‹‹አንድ ጥይት መቀነስ›› የኪነ
ጥበብ ምሽት ሰኞ ይካሄዳል
የኢፌዲሪ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ከተስፋ ፊልም
ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና በተፈጥሮ፣ በዘመንና የሰው ልጆች
ግንኙነትና መስተጋብር ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገው ‹‹አንድ ጥይት መቀነስ››
የተሰኘ የኪነ-ጥበብ ምሽት የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በብሄራዊ
ቴአትር ይካሄዳል፡፡
በዝግጅቱ ላይ #ደራሲና ሀያሲ ዓለማየሁ ገላጋይ ሥነ-ጽሑፍና ተፈጥሮ፣
#የሙዚቃ ባለሙያ ሰርፀ ፍሬ ስብሃት ሙዚቃና ተፈጥሮ፣# ሀኪም አበበች
ሽፈራው የባህል ሕክምናና እፅዋት፣ #ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ኢስላምና
ተፈጥሮ፣ #ፕ/ር ሽብሩ ተድላ ደግሞ በእንስሳት ዙሪያ፣ #ደራሲ አለማየሁ ዋሴ
(ዶ/ር) ቤተ ክርስቲያንና ተፈጥሮ፣ #ፕ/ር ታደሰ ደሴ ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ
አለማት በእንስሳትና በእጽዋት አያያዝና ተሞክሯቸው ዙሪያ በሚል
ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን #ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም፣ #ደራሲና ጋዜጠኛ
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ #ፕ/ር ሰብስቤ ደምሴ፣ በተመሳሳይ ርዕስ ስራዎቻቸውን
ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
#ገጣሚ ረድኤት ተረፈና ገጣሚ #ተዋናይ ተፈሪ አለሙ ግጥሞቻቸውን የሚያነቡ
ሲሆን፣ ‹‹አንድ ጥይት መቀነስ›› የተሰኘ የ15 ደቂቃ አጭር ተውኔት
እንደሚቀርብም አዘጋጆቹ ገልጸዋል::
@getem
@balmbaras
ጥበብ ምሽት ሰኞ ይካሄዳል
የኢፌዲሪ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ከተስፋ ፊልም
ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና በተፈጥሮ፣ በዘመንና የሰው ልጆች
ግንኙነትና መስተጋብር ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገው ‹‹አንድ ጥይት መቀነስ››
የተሰኘ የኪነ-ጥበብ ምሽት የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በብሄራዊ
ቴአትር ይካሄዳል፡፡
በዝግጅቱ ላይ #ደራሲና ሀያሲ ዓለማየሁ ገላጋይ ሥነ-ጽሑፍና ተፈጥሮ፣
#የሙዚቃ ባለሙያ ሰርፀ ፍሬ ስብሃት ሙዚቃና ተፈጥሮ፣# ሀኪም አበበች
ሽፈራው የባህል ሕክምናና እፅዋት፣ #ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ኢስላምና
ተፈጥሮ፣ #ፕ/ር ሽብሩ ተድላ ደግሞ በእንስሳት ዙሪያ፣ #ደራሲ አለማየሁ ዋሴ
(ዶ/ር) ቤተ ክርስቲያንና ተፈጥሮ፣ #ፕ/ር ታደሰ ደሴ ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ
አለማት በእንስሳትና በእጽዋት አያያዝና ተሞክሯቸው ዙሪያ በሚል
ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን #ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም፣ #ደራሲና ጋዜጠኛ
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ #ፕ/ር ሰብስቤ ደምሴ፣ በተመሳሳይ ርዕስ ስራዎቻቸውን
ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
#ገጣሚ ረድኤት ተረፈና ገጣሚ #ተዋናይ ተፈሪ አለሙ ግጥሞቻቸውን የሚያነቡ
ሲሆን፣ ‹‹አንድ ጥይት መቀነስ›› የተሰኘ የ15 ደቂቃ አጭር ተውኔት
እንደሚቀርብም አዘጋጆቹ ገልጸዋል::
@getem
@balmbaras
፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨ ፨፨
(((እኔም #ገጣሚ_ነኝ)))
ስሙኝ.......
እኔም #ገጣሚ_ነኝ!
በሶሻል ሚዲያ
ስሜ ያልተጠራ
ብዙም ያልታወኩኝ....
በደሳሳ ጎጆ
ህልሜን ያጠበብኩኝ
እኔም #ገጣሚ_ነኝ!
*
*
*
ከምሁራን ተርታ
ፈፅሞ ያልተሰለፍኩ
ከእውቅ ፀሀፊያን
መሀል ያልተካተትኩ
እኔም #ደራሲ_ነኝ!
በሰላች ብእሬ
ስሜቴን የገለፅኩ
*
*
ነገር ግን......
እንደነ እንትና
እስካርፕ አልጠመጠምኩ
እንደ ሀያሲያን
ሸሚዝ በከረባት
ታጥቄ አለበስኩ
በአምስቱ ጣቶቼ
የእከሌን መፅሀፍ
ይዤ አልተሽከረከርኩ....
በሄድኩበት ሁሉ
#ደራሲ_ነኝ እኔ
እውቅ ነው ሀሳቤ
ብዬም አልተናዘዝኩ.....
*
*
.........ግናም እፅፋለሁ........
ብእር ከወረቀት
እያዋደድኳቸው
ለሰው የማይገባ
ዝብርቅርቅ ሀሳባት
እኔም አፈሳለሁ ...
በሀሳቤ አርግዤው
ለአእላፉ ቀናት
እያብሰለሰልኩት
ይዤው እከርማለሁ...
የቁርጥ ቀን መቶ
እስክገላገለው
ወረቀት ከብእር
እስከማጋጥመው
ብዙ አምጣለሁ...
ያማጥኩት ተባርኮ
በመድብል ሲወለድ
ማየትን እሻለሁ..
*
*
እና እንደሌሎቹ.....
#እኔም_ገጣሚ ነኝ!
ብዬ አልዘባርቅም...
የገጠምኩት #ግጥም
የደረስኩት ድርሰት
የከሌ ነው ታሪክ ነው
ብዬ አልናገርም...
*
*
እውነቱ ገብቷቸው
አንተ #ደራሲ_ነክ
የሰዎችን እውነት
በብእር የገለፅክ
ብለው እስኪረዱኝ
በቤቴ የምኖር
እኔም #ገጣሚ_ነኝ!
✍ተፃፈ በ @Mak_bale
ግንቦት 1,2012
@getem
@getem
@getem
(((እኔም #ገጣሚ_ነኝ)))
ስሙኝ.......
እኔም #ገጣሚ_ነኝ!
በሶሻል ሚዲያ
ስሜ ያልተጠራ
ብዙም ያልታወኩኝ....
በደሳሳ ጎጆ
ህልሜን ያጠበብኩኝ
እኔም #ገጣሚ_ነኝ!
*
*
*
ከምሁራን ተርታ
ፈፅሞ ያልተሰለፍኩ
ከእውቅ ፀሀፊያን
መሀል ያልተካተትኩ
እኔም #ደራሲ_ነኝ!
በሰላች ብእሬ
ስሜቴን የገለፅኩ
*
*
ነገር ግን......
እንደነ እንትና
እስካርፕ አልጠመጠምኩ
እንደ ሀያሲያን
ሸሚዝ በከረባት
ታጥቄ አለበስኩ
በአምስቱ ጣቶቼ
የእከሌን መፅሀፍ
ይዤ አልተሽከረከርኩ....
በሄድኩበት ሁሉ
#ደራሲ_ነኝ እኔ
እውቅ ነው ሀሳቤ
ብዬም አልተናዘዝኩ.....
*
*
.........ግናም እፅፋለሁ........
ብእር ከወረቀት
እያዋደድኳቸው
ለሰው የማይገባ
ዝብርቅርቅ ሀሳባት
እኔም አፈሳለሁ ...
በሀሳቤ አርግዤው
ለአእላፉ ቀናት
እያብሰለሰልኩት
ይዤው እከርማለሁ...
የቁርጥ ቀን መቶ
እስክገላገለው
ወረቀት ከብእር
እስከማጋጥመው
ብዙ አምጣለሁ...
ያማጥኩት ተባርኮ
በመድብል ሲወለድ
ማየትን እሻለሁ..
*
*
እና እንደሌሎቹ.....
#እኔም_ገጣሚ ነኝ!
ብዬ አልዘባርቅም...
የገጠምኩት #ግጥም
የደረስኩት ድርሰት
የከሌ ነው ታሪክ ነው
ብዬ አልናገርም...
*
*
እውነቱ ገብቷቸው
አንተ #ደራሲ_ነክ
የሰዎችን እውነት
በብእር የገለፅክ
ብለው እስኪረዱኝ
በቤቴ የምኖር
እኔም #ገጣሚ_ነኝ!
✍ተፃፈ በ @Mak_bale
ግንቦት 1,2012
@getem
@getem
@getem