው
በድን ስጋን ያዘሉ
ኗሪ ነን ባይ ሙታን ናቸው
.
ከሞተ ጋር ግብግቡ
ምን ሊጠቅም? ምን ሊያመጣ?
አንገትህን ደፍተህ ቀጥል
ያለምከው ቀን እስኪመጣ

በ ኪሩቤል አሰፋ  @Ebuh_bhr

@getem
@getem
@paappii
43👍30🔥4🎉3🤩3
ደርሶ

ያለ ክስ  ያለ ዳኛ
ያለ ፍርድ  ደርሶ እስረኛ
ወታደር ሳይኖር  ደርሶ መማረክ
አስገዳጅ ሳይኖር  ደርሶ መንበርከክ
ዘራፊ ሳይኖር  መሰረቅ ደስታ
ደርሶ መታመም  ሳይኖር በሽታ
ጠበቃ ሳይኖር  ፈራጅም ዳኛ
ማረሚያ ሳይገቡ  የቁም እስረኛ
እራስን ሰጥቶ  ማንነት ማጣት
ደርሶ መኮነን  ሳያጠፉ ቅጣት
ቅኔው የማይገባ  ሰም እና ወርቁ
የስሜት ጋጋታ   እየተፈራረቁ
ከሌላ አድሮ  ፈቅዶ መታፈን
ደርሶ መቃጠል  በእሳት ወላፈን

By @poem2513

@getem
@getem
@getem
👍569🔥4🤩2
ስረቅ!
ንጠቅ!
ዝረፍ!
ግረፍ!

ክፉ ሀሳብ
ነፍሴን ሊቀጭ ውስጤን ሲያምስ፣
#ስዕልሽ ፊት
ላፍታ ብቆም ጥፋት እብስ!

ተንኮል ወሮኝ
ቅጥፈት ባህር ሊዘፍቀኝ ሲል፣
#ተአምርሽን
ድንገት ባስብ ጋኔል ቅጥል!

እርጉም ሀሴት
ሊያሳፍሰኝ ከሴት ጭን ስር፣
እርኩስ ስሜት በደል ሲጭር፤
#ውዳሴሽን
ገልጬ ባይ ሰይጣን እርር!

ውድቀት ጠርቶኝ
ክፋት አንቆኝ በኃጢአት ስዋጥ፣
#ማር_ስምሽን
ልክ ስጠራ ዲያቢሎስ ላጥ!

ኃጢአት ጦሩን
ሲሰድ ሰብቆ በጥላቻ፣
#ጋሻዬ ነሽ
#ድንግል_ማርያም
ያጋንንትን መርዝ መግቻ።

#ኤልዳን
@eldan29

@getem
@getem
@getem
103👍32🎉3👎2🔥2
ምን ያክል አጠፋሽ ?

አንቺ ያላውቅሽው  ምን ያክል አጠፋሽ
በንፁህ ልብ ላይ  እዳፊሽን ደፋሽ
ከሳቂታ ፊት ላይ  ፈገግታን አጠፋሽ


አንቺ ልብ ያላልሽው  ስንት አበባ ደረቀ
ስንት አበባ ረገፈ
ከቁብ ያልቆጠርሽ  የስንቱ ሞራል ተገፈፈ
ህልሙ ጨነገፈ

ምን ያክል አጠፋሽ ?


አንቺ ያላውቅሽው ምን ያክል አሳመምሽ 
ምን ያክልስ ገደልሽ
ማመን የሚችልን  ማፍቀር የሚችልን
ስንት ልብ አጎደልሽ
.........................ስንት ልብ አበደንሽ

ምን ያክል አጠፋሽ ?

በድን ያደረግሽው  ነፍሱን የነጠቅሽው
በመጠን ካወቅሽው
ምን ያክል አጠፋሽ  በየትኛው ልኬት
በምንስ ሰፈርሽው

ምን ያክል አጠፋሽ ?


ያንችን ሳቅ  ያንችን ጨፋታ ያንችን እብደት
ስንት ልብ አለመ ? 
           ስ
              ን
                 ት ልብ ከሰመ ?
ከእሷ ውጭ እያለ   የመውደድ የማፍቀር
ተስፋው አከተመ


ምን ያክል አጠፋሽ ?

By @poem2513

@getem
@getem
@getem
30👍19😢8🔥2
ዝምታ ሲደመጥ

አቤት! ጩኸቱ ዝምታ
ጆሮ ጠልዞ ናላ ሲመታ
ከወዲያ ወዲህ ሲያላጋ
በሞገዱ ቋጥኝ ሲያናጋ
ነጎድጓድ ነው ነው ዝምታ
የገዛ ራስ ጉርምርምታ
የደምን ፋፋቴ ጉዘት
የልብን ህይወታዊ ዑደት
እንደጢስ አባይ ፏፏቴ ቅኝት
ሰማይ ሰቅሎ ዶሎ አዘቅት
ያኖጋዋል ሲያዳምጡት
በሁካታ ዉስጥን ሞልቶ
በፀጥታ ነፍስ ዘርቶ
ከአፅናፍ አፅናፍ አስተጋብቶ
እንኳንማ ጆሮ ቀርቶ
ይደመጣል ባይን ገብቶ
ነጎድጓድ ነው ዝምታ
የገዛ ራስ ጉርምርምታ
እንዳፍላ ጎርፍ ይነደፋል
ሳይቀዝፍ ያጓጉዛል
ታገር አገር ያዘልላል
ማሚቶ አለዉ ይመልሳል
ነጎድጓዱ ዝምታ
የገዛ ራስ ጉርምርምታ።

@topazionnn
@getem
@getem
👍509🤩4😢1🎉1
ለምሠራው መልአክ
።።።።።።።።።።።።።።
ካንቺ ላይ ቆንጥሬ
የሆነች በጎነት
ከልቤ ገነት ውስጥ ባዲስ በመፍጠሬ
ቀዬው በተደሞ
ሲነጋገር ቀድሞ
ዝም እግዜርሽ ደግሞ!

ካንቺ ላይ ቀንሼ
የሆነች ፈገግታ
እርቃኗን እንዳለች ፊቴ ላይ ነስንሼ
(በሳቅ በመቆሜ)
ቀዬው በፈገግታ ሲነጋገር ቀድሞ
ፀጥ እግዜሬ ደግሞ!

ካንቺ ላይ ወስጄ
የሆነች ጨዋነት
ስድ ገላዬ ላይ እንደ ልብስ ገድግጄ
(ክብሬን በማወጄ)
ምድር በትህትና
ሲያወራ እንደገና
ዝም፣ የግዜር ፅሞና!

እንዲ እየሸረፍኩሽ
እኔና ትናንቴ ባዲስ ክብር ገነናል።
እግዜር ከፅሞናው
አንቺን ልጁን ሲያጣሽ ይናገር ይሆናል
በሚል ጅምር ተስፋ
ካንቺ እየቀነስኩኝ ወደኔ ሳከማች
አንዲት ቃል ተሰማች
"ሁሉን መውሰድ ለካ ይቀለዋል ለሟች።"

አጥቻለሁና
ባንቺ እየቀባባሁ የነተበ መልኬን
ከሞቴ ተኝተሽ ውለጂው መልአኬን።

@getem
@getem
@paappii

#Yadel Tizazu
👍3722😢2
እውነት እውነት ልጁ ያምራል
ያለእንከን ይወደዳል
ሰላም ያለው እርግት ያለ
መልክ ቁመት የታደለ
በፈገግታው ገዳይ ሁሉን
ግርማሞገስ ገላጭ ቃሉን
ደሞ ጎበዝ ደሞ አስተዋይ
ቢገለውስ ይፈረዳል በ ቃየል ላይ?

ተፃፈ በ Le ለ Abel

@getem
@getem
@paappii
👍28😢93🤩1
አስታወሼ እኮ ነው
ስጠፋ ሚጨነቅ ስሸሸው ናፋቂ
በቀን ሶስት አራቴ አጥብቆ ጠያቂ
ማጣቴን ማይሻ ሲያልፍልኝ ደስተኛ
ስቸገር ስከፋ አለው ባይ መፅናኛ
ኖሮት የማይሰስት እጁን ሚዘረጋ
አለውልህ ባዬ በመሸ በነጋ
.
ለበዓል ስጦታ አስታውሶ ለጋሼ
ስንቱን ያሳለፍኩት እርሱን ተተርሼ
ቃላት የማይገልፁት ከቶ ማይተረጎም
ውለታው ብዙ ነው ኢትዮ-ቴሌኮም


ላንተ ቃል የለኝም.....በተለይ 810🫶

በኪሩቤል አሰፋ   @Ebuh_bhr

@getem
@getem
@getem
😁120👍3214🤩10🔥1
ተለያይተን ፡ አይደል ? ተጣልተሽኝ ፡ የለ ?

ቀኑን ፡ ባላስብሽ ፡ በህልሜ ፡ ባትመጪ ፡ምን አለ ?

ትዝ ፡ እያልሽኝ ፡ ሁሌ ፡ ከአጥንቴ ፡ በቀር ፡ ስጋዬስ ፡ የታለ ?

ቀልቤስ ፡ ቢሆን ፡ የታል ? በድኑን ፡ ለእኔ ትቶ ፡ ካንቺጋ ፡ እየዋለ ፣

አላሳዝንሽም ? ትወድጅኝ ፡አልነበር ? ትንገበገቢልኝ ?

ላላገኝሽ ፡ ነገር ፡ ባንቺ ፡ እንዲህ ስሰቃይ ፡ ምናለ ፡ ብተይኝ ?

በምሰማው ፡ ደምፅ ፡ በማየው ፡ መልክ ሁሉ ፡ የምትታወሺኝ ?

በህልሜም ፡ በእውኔም ፡ ካላንቺ : የማላውቅ ፡ ሌላ ፡ ማይታየኝ ፣

አዋቂ ፡ ጋር ፡ ሄድሽ ፡ ወይ ? የኔታን ፡ አማከርሽ ፡ ያኔ ፡ እንደዛትሽብኝ ?

ተለያይተን ፡ አይደል ? ተጣልተሽኝ ፡ የለ ?
ባክሽ ፡ አትናፍቂኝ ፣

ከሰው ፡ አለያይተሽ ፡ ከፍጥረት ፡ ነጥለሽ ለብቻ ፡ አታዉይኝ ፣

አጥቼሽም ፡ ቢሆን ፡ ባክሽ ፡ ልኑርበት ፡  አትፈታተኚኝ ።

                 ዘረ ሠናይ
             @Prince_zeresenay

@getem
@getem
@paappii
62👍46😢23😁5👎4🤩2
(የሚያደበዝዘው..)
==============

የትናንቱን ዝናብ
ያመሰግናል ሰው ሰማይ ስላጠራ
ምን ነበር ባየልኝ
ቤቴን እንደናደው ጎርፉ ሆኖ መከራ

ምናል ሰው ደስታውን
ለልቡ ለራሱ አምቆ ቢይዘው
ያንዱ መድመቂያ ነው
የሌላኛውን ቤት የሚያደበዝዘው

@kiyorna

መነሻ: The last breath " Japanese Movie on storm"

@getem
@getem
@paappii
58👍31🔥3👎1🤩1
ጌጤ እና ሽጉጤ ቀናቸው ነው ዛሬ
ሲባባሉ ያድራሉ ሀኒ፣ ቤቢ ፍቅሬ
ጌጤም በመልኳ ላይ ሜካፗን ለቅልቃ
ችሎ ያኖራትን ሺቲዋን አውልቃ
የእራት ልብሷን ለብሳ ቀጭ ቋ እያለች
ከሽጉጤ ዕቅፍ ጠልቃ ትገባለች
.
ሽጉዬም ላመሉ ፀጉሩን አስፈርዞ
የኪራይ ሱፍ ኮቱን በእጁ ላይ ይዞ
እንደ ውጪዎቹ አበባ አንጠልጥሎ
ለአንድ ቀንም ቢሆን ድህነቱን ጥሎ
ቀፍሎ ባመጣው ኪሱን አሳብጦ
ጌጥዬን እያየ ይበላል አማርጦ
.
ተበላ ተጠጣ ፍቅራቸው ነደደ
ገና ነው እያሉ ሰዓቱ እረፈደ
በፍቅራዊ ቃና እየተገፋፉ
ለሊቱን አነጉት አልጋ ሲያነጥፉ
ለስራቸው ጥራት ለድካም ወዛቸው
ከወራት በኃላ ደሞዝ ደረሳቸው

ዘንድሮም ጠንክራቹ ስሩ💪


በኪሩቤል አሰፋ @Ebuh_bhr

@getem
@getem
@getem
😁102👍4423👎5🤩5🎉1
እርዕስ ስጡት!

በለበስኩት ልብስ ተመን ስታወጪ
ከኋላዬ ሆነሽ ማይሆን ስም ስትሰጪ

በገንዘብ ተታለሽ ፍቅርን ስታጪ
በዝና ተውጠሽ ባህር ውስጥ ስትሰምጪ

ታዲያ ከአሁን ወዲህ እዚህ እንዳትመጪ
ልምከርሽ ውድዬ ምንም ሳታወጪ

ሼባውን ሸብ አርጊው እሱን እንዳታጪ
ድንገተኛ መርዶ ስትሰሚ በውጪ

የፈራሁት ደርሶ ያንን ብር ስታጪ
ቤተሰብ በድንገት ሲልሽ ከቤት ውጪ

ፍቅር አለኝ ብለሽ እዚህ እንዳትመጪ
እኔም አገኘሁሽ ቤቴን ለቀሽ ውጪ።
                  
BY፦LIONEL YOHANNES

@getem
@getem
@getem
👍3927😁17👎7🔥2😢2🎉2
2 ኢትዮጵያ
በኤደን ታደሰ እና በኪሩቤል አሰፋ
፪ ኢትዮጵያ
በዔደን ታደሰ እና ኪሩቤል አሰፋ
ተፅፎ እንደ ቀረበ
@ediwub & @idcfe

@getem
@getem
@getem
20👍8🔥2
( ባክሽ አፈር ስሆን )


በምትወጅው ደብር በአርባራቱ ታቦት
የልቤን ውስጥ ሀዘን ልብሽ ተገንዝቦት
      ቀና ብዬ እንድኖር
የፍቅርሽን ማዛ ህይዎቴ አጣጥሞት
      ባክሽ አፈር ስሆን
ጥለሽኝ አትሂጅ ተመለሽ በኔ ሞት
ያፍቃሪ ሰው ልቡ ባሀዘን ቢደነድን
ዘላለም ከማልቀስ ከመጎዳት አይድን
ላንቺ ያነባሁትን ላንቺ የደከምኩትን
ላንቺ ያለቀስኩትን ላንቺ የሆኩትን
ሄዋኔን ለማግኘት አንቺን የምትመስል
ዳግም መሷትነት እንደምንስ ልክፈል
        ታፈቅሪኝ እያለሽ
ህይዎቴ ለመኖር ይጓጓ እንዳልነበር
      ዛሬ ግን ስትከጅኝ
መኖርም ሰለቼኝ ልቤ አዝኖ ሲሰበር

ትላንት ቀና አድርጎ የጠገነኝ ፍቅርሽ
መልሶ ሰበረኝ ዛሬ ፈርሶ ቃልሽ
ትመጭ እንድሆነ ስታልፊ እንዳገኝሽ
ንገሪኝ በኔ ሞት የቱጋር ልጠብቅሽ

By@Habtishe01

@getem
@getem
@paappii
👍3614😢8👎3🔥2😱1🎉1
#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር
.
ያሳለፍነዉ ሁሉ
አሁን ትዝታ እንጂ
ዉስጡ ህይወት የለም እያልሽ ላገሩ
ታወሪያለሽ አሉ
.
.
(እኔ ግን ልንገርሽ)
የሁለታችን ፍቅር
ምን እንደሚመስል. . .
እንዴት እንደነበር
በሶስት ምስክር
1
አሁን በቀደም ለት
የሆነ ቦታ ላይ
ድምጻችን ከፍ አርገን የሳቅንበት ቦታ
ፒያሳ አደባባይ
ድንገት
በቀደም ለት
በዛ ቦታ ስሄድ
ከሰባት ወር በፊት
ስቀሽ የነበረዉ
ያንቺ ሳቅ ተሰማኝ
መራመድ አቃተኝ
የሚገርምሽ ነገር
ያለፈ ነዉ ያልሺዉ
ትዝታ ነዉ ያልሽዉ
ፍቅርሽና ሳቅሽ
ከሰባት ወር ኋላ እንደ ወንዝ ፍሳሽ
ይሰማል ልንገርሽ
.
(ታዲያ ለምንድን ነዉ)
የወንዝ ዉሀ ሳቅሽ
ያለፈ ትዝታ ምናምን ነዉ ብሎ
ማንም ተራ ዘፋኝ የሚሸነግልሽ
(ይልቅ እኔን ስሚኝ)
.
ወደየትም ሳይሆን
ወዴትም ተመለሽ
የትም ሳትደርሺ
ጊዜን እንዳቆምነዉ
እንኳን ጊዜ ቀርቶ ሰዓት እንዳልሄደ
ደቂቃ እንዳልሄደ
አስረጂ ሊሆንሽ
ምስክር ሊሆንሽ
ከምንም አቅጣጫ. . . የትም ሳትመለሽ
አደባባይ መሀል
ከቡና ጠረን ጋር
እንደወንዝ የሚፈስ
ሳቅሽን ትሰሚያለሽ
.
2
ትዝ ይልሽ እንደሆን
ካንቺ መኖሪያ ቤት
(የመጣሁኝ ጊዜ)
የመራራቅ ናፍቆት
አስክሮን ቸኩለን
ሰማያት ለመዝለቅ
ከመሬት ላይ ወድቀን
ፍቅር ስንሰራ
ፍቅር ስንሰራ
ፍቅር ስንሰራ
ከሴት ወዝሽ ጋራ
የጡትሽ ስር ሽቶ
ሸሚዜ ላይ ቀርቶ
ሸሚዜ ላይ ቀርቶ
ምወደዉን ሸሚዝ
ለመልበስ እርም አልኩኝ
ለብሼዉ እንዳልሄድ
ከበደኝ ጨነቀኝ
ያንቺን ጠረን ማጠብ. . .
ነፍስ የማጥፋት ያህል
ሀጥያት መስሎ ታየኝ
(የሚገርምሽ ነገር)
እስከ ዛሬ ድረስ
በመስኮቱ ዘልቆ. . .በበሬ
የሚወጣዉ የማለዳዉ ነፋስ
በሽቶሽ ጠረን ነዉ መንደሩን የሚብስ
.
3
ታስታዉሽ እንደሆን
የሆነ ቅዳሜ
የሆነ ዉብ ሆቴል
ደግሞም አትረሺዉም. . .ፍጻሜ ምሳ ነዉ
ይኼ እንኳን ትዝ ይላል
እና. . .
እኔና አንቺ ብቻ
የተቀመጥንበት ወንበር ጠረጴዛዉ
ከዘጠኝ ወር ኋላ. . .
እዛዉ ቤት ዳግመኛ ተመልሼ ባየዉ
የሚገርምሽ ነገር
ጻፊዉን ባላዉቅም
#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር
የሚል ጽሁፍ ሰቅለዉ
ከዘጠኝ ወር ኋላ
አንድ ለብቻዬ ካንድ አንቺ ናፍቆት ጋር
ነበር ለምትይዉ ለሁለታችን ፍቅር
(ምስክር ሊሆኑን)
ያኔ ሁለታችን የጠጣነዉ ወይን
ከወይንም. . . Two Ocean
እኔ የጨለጥኩት
አንቺ ያጋመስሽዉ
እኛ ያስተረፍነዉ
እስከዛሬ ድረስ
ያተረፍነዉ ማዕድ. . .
ጠርሙስና ጽዋዉ
በክብር ተቀምጧል
ማንም ሳያነሳዉ. . .ያኔ እንደነበረዉ
(ታዲያ ምን ማለት ነዉ)
.
.
.
ፒያሳ አደባባይ
የወንዝ ዉሃ ሳቅሽ
ከቡና ጠረን ጋ
ከኔ መኖሪያ ቤት. . .
የምወደዉ ሸሚዝ ላይ
የሽቶ መአዛሽ
ከሴት ላቦትሽ ጋር
ደግሞም
እዚያ ዉብ ሆቴል ስር
ያስተረፍነዉ . . .
ማዕድ ጠርሙስና ጽዋ
አንጀት ከሚበላ
ከቆንጆ ጥቅስ ጋር
‘’#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር::’’
.
ነበርን እስካሁን
በመሆን እያየሽ
ሳቅሽ ፈሶ ሳያልቅ
ከምወደዉ ሸሚዝ
የሽቶ መዓዛሽ ዉብ ጠረኑ ሳይለቅ
ማዕድ ሳይነሳ ጽዋዉ ሳይታጠብ
ሦሥቱን ምስክሮች በዓይንሽ ፊት እያየሽ
(ታዲያ ለምንድን ነዉ)
ያሳለፍነዉ ሁሉ
#አሁን_ትዝታ_እንጂ.....
#ዉስጡ_ህይወት_የለም
ብለሽ ለመንደሩ
ላገሩ ማዉራትሽ
እዉነት ለምንድን ነዉ?
.
.
.


By ኤፍሬም ስዩም

@getem
@getem
@paappii
101👍73🔥14👎1
ያልወረደ እንባ
.
ላዩኝ ሁሉ ደስተኛ  ነኝ እስቃለሁ፤
በነሱ ቤት መከፋትን  የት አዉቃለሁ፤
.
የሚገርመዉ.....

በኔ መፍካት መቅናታቸዉ፤
እኔን መሆን ምኞታቸው፤

መች ያዉቁና ማስመሰሌን፤
የዉስጥ ሀዘን ስዉር ቁስሌን፤

በዉስጤ ታጭቆ ሰላም የሚነሳኝ፤
በነጋ በጠባ ሆድ ሆዴን ሚበላኝ፤

አዉጥቼ እንዳልጥለዉ አፍኖ የያዘኝ፤
ሳቅ የሸፋፈነዉ ያልወረደ እምባ አለኝ።
.......................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
96👍61😢25🔥7🎉2
።።።።።።።። መሀል።።።።።።።።።።።።

እያለቀሱ መሳቅ እየቀረቡ መራቅ
።። ላይለምድለት ሆዴ።።።።።።።።
እስቲ አትደሰት ፣ አትጨነቅ ባንዴ።
ቶሎ ሰፍ አትበል አትቸኩል ፣ አታርፍድ፣
ልቤ አትንጠልጠል ሆድህን አታልምድ።
እየቀረቡ መራቅ እያለቀሱ መሳቅ
።።። ላይለምድልህ ሆዴ።።።።።።።
እስቲ አትጨነቅ፣ አትደሰት ባንዴ፣
።።።።።።።። መሀል ሁን አንዳንዴ።።።


ገጣሚ:-papiel

@getem
@getem
@paappii
👍5420🔥13😱1
የፈሰሰ አይታፈስም
ትላንትና አይመለስም
ስኖር ያኔ ከጎናቹ
ውል ጥቅሜ ያልገባቹ
ምን ፍለጋ ምን ቀረና
ከደጃፌ ተገኛቹ?
.
በትላንቴ ሳልበገር
ወደፊቴ ገስግሻለው
የራስ ዋጋ ሚገባኝን
አሁን በደንብ አውቂያለው
እንደ ወትሮው ላልጎተት
ለአንድ እራሴ ቃል ገብቼ
ሚገባኝን ስላወኩኝ
አልፊያለው ሁሉን ትቼ
.
ባለሁበት ስላልቆምኩኝ
ተጨንቃቹ ተጠባቹ
ካመለጥኩት ትላንትና
ልትመልሱኝ ላሰባቹ
.
የጣልኩትን ዞሬም አላይ
እንኳን ቀርቶ ልመለከት
በመጣ እግር ተመለሱ
ደስተኛ ነኝ ባለሁበት

በኪሩቤል አሰፋ @Ebuh_bhr

@getem
@getem
@paappii
47👍34🤩4🔥2
አግኝቼ ነበር
የህዝብ መድረክ ግጥም ማንበቢያ።
ታዲያ ግጥሙ
ወረቀት የለ ከስልክ አይቻል
በቃል ነው አሉ የሚነበበው
ምን ነክቶታል ሰው
ከግጥም መሃል አንቺን ብቻ ነው የማስታውሰው።

እና ችግሩ
ህዝብ ባለበት የተለፈፈ ህዝብ አፍ ላይ ያልቃል
አንቺ...
አደባባይ ላይ አትነበቢም እንደተራ ቃል።
ላንብብሽ እንጂ
ስውር አድርጎ እርሱ እንደሠራሽ
በቃሌ ይዤሽ ወጣሁ ካዳራሽ።

By Yadel Tizazu

@getem
@getem
@paappii
70👍28😱6😢2🔥1
“ናልኝ” ቢሉህ ፥ ትመጣለህ
“ስጠኝ” ቢሉህ ፥ ትሰጣለህ
ቸር አይደለህ !
….
እኔስ ግን…
ምን ብዬ ልጠይቅ ?
ሕይወቴን ፣ ምን ላ’ርገው ?
እወቅልኝ እስቲ
ምንድነው ጌታዬ ፥ እኔ ምፈልገው ?

@getem
@getem
@paappii

By henock bekele
166😢39👍23😁3