ተወዳጁ ሙዚቀኛ ሙሌ ሐመልማሎ በተለይም ከኤፍሬም አማረጋ "ተሸንፊያለሁ" በሚለው ስራው በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ሙሉአለም በደረሰበት የኩላሊት ህመም ዲያሊሲስ እንዲያደርግ በሀኪሞች ተነግሮታል። እንደሚታወቀው ይህ ሂደት ከፍተኛ ገንዘብን የሚጠይቅ ሲሆን በአርቲስቱ አቅም ደግሞ እስከ መጨረሻው መግፋት የማይቻል በመሆኑ ሁሉም ሰው ድጋፉን ያሳየው ዘንድ በፈጣሪ ስም እንጠይቃለን..
ይህ ወጣት አርቲስት ብዙ የሚጠበቅበት ገና ሙዚቃን ጀመርኳት እያለ እሩቅ በሚያስብበት በዚህ ሰዓት እንዲህ ባለው አደጋ ተደናቅፎ እንዳይቀር ሁላችንም በመረባረብ የበኩላችንን ማድረግ ይኖርብናል። አርቲስት የህዝብ ሀብት ነው። ህይወቱን እና ጊዜውን ለህዝብ ሰቶ የሚሰራ ጥበበኛ መጠለያው መሸሸጊያው ይኼው ያገለገለው ህዝብ ነውና ሁላችን ወደ ህዝብ እንጮሃለን..? ድጋፋችሁን ሽተን ደጃቹን የምንረግጥ ድርጅቶችም ትተባበሩን ዘንድ በዙሁ አጋጣሚ ለመጠየቅ እንገደዳለን።
ከፀሎት ጀምሮ ሁላችንም በምንችለው አቅም ከአርቲስቱ ጎን በመሆን እንርዳው.. #ጓደኞቹ
mulualem takele
1000182044184
ንግድ ባንክ
ከጎን ሆናችሁ ሀሳብ ለመስጠት ይሄን group ተጠቀሙ
https://tttttt.me/joinchat/JSJyPhNcOTNP5V8x4LOXOw
ይህ ወጣት አርቲስት ብዙ የሚጠበቅበት ገና ሙዚቃን ጀመርኳት እያለ እሩቅ በሚያስብበት በዚህ ሰዓት እንዲህ ባለው አደጋ ተደናቅፎ እንዳይቀር ሁላችንም በመረባረብ የበኩላችንን ማድረግ ይኖርብናል። አርቲስት የህዝብ ሀብት ነው። ህይወቱን እና ጊዜውን ለህዝብ ሰቶ የሚሰራ ጥበበኛ መጠለያው መሸሸጊያው ይኼው ያገለገለው ህዝብ ነውና ሁላችን ወደ ህዝብ እንጮሃለን..? ድጋፋችሁን ሽተን ደጃቹን የምንረግጥ ድርጅቶችም ትተባበሩን ዘንድ በዙሁ አጋጣሚ ለመጠየቅ እንገደዳለን።
ከፀሎት ጀምሮ ሁላችንም በምንችለው አቅም ከአርቲስቱ ጎን በመሆን እንርዳው.. #ጓደኞቹ
mulualem takele
1000182044184
ንግድ ባንክ
ከጎን ሆናችሁ ሀሳብ ለመስጠት ይሄን group ተጠቀሙ
https://tttttt.me/joinchat/JSJyPhNcOTNP5V8x4LOXOw
ትዝታና ተስፋ(ልዑል ሀይሌ)
ያኔ ባዲስ ዓመት
በጥበብ ሳገኝሽ
ቅኔዬንም ባጣ
የሰው ስዘርፍልሽ
በልቤ የቋጠርኩት
ጅምር ስንኝ ይዤ
ወዳንቺ ስመጣ
ይታወቀኝ ነበር
ባንቺ መድፊያ ፍቅር
ውብ ግጥም ሲወጣ
..
.
ያ ውብ ጅምር ግጥም...
.
የኔ ጅምር ስንኝ
ያንቺ ውብ መድፊያዎች
ዘላለም ሊያቆዩን
ቃላት ሲያማምሉን
እልፍ መሃላዎች
..
ታዲያ ምን ያደርጋል
.
.
አዲስ ያልነው ዓመት
እርጅና ተጭኖት
ያን ውብ ግጥማችንን
አንድ አፍራሽ ቃል ሰብሮት
ከጅምር ስንኜ ጥለሺኝ ስትሄጂ
ቤት ደፊስ አልጠፋም
አንቺ ቀረሽ እንጂ
..
.
ዛሬ
.
በጳጉሜ ላይ ሆኜ
የትናንት ና ነገ
መስከረም ሳያቸው
ትዝታና ተስፋ
እኩል መዝኛቸው
ካለፈ ትዝታ ተስፋ በልጦብኛል
ካምናው መስከረምሽ
የነገው ናፍቆኛል
..
.
በጊዜ ሂደት ውስጥ...
...
.
ያንድ ኑሮ ግጥም
ርዝመት አውቄያለሁ
ግጥሜን ልቀጥል
ጅምር ስንኝ ይዤ
መድፊያው ጋ ሄጃለሁ
4-13-2008
@getem
@getem
Share it.... @getem
ያኔ ባዲስ ዓመት
በጥበብ ሳገኝሽ
ቅኔዬንም ባጣ
የሰው ስዘርፍልሽ
በልቤ የቋጠርኩት
ጅምር ስንኝ ይዤ
ወዳንቺ ስመጣ
ይታወቀኝ ነበር
ባንቺ መድፊያ ፍቅር
ውብ ግጥም ሲወጣ
..
.
ያ ውብ ጅምር ግጥም...
.
የኔ ጅምር ስንኝ
ያንቺ ውብ መድፊያዎች
ዘላለም ሊያቆዩን
ቃላት ሲያማምሉን
እልፍ መሃላዎች
..
ታዲያ ምን ያደርጋል
.
.
አዲስ ያልነው ዓመት
እርጅና ተጭኖት
ያን ውብ ግጥማችንን
አንድ አፍራሽ ቃል ሰብሮት
ከጅምር ስንኜ ጥለሺኝ ስትሄጂ
ቤት ደፊስ አልጠፋም
አንቺ ቀረሽ እንጂ
..
.
ዛሬ
.
በጳጉሜ ላይ ሆኜ
የትናንት ና ነገ
መስከረም ሳያቸው
ትዝታና ተስፋ
እኩል መዝኛቸው
ካለፈ ትዝታ ተስፋ በልጦብኛል
ካምናው መስከረምሽ
የነገው ናፍቆኛል
..
.
በጊዜ ሂደት ውስጥ...
...
.
ያንድ ኑሮ ግጥም
ርዝመት አውቄያለሁ
ግጥሜን ልቀጥል
ጅምር ስንኝ ይዤ
መድፊያው ጋ ሄጃለሁ
4-13-2008
@getem
@getem
Share it.... @getem
👍1
ኢትዮጲያ በሚሏት የሚስኪኖች ሀገር
ሁሉም ሰው እረስቷት እኔ ብቻ ብቀር
መቼም አላቆምም እሷን ብቻ ማፍቀር።
(ልብ አልባው ገጣሚ )
@getem
@getem
@gebriel_19
ሁሉም ሰው እረስቷት እኔ ብቻ ብቀር
መቼም አላቆምም እሷን ብቻ ማፍቀር።
(ልብ አልባው ገጣሚ )
@getem
@getem
@gebriel_19
ያስተሰርያል ቁጥር ሁለት " ፈገግ ብላችሁ እደሩ
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ወያኔነታቸው ከዚህ ሰረገላ
ስልጣን ሀክ ተደርገው ፣ ሲተኩ በሌላ
በአፈሙዞች ራስ ፣ ያስወጣችው ጠብሳ
ጋብዛ አስገባችው ፣ መቀሌ ላይ ምሳ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
አስራ ሰባት መርፌው ፣ ወጋግቶን ሲወጣ
አስራ ሰባት ባንኮች ፣ የሚዘርፈው መጣ
ይህን ሁሉ እያየ ፣ ከአፉ ቃል ያልወጣ
አንዲት ቅኔ ብዘርፍ ፣ ቆይ ለምን ተቆጣ?
ይቅር በለውና ፣ ከፋፋዩን ወቅሰህ
አንድ የነበረን ህዝብ ፣ አንድ አርገው መልሰህ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ኢትዮጵያ
እማማ አቢሲኒያ
ኢትዮጵያ ስሚ
እማማ አቢሲኒያ
ቂም በቀል ክፉ ነው ፣ከአምላክ ያለያያል
በቀለን በማሰር ፣ የህዋት ፅድቅ ይታያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ዘፅአት በኢትዮጵያ ፣ ወደ ለውጥ ጉዞ
ኩሬውን ሚያሻግር፣ ባህር ሀሳብ ይዞ
ቅርብ ነው አይርቅ ፣ የኢትዮጵያ ቀን መውጫ
ባንድነት ከጣልን ፣ ዱላ ክላሽ ሜንጫ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ፍቅር አጥተን እንጂ ፣ በርሀብ የተቀጣን
ጭማሪ ጥላቻ ፣ ሚሰጠን መች አጣን
ኦሲሳ ኦሲሳ ፣ ኦሲሳ ማንደላው
ይቅርታን አያውቅም ፣ ክላሽ እና ዱላው
በተስፋዋ መሬት ፣ እንዲፈፀም ቃሉ
መሥጅት ቤተስኪያኑን ፣ አትናዱ አታቃጥሉ
እማማ ኤሎሔ አላሔ
እማማ አትሰማኝ ወይ በይው
እማማ ማማዬ እማማ
ይሔም በክፉ ቃል ፣ ይሄንን ሲወቅሰው
ይህም በጥላቻ ፣ ይሄንን ሲከሰው
ህዝቦች እመሐል ቤት ፣ የምንቧቀሰው
መለየት አቅቶን ነው ፣ ሚበጀውን ሰው
ኦኦኦኦ ያስተሰርያል
ጃ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ማለት ፈጣሪ ፣ መሰረይ ይቅርታ
እኛ ሳንስማማ ፣ እንዴት ይስማን ጌታ
ኤሎሔ አላሔ
እማማ ማማዬ እማማ
እስቲ ተደመሩ ፣ እርስ በእርሳችሁ
እናንተን እያየ ፣ ህዝብ ይማርባችሁ
አንድ ሀገር አድኑ ፣ በልዩነታችሁ
አለበለዚያማ
በምን ያስታውቃል ፣ እኛን መውደዳችሁ?
።።።
አቤት ስቃይ ፣ አቤት ጠኔ
ኡንዱ ኬኛ ፣ ሁሉ የኔ
አልቅሰን ሳናባራ ፣ በወያኔ
እዚ ደግሞ ፣ ሌላ ትኩሳት
ሳይጠሩት አቤት ፣ ብሎ መነሳት
ወዲህ አፈናቃይ ፣ ወዲያ እድሳት
ወገኔ አለቀ ፣ በዘረኛ እሳት
እሳት
እሳት
እሳት
ኧረ አይነጋም ወይ
ኧረ አይነጋም ወይ ኢትዮጵያዬ
@getem
@getem
@gebriel_19
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ወያኔነታቸው ከዚህ ሰረገላ
ስልጣን ሀክ ተደርገው ፣ ሲተኩ በሌላ
በአፈሙዞች ራስ ፣ ያስወጣችው ጠብሳ
ጋብዛ አስገባችው ፣ መቀሌ ላይ ምሳ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
አስራ ሰባት መርፌው ፣ ወጋግቶን ሲወጣ
አስራ ሰባት ባንኮች ፣ የሚዘርፈው መጣ
ይህን ሁሉ እያየ ፣ ከአፉ ቃል ያልወጣ
አንዲት ቅኔ ብዘርፍ ፣ ቆይ ለምን ተቆጣ?
ይቅር በለውና ፣ ከፋፋዩን ወቅሰህ
አንድ የነበረን ህዝብ ፣ አንድ አርገው መልሰህ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ኢትዮጵያ
እማማ አቢሲኒያ
ኢትዮጵያ ስሚ
እማማ አቢሲኒያ
ቂም በቀል ክፉ ነው ፣ከአምላክ ያለያያል
በቀለን በማሰር ፣ የህዋት ፅድቅ ይታያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ዘፅአት በኢትዮጵያ ፣ ወደ ለውጥ ጉዞ
ኩሬውን ሚያሻግር፣ ባህር ሀሳብ ይዞ
ቅርብ ነው አይርቅ ፣ የኢትዮጵያ ቀን መውጫ
ባንድነት ከጣልን ፣ ዱላ ክላሽ ሜንጫ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ፍቅር አጥተን እንጂ ፣ በርሀብ የተቀጣን
ጭማሪ ጥላቻ ፣ ሚሰጠን መች አጣን
ኦሲሳ ኦሲሳ ፣ ኦሲሳ ማንደላው
ይቅርታን አያውቅም ፣ ክላሽ እና ዱላው
በተስፋዋ መሬት ፣ እንዲፈፀም ቃሉ
መሥጅት ቤተስኪያኑን ፣ አትናዱ አታቃጥሉ
እማማ ኤሎሔ አላሔ
እማማ አትሰማኝ ወይ በይው
እማማ ማማዬ እማማ
ይሔም በክፉ ቃል ፣ ይሄንን ሲወቅሰው
ይህም በጥላቻ ፣ ይሄንን ሲከሰው
ህዝቦች እመሐል ቤት ፣ የምንቧቀሰው
መለየት አቅቶን ነው ፣ ሚበጀውን ሰው
ኦኦኦኦ ያስተሰርያል
ጃ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ማለት ፈጣሪ ፣ መሰረይ ይቅርታ
እኛ ሳንስማማ ፣ እንዴት ይስማን ጌታ
ኤሎሔ አላሔ
እማማ ማማዬ እማማ
እስቲ ተደመሩ ፣ እርስ በእርሳችሁ
እናንተን እያየ ፣ ህዝብ ይማርባችሁ
አንድ ሀገር አድኑ ፣ በልዩነታችሁ
አለበለዚያማ
በምን ያስታውቃል ፣ እኛን መውደዳችሁ?
።።።
አቤት ስቃይ ፣ አቤት ጠኔ
ኡንዱ ኬኛ ፣ ሁሉ የኔ
አልቅሰን ሳናባራ ፣ በወያኔ
እዚ ደግሞ ፣ ሌላ ትኩሳት
ሳይጠሩት አቤት ፣ ብሎ መነሳት
ወዲህ አፈናቃይ ፣ ወዲያ እድሳት
ወገኔ አለቀ ፣ በዘረኛ እሳት
እሳት
እሳት
እሳት
ኧረ አይነጋም ወይ
ኧረ አይነጋም ወይ ኢትዮጵያዬ
@getem
@getem
@gebriel_19
❤1👍1
የማጀት ሥር ወንጌል
(ህሊና ደሳለኝ)
ሙያተኛ ሀገሬ ከማጥገብ ጎደለ በረከት እራቀው የገበታሽ ለዛ፣
ተሻምቶ ለመጉረስ ከበላነው ይልቅ የደፋነው በዛ፡፡
ሙያሽ ባያስደፍር አጀብ ቢሰኙበት፣
ማዕዱ ቢሙላላ ዓይነቱ ቢያምርበት፣
አበዛዙ አይደለም አበላሉ ላይ ነው የገበታሽ ውበት፡፡
እየተማመንን! የፉክክር ቅሚያ በርሃብ እየናጥን፣
ከደፋነው ጠግቦ ውሻችን በለጠን፡፡
ከምርት አላነስን፣
ጎተራችን ሙሉ ጀግና አራሽ መች አጥተን፣
ማሰብ የጎደለው አያያዛችን ነው ገደል የከተተን፡፡
ይልቅ ግዴለሽም! ከምግባር ምጣድ ላይ ሳንበስል አንጋግተሸ ከማዕድ አትምሪን፣
ገበታሽ እንዲያምር ከእግዜር የሚያስታርቅ ፍቅር አስተምሪን፡፡
ገበታ ዕድሜ ነው ባለ ማሰብ መክነን፣
ሳንፀነስ ጃጀን፣
ሳንጣድ አረርን፣
ከዘመን ገበታ ከፊደል አቅድመን ዘር እየቆጠርን፡፡
ገበታ ሀቅ ነው በክፋት ሊጥ ጋግረው ያሻገቱት እውነት፣
በሆዳም እስክስታ ረግጠው ያፈኑት የምስኪናን ጩኸት፡፡
እስከ ልጠይቅሽ በጥም ደዌ ደቆ የረሃብ ጠኔ ደፍቶት እልፍ ትውልድ ያልፋል፣
ቢራ ለመጥመቂያ ሚበተን ገብስ ግን ከሀገር መች ይጠፋል፡፡
ከሆድ በማይሻገር የማጀት ቤት ዕውቀት አጥብበሽ አትለኪን፣
እስቲ መኖር ይግባን ከማስተዋል መቅደስ ሰው መሆን ስበኪን፡፡
ዘመን ካልገበረው ከችጋር ተራራ ከሲኦል ዳር ኑሮ፣
እንዴት ነው መሻገር ከመርፌ ቀዳዳ በጠበበ አይምሮ፡፡
ከምስኪን ዘመን ላይ የማይኖሩበትን ዕድሜ መበዳደር፣
ለአንዲት ማምሻ ደስታ በአያት እስትንፋስ ላይ ቁማር መደራደር፣
ያሳፍራል አይደል?
እያደጉ ማነስ እያነሱ መዝቀጥ፣
አጎንብሶ ያፀናን የድሃ እናት ጉልበት በጭካኔ መርገጥ፣
ያሳምማል አይደል?
መንገስ ከሚያባላስ መጥገብ ከሚያቃቅር ማግኘት ከሚያጎለን፣
ማጣት ውሎ ይግባ ባርነት ይሰንብት ድህነት ይግደለን፡፡
ከረፈደ ፀፀት ደረት እየደቁ ከእግዜር ቢዋቀሱ፣
ትርጉሙ ምንድነው ሲኖር ተቃቅሮ ሲሞት መላቀሱ፡፡
በእናታችን አድባር በፍቅሯ ይሁንብን፣
መድመቅ ካጋደለን ቆሽሸን ይመርብን፡፡
በመጠማት ሲቃ እስትንፋስ እስኪያንቃት ነፍሳችን ትርበትበት፣
ብቻህን ከመጥገብ አብሮ መራብህ ነው ሰው የመሆን ውበት፡፡
በድፍን ግልብ እሚያጋድል ህዝብ የመሆን መንጋ አይንዳን፣
በማሰብ ስር እንፈወስ በሰውነት ፀበል እንዳን፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ከመንጋነት ሚያግድ እረኛ አያሻህም ከህሊናህ በላይ፣
ስታስብ መሪ ነህ በብስለት ከፍታ በማስተዋል ሰማይ፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን የጎጥ አረም ነቅለህ በአንድነት መስክ ላይ ፍቅር ትዘራለህ፣
በወረወሩብህ የጥላቻ ድንጋይ ትውልድ የሚያፋቅር ድልድይ ታበጃለህ፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ዝምታህ ኃያል ነው ጀግና የሚያንበረክክ፣
ከፈሪ ቀረርቶ ከባዶ ሰው ጩኀት፣
ሀገር ላምስ ከሚል በመንደር አጀንዳ በአሽኮለሌ ተረት፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ነጻ ነህ እያሉህ መታሰር ያምርሃል፣
መቀመቅ መበስበስ፡፡
የኖርክለት እውነት ሀገር እስኪፈታ፣
በሀቁ እስኪመዘን ስለ በርባን ክብር የቆሸሸው ፍቅር የታሰረው ጌታ፣
ከድል ታሪክ ሰማይ ከሥልጣኔ ዳር ከጥበብ ከፍታ፣
እንሻገራለን ህዝብነትን ትተን ሰው የሆንን ለታ፡፡
በትረ ጥበበ ቢካን ዓለም ሊያንቀጠቅጥ ድል ሥልጣን ቢሰጠው፣
ጀግና መሪ አይደለም ብርቱ ተመሪ ነው ሀገር ሚለውጠው፡፡
አስተውል ወዳጄ ጠልተን ላንጣላ ችለን ላንጋደል ነደን ላንፋጀው፣
የኛው ትርምስ ነው በልቶ ለሚያባላ ጠላት ሚበጀው፡፡
ስጋና ደም እንጂ የአንድነታችን ውል የፍቅራችን ቀለም፣
ያሰመርነው ክልል የታጠርንበት ዘር ቋንቋችን አይደለም፡፡
ከመዋሃድ መቅደስ ትውልድ እናስተምር፣
ዘመን ይመርቀን ፍቅራችን ምን ጎድሎት ደማችን ያስታርቀን፡፡
በልጆቿ አጥንት በደም ኪዳን ምለን የገባንላት ቃል፣
ከጩኀት ያለፈ ዘመን የሚሻገር ተግባር ይጠይቃል፡፡
በአንድ ሃሳብ ተጋምደን በድል ድር እናብር ውድቀታችን ያንቃን፣
ሠርተን እናሳምን ሆነን ድል እንንሳ የአፍ ጀግንነት ይብቃን፡፡
ምስኪኒቷ እናቴ! በሞላ ጎዳና ባልጠበበ ድንበር በዘር ገመድ ታግዳ፣
ነጻ ነኝ ትላለች መንጋነት ያሰረው ባሪያ ትውልድ ወልዳ፡፡
የጀግንነት እብሪት ልባችንን ደፍኖት ማሰብ እየከዳን፣
እንዴት ነው ነጻነት እንዳበደ ፈረስ ስሜት እየነዳን፡፡
ገድሎ የመንገስ ጥማት ጩኀት ላገነነ አመጽ ላጀገነው፣
ለዚህ ምስኪን ትውልድ በጅምላ እየነዱት፣
በመንጋ እያሰበ ነጻነት እንዴት ነው?
ነጻነት ምርጫ ነው አምሮ ቢደላደል ጥፋት ያመነነው የመንጋዎች መንገድ፣
እንቅፋቱን ወዶ ለኖሩለት እውነት ለብቻ መራመድ፡፡
ነጻነት ማመን ነው ቀን ወዶ ቢያጀግን ቀን ጠልቶ ቢከዳም፣
ቢቆሽሹም ቢደምቁም እራስን መቀበል ራስን መምሰል ነው የነጻነት ገዳም፡፡
ነጻነት ማሰብ ነው በአንድነት መለምለም የኔነትን አረም ከህሊና ማጥፋት፣
ዘር ሆኖ ከማነስ ሀገር ሆኖ ማበብ ዓለም ሆኖ መስፋት፡፡
ንገሯት ለሀገሬ በጀግኖቿ ትግል ድንበር ባታስደፍር ከእጀ ገዥ ብትወጣ፣
ነጻ ነኝ እንዳትል በገዛ ልጆቿ በእጅ አዙር ተሸጣ ፡፡
ስሩን ካልሸመነው በመዋሃድ ጥለት በማስተዋል ሸማ፣
ታሪክ አናደምቅም በጭብጨባ ድግስ በሆይ ሆይታ ዜማ፡፡
ምን ብናቀነቅን በየሰልፉ ሜዳ ወኔ ብንደግስም፣
በፈረሰ አይምሮ በደቀቀ አንድነት ሀገር አናድስም፡፡
በጭፍን ከመሮጥ አስቦ ማዝገም ነው የመራመድ ውሉ፣
ሁሉም እንቅፋቶች እስኪጥሉን ድረስ ምርኩዝ ይመስላሉ፡፡
በድፍን ግልብ እሚያጋድል ህዝብ የመሆን መንጋ አይንዳን፣
በማሰብ ስር እንፈወስ በሰውነት ፀበል እንዳን፡፡
ከእግዜር ልንወዳጅ ለምህረቱ ጥላ እምባ ብንደግስም፣
ልብን ሳይመልሱ ለንስሃ መሮጥ ከጽድቅ አያደርስም፡፡
ውብ ነገን እናውርስ ትላንትን አክመን በይቅርታ ፀበል፣
ትውልድ ይጨርሳል ያረገዝነው እምባ የቋጠርነው በቀል፣
ከመስጠት አንጉደል ከቀማኞች ገደል ተረግጠን ብንጣል፣
ካሸከሙን በቀል ምናወርሰው ፍቅር ሀገር ይለውጣል፡፡
ከዕድሏ ጣሪያ ላይ ዘር የቀዳደው ሽንቁሯ ቢበዛም፣
ያ ከንቱ ፎካሪ ባፈጀ ቀረርቶ ሺህ ጉራ ቢነዛም፣
ሚሊዮን ዘር ቢሸጥ አንድ ሀገር አይገዛም፡፡
ኢዮጵያዊነት ነው የትርታችን ልክ የነፍሳችን ግጥም፣
መልስ ቤት በራቀው በከረመ ፀሎት ሰርክ ብታንጋጥም
አጎንብሳ ድሃ ባፀናችው ጉልበት ብትረጋገጥም
ነፍሷን አደህይታ ባሻረችው ቁስል ብትገሸለጥም፣
ሀገር ሆና ገዝፋ በየ ጎጣጎጡ አትርመጠመጥም፡፡
የዘመን እውነት ነን ከደግነት ሰማይ በጥበብ የኖርን፣
ትዕግስትም ልክ አለው ፈርተን እንዳይመስለው ስላቀረቀርን፡፡
ማተብ አስሮን እንጂ ተጣልተን እንዳንቀር በክፍፍል ገደል፣
ከሀገር ክብር በልጦ ሞት ብርቃችን አይደል፡፡
ንገሩት ለዛ ሰው ከዓለም ጫፍ እስከ ጫፍ ኃይል እንደ ተራራ ገዝፎ ቢከመርም፣
ክንዱን አፈርጥሞ እልፍ የሰገደለት ጀግና ቢሰድርም፣
ዓለም የሞተበት የጠላት ማርከሻ ጦር ቢደረድርም፣
በአንድ ዓይናችን ሰላም በኢትዮጵያችን ክብር አንደራደርም!!!
©ሕሊና ደሳለኝ
ኅሊና_ደሳለኝ በአዲስ ዓመት ዋዜማ በቤተ መንግስት
ካቀረበችው ግጥም
@getem
@getem
@getem
(ህሊና ደሳለኝ)
ሙያተኛ ሀገሬ ከማጥገብ ጎደለ በረከት እራቀው የገበታሽ ለዛ፣
ተሻምቶ ለመጉረስ ከበላነው ይልቅ የደፋነው በዛ፡፡
ሙያሽ ባያስደፍር አጀብ ቢሰኙበት፣
ማዕዱ ቢሙላላ ዓይነቱ ቢያምርበት፣
አበዛዙ አይደለም አበላሉ ላይ ነው የገበታሽ ውበት፡፡
እየተማመንን! የፉክክር ቅሚያ በርሃብ እየናጥን፣
ከደፋነው ጠግቦ ውሻችን በለጠን፡፡
ከምርት አላነስን፣
ጎተራችን ሙሉ ጀግና አራሽ መች አጥተን፣
ማሰብ የጎደለው አያያዛችን ነው ገደል የከተተን፡፡
ይልቅ ግዴለሽም! ከምግባር ምጣድ ላይ ሳንበስል አንጋግተሸ ከማዕድ አትምሪን፣
ገበታሽ እንዲያምር ከእግዜር የሚያስታርቅ ፍቅር አስተምሪን፡፡
ገበታ ዕድሜ ነው ባለ ማሰብ መክነን፣
ሳንፀነስ ጃጀን፣
ሳንጣድ አረርን፣
ከዘመን ገበታ ከፊደል አቅድመን ዘር እየቆጠርን፡፡
ገበታ ሀቅ ነው በክፋት ሊጥ ጋግረው ያሻገቱት እውነት፣
በሆዳም እስክስታ ረግጠው ያፈኑት የምስኪናን ጩኸት፡፡
እስከ ልጠይቅሽ በጥም ደዌ ደቆ የረሃብ ጠኔ ደፍቶት እልፍ ትውልድ ያልፋል፣
ቢራ ለመጥመቂያ ሚበተን ገብስ ግን ከሀገር መች ይጠፋል፡፡
ከሆድ በማይሻገር የማጀት ቤት ዕውቀት አጥብበሽ አትለኪን፣
እስቲ መኖር ይግባን ከማስተዋል መቅደስ ሰው መሆን ስበኪን፡፡
ዘመን ካልገበረው ከችጋር ተራራ ከሲኦል ዳር ኑሮ፣
እንዴት ነው መሻገር ከመርፌ ቀዳዳ በጠበበ አይምሮ፡፡
ከምስኪን ዘመን ላይ የማይኖሩበትን ዕድሜ መበዳደር፣
ለአንዲት ማምሻ ደስታ በአያት እስትንፋስ ላይ ቁማር መደራደር፣
ያሳፍራል አይደል?
እያደጉ ማነስ እያነሱ መዝቀጥ፣
አጎንብሶ ያፀናን የድሃ እናት ጉልበት በጭካኔ መርገጥ፣
ያሳምማል አይደል?
መንገስ ከሚያባላስ መጥገብ ከሚያቃቅር ማግኘት ከሚያጎለን፣
ማጣት ውሎ ይግባ ባርነት ይሰንብት ድህነት ይግደለን፡፡
ከረፈደ ፀፀት ደረት እየደቁ ከእግዜር ቢዋቀሱ፣
ትርጉሙ ምንድነው ሲኖር ተቃቅሮ ሲሞት መላቀሱ፡፡
በእናታችን አድባር በፍቅሯ ይሁንብን፣
መድመቅ ካጋደለን ቆሽሸን ይመርብን፡፡
በመጠማት ሲቃ እስትንፋስ እስኪያንቃት ነፍሳችን ትርበትበት፣
ብቻህን ከመጥገብ አብሮ መራብህ ነው ሰው የመሆን ውበት፡፡
በድፍን ግልብ እሚያጋድል ህዝብ የመሆን መንጋ አይንዳን፣
በማሰብ ስር እንፈወስ በሰውነት ፀበል እንዳን፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ከመንጋነት ሚያግድ እረኛ አያሻህም ከህሊናህ በላይ፣
ስታስብ መሪ ነህ በብስለት ከፍታ በማስተዋል ሰማይ፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን የጎጥ አረም ነቅለህ በአንድነት መስክ ላይ ፍቅር ትዘራለህ፣
በወረወሩብህ የጥላቻ ድንጋይ ትውልድ የሚያፋቅር ድልድይ ታበጃለህ፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ዝምታህ ኃያል ነው ጀግና የሚያንበረክክ፣
ከፈሪ ቀረርቶ ከባዶ ሰው ጩኀት፣
ሀገር ላምስ ከሚል በመንደር አጀንዳ በአሽኮለሌ ተረት፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ነጻ ነህ እያሉህ መታሰር ያምርሃል፣
መቀመቅ መበስበስ፡፡
የኖርክለት እውነት ሀገር እስኪፈታ፣
በሀቁ እስኪመዘን ስለ በርባን ክብር የቆሸሸው ፍቅር የታሰረው ጌታ፣
ከድል ታሪክ ሰማይ ከሥልጣኔ ዳር ከጥበብ ከፍታ፣
እንሻገራለን ህዝብነትን ትተን ሰው የሆንን ለታ፡፡
በትረ ጥበበ ቢካን ዓለም ሊያንቀጠቅጥ ድል ሥልጣን ቢሰጠው፣
ጀግና መሪ አይደለም ብርቱ ተመሪ ነው ሀገር ሚለውጠው፡፡
አስተውል ወዳጄ ጠልተን ላንጣላ ችለን ላንጋደል ነደን ላንፋጀው፣
የኛው ትርምስ ነው በልቶ ለሚያባላ ጠላት ሚበጀው፡፡
ስጋና ደም እንጂ የአንድነታችን ውል የፍቅራችን ቀለም፣
ያሰመርነው ክልል የታጠርንበት ዘር ቋንቋችን አይደለም፡፡
ከመዋሃድ መቅደስ ትውልድ እናስተምር፣
ዘመን ይመርቀን ፍቅራችን ምን ጎድሎት ደማችን ያስታርቀን፡፡
በልጆቿ አጥንት በደም ኪዳን ምለን የገባንላት ቃል፣
ከጩኀት ያለፈ ዘመን የሚሻገር ተግባር ይጠይቃል፡፡
በአንድ ሃሳብ ተጋምደን በድል ድር እናብር ውድቀታችን ያንቃን፣
ሠርተን እናሳምን ሆነን ድል እንንሳ የአፍ ጀግንነት ይብቃን፡፡
ምስኪኒቷ እናቴ! በሞላ ጎዳና ባልጠበበ ድንበር በዘር ገመድ ታግዳ፣
ነጻ ነኝ ትላለች መንጋነት ያሰረው ባሪያ ትውልድ ወልዳ፡፡
የጀግንነት እብሪት ልባችንን ደፍኖት ማሰብ እየከዳን፣
እንዴት ነው ነጻነት እንዳበደ ፈረስ ስሜት እየነዳን፡፡
ገድሎ የመንገስ ጥማት ጩኀት ላገነነ አመጽ ላጀገነው፣
ለዚህ ምስኪን ትውልድ በጅምላ እየነዱት፣
በመንጋ እያሰበ ነጻነት እንዴት ነው?
ነጻነት ምርጫ ነው አምሮ ቢደላደል ጥፋት ያመነነው የመንጋዎች መንገድ፣
እንቅፋቱን ወዶ ለኖሩለት እውነት ለብቻ መራመድ፡፡
ነጻነት ማመን ነው ቀን ወዶ ቢያጀግን ቀን ጠልቶ ቢከዳም፣
ቢቆሽሹም ቢደምቁም እራስን መቀበል ራስን መምሰል ነው የነጻነት ገዳም፡፡
ነጻነት ማሰብ ነው በአንድነት መለምለም የኔነትን አረም ከህሊና ማጥፋት፣
ዘር ሆኖ ከማነስ ሀገር ሆኖ ማበብ ዓለም ሆኖ መስፋት፡፡
ንገሯት ለሀገሬ በጀግኖቿ ትግል ድንበር ባታስደፍር ከእጀ ገዥ ብትወጣ፣
ነጻ ነኝ እንዳትል በገዛ ልጆቿ በእጅ አዙር ተሸጣ ፡፡
ስሩን ካልሸመነው በመዋሃድ ጥለት በማስተዋል ሸማ፣
ታሪክ አናደምቅም በጭብጨባ ድግስ በሆይ ሆይታ ዜማ፡፡
ምን ብናቀነቅን በየሰልፉ ሜዳ ወኔ ብንደግስም፣
በፈረሰ አይምሮ በደቀቀ አንድነት ሀገር አናድስም፡፡
በጭፍን ከመሮጥ አስቦ ማዝገም ነው የመራመድ ውሉ፣
ሁሉም እንቅፋቶች እስኪጥሉን ድረስ ምርኩዝ ይመስላሉ፡፡
በድፍን ግልብ እሚያጋድል ህዝብ የመሆን መንጋ አይንዳን፣
በማሰብ ስር እንፈወስ በሰውነት ፀበል እንዳን፡፡
ከእግዜር ልንወዳጅ ለምህረቱ ጥላ እምባ ብንደግስም፣
ልብን ሳይመልሱ ለንስሃ መሮጥ ከጽድቅ አያደርስም፡፡
ውብ ነገን እናውርስ ትላንትን አክመን በይቅርታ ፀበል፣
ትውልድ ይጨርሳል ያረገዝነው እምባ የቋጠርነው በቀል፣
ከመስጠት አንጉደል ከቀማኞች ገደል ተረግጠን ብንጣል፣
ካሸከሙን በቀል ምናወርሰው ፍቅር ሀገር ይለውጣል፡፡
ከዕድሏ ጣሪያ ላይ ዘር የቀዳደው ሽንቁሯ ቢበዛም፣
ያ ከንቱ ፎካሪ ባፈጀ ቀረርቶ ሺህ ጉራ ቢነዛም፣
ሚሊዮን ዘር ቢሸጥ አንድ ሀገር አይገዛም፡፡
ኢዮጵያዊነት ነው የትርታችን ልክ የነፍሳችን ግጥም፣
መልስ ቤት በራቀው በከረመ ፀሎት ሰርክ ብታንጋጥም
አጎንብሳ ድሃ ባፀናችው ጉልበት ብትረጋገጥም
ነፍሷን አደህይታ ባሻረችው ቁስል ብትገሸለጥም፣
ሀገር ሆና ገዝፋ በየ ጎጣጎጡ አትርመጠመጥም፡፡
የዘመን እውነት ነን ከደግነት ሰማይ በጥበብ የኖርን፣
ትዕግስትም ልክ አለው ፈርተን እንዳይመስለው ስላቀረቀርን፡፡
ማተብ አስሮን እንጂ ተጣልተን እንዳንቀር በክፍፍል ገደል፣
ከሀገር ክብር በልጦ ሞት ብርቃችን አይደል፡፡
ንገሩት ለዛ ሰው ከዓለም ጫፍ እስከ ጫፍ ኃይል እንደ ተራራ ገዝፎ ቢከመርም፣
ክንዱን አፈርጥሞ እልፍ የሰገደለት ጀግና ቢሰድርም፣
ዓለም የሞተበት የጠላት ማርከሻ ጦር ቢደረድርም፣
በአንድ ዓይናችን ሰላም በኢትዮጵያችን ክብር አንደራደርም!!!
©ሕሊና ደሳለኝ
ኅሊና_ደሳለኝ በአዲስ ዓመት ዋዜማ በቤተ መንግስት
ካቀረበችው ግጥም
@getem
@getem
@getem
ልብ ነው!!!!!
የነፍስህን ጉልበት፤
የአቅምህን ዳርቻ፤
የውስጥህን ቅዋ ፤ መዝኖ ፈራጅ፤
ሃቀኛው መስፈሪያህ፤
አይንህ እንዳይመስል፤ ልቡናህ ነው እንጅ።
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
የነፍስህን ጉልበት፤
የአቅምህን ዳርቻ፤
የውስጥህን ቅዋ ፤ መዝኖ ፈራጅ፤
ሃቀኛው መስፈሪያህ፤
አይንህ እንዳይመስል፤ ልቡናህ ነው እንጅ።
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
"...የሰፋ ሀገር ይዘን፣ ጠቦ መሞት ይብቃን፤..."
(ገጣሚት፥ ህሊና ደሳለኝ)
---------------------
አይችለው የለ እንጂ - የልባም ትከሻ፣
ከውርደቱ ደጃፍ - ነውሩን ማምለጥ ሲሻ፣
ገርፎ ማሳመን ነው፣ የፈሪ ሰው በትር፣ የሽንታም ሰው ጋሻ።
እንመን ግድ የለም…
ፍትሕ አይታለምም - ሐቁን እየሸሹ፣
የጠፋው እንዲገኝ፣ እስኪ መጀመርያ፣ ይፈተሽ ፈታሹ፤
አቀርቅራ ታዝግም፣ ትጎናበስ እንጂ፣ መሔድ እስኪያድላት፣
ሰብረህ ስታበቃ፣ 'ምርኩዝ እንቺ' ብለህ ደርሰህ አትደልላት፤
'በኔ ብቻ' በሽታ - ጥበት እየቀጣን፣
በ'ናታችን ርስት፣ ባባታችን መሬት፣ መደገፊያ እያጣን፤
ቁልቁል እያሰቡ - ምንድነው ከፍታ፣
መብት እየነጠቁ - ምንድነው ግዴታ?
እስከ መቼ ተረት - ግዴለም ይነጋል፣
መንገድ እየቀሙ - ምርኩዝ ምን ያደርጋል?
አንተ እንደሁ ልማድህ አለስልሶ መግደል አሳስቆ መግፋት፣
'ካብኩ' እያሉ 'ማቅለል' 'ሳምኩ' እያሉ 'መትፋት'፣
የበደል ላይ ጀግና - ሬሳ ላይ መዛት፣
መዋረድን ሽሽት - የአሽቃባጭ አፍ መግዛት፤
እየሸሹ ትግል - እየሮጡ ዛቻ፣
በጉንዳን ልቡና - የነብር ዘመቻ፤
የበላ እያሠረ - የቀማ ቢገፈው፣
የሳተ እያረመ - ያጠፋ ቢገርፈው፤
ጀግና ልማዱ ነው፣ ባርያ ሆኖ ታሽቶ፣ ንጉሥ ኾኖ መግዛት፣
እያነሰ ገዝፎ - እየሞተ መብዛት፤
ያ ሽንታም ላመሉ - በሬሳ ይፎክራል፣
ከፈሪ ገዳይ 'ድል' - የጀግና 'ሞት' ያምራል፤
ይልቅ……
በእኔ ልቅደም ትርክት- የዘር ደዌ አያጥቃን፣
ከጎጥ ቀንበር ፍቱን - ጠቦ መሞት በቃን፤
የጸደይ ወይን ኾኖ - የሐቅ እንባ ቢጥም፣
በድሎ መጀገን - ጀብድ ሆኖ ቢረግጥም፣
የትግላችን ልኩ - ያሳር ደም ቢያስምጥም፣
በሰፋ ሀገር ጠበን - ኢትዮጵያን አንሰጥም!!!
@getem
@getem
@gebriel_19
(ገጣሚት፥ ህሊና ደሳለኝ)
---------------------
አይችለው የለ እንጂ - የልባም ትከሻ፣
ከውርደቱ ደጃፍ - ነውሩን ማምለጥ ሲሻ፣
ገርፎ ማሳመን ነው፣ የፈሪ ሰው በትር፣ የሽንታም ሰው ጋሻ።
እንመን ግድ የለም…
ፍትሕ አይታለምም - ሐቁን እየሸሹ፣
የጠፋው እንዲገኝ፣ እስኪ መጀመርያ፣ ይፈተሽ ፈታሹ፤
አቀርቅራ ታዝግም፣ ትጎናበስ እንጂ፣ መሔድ እስኪያድላት፣
ሰብረህ ስታበቃ፣ 'ምርኩዝ እንቺ' ብለህ ደርሰህ አትደልላት፤
'በኔ ብቻ' በሽታ - ጥበት እየቀጣን፣
በ'ናታችን ርስት፣ ባባታችን መሬት፣ መደገፊያ እያጣን፤
ቁልቁል እያሰቡ - ምንድነው ከፍታ፣
መብት እየነጠቁ - ምንድነው ግዴታ?
እስከ መቼ ተረት - ግዴለም ይነጋል፣
መንገድ እየቀሙ - ምርኩዝ ምን ያደርጋል?
አንተ እንደሁ ልማድህ አለስልሶ መግደል አሳስቆ መግፋት፣
'ካብኩ' እያሉ 'ማቅለል' 'ሳምኩ' እያሉ 'መትፋት'፣
የበደል ላይ ጀግና - ሬሳ ላይ መዛት፣
መዋረድን ሽሽት - የአሽቃባጭ አፍ መግዛት፤
እየሸሹ ትግል - እየሮጡ ዛቻ፣
በጉንዳን ልቡና - የነብር ዘመቻ፤
የበላ እያሠረ - የቀማ ቢገፈው፣
የሳተ እያረመ - ያጠፋ ቢገርፈው፤
ጀግና ልማዱ ነው፣ ባርያ ሆኖ ታሽቶ፣ ንጉሥ ኾኖ መግዛት፣
እያነሰ ገዝፎ - እየሞተ መብዛት፤
ያ ሽንታም ላመሉ - በሬሳ ይፎክራል፣
ከፈሪ ገዳይ 'ድል' - የጀግና 'ሞት' ያምራል፤
ይልቅ……
በእኔ ልቅደም ትርክት- የዘር ደዌ አያጥቃን፣
ከጎጥ ቀንበር ፍቱን - ጠቦ መሞት በቃን፤
የጸደይ ወይን ኾኖ - የሐቅ እንባ ቢጥም፣
በድሎ መጀገን - ጀብድ ሆኖ ቢረግጥም፣
የትግላችን ልኩ - ያሳር ደም ቢያስምጥም፣
በሰፋ ሀገር ጠበን - ኢትዮጵያን አንሰጥም!!!
@getem
@getem
@gebriel_19
👍1
✍እኔና አንቺ!✍
( በረከት በላይነህ).
በጥምር ነፍሳችን ፣ አረፍ ስንልበት ጨለማው ወገገ፤
ፈጣሪ ተገርሞ ለደስታ ፍቺ አዲስ ቃል ፈለገ።
እኔና አንቺን እኮ!
አበቦቹ ያጅቡናል፣
ፍራፍሬው ይከበናል፤
ሕይወት ጉንጯ ሲንቆረቆር ይሰማናል።
ወፎቹ!
እኔና አንቺን አይተው ተቃቅፈው በረሩ፤
ከጨረቃ ታርቀው በምሽት በረሩ።
ኮከቦቹ!
" ጨረቃ ወለደች! " እየተባባሉ፤
ከእኛ ተጠግተው ብርሀን ተሞሉ።
በቀቀኖች እንኳን!
ከፃድቃን ቃል ውጭ መድገም የማይችሉ፤
ከእኛ ሳቅ በሁዋላ " ድምፅ ሰማን! " አሉ።
‘ ባክሽ እንዳይገርምሽ!
በእኛ ሲከፋፈት ~ የምድር የሰማይ በር፣
እንዲህ ቀልቡን ሲሰጥ ~ የአዕዋፍ የአራዊተ ዘር ፣
ሁሉን ይሸምታል ~ ፍቅር ሲዘረዘር።
@getem
@getem
@getem
( በረከት በላይነህ).
በጥምር ነፍሳችን ፣ አረፍ ስንልበት ጨለማው ወገገ፤
ፈጣሪ ተገርሞ ለደስታ ፍቺ አዲስ ቃል ፈለገ።
እኔና አንቺን እኮ!
አበቦቹ ያጅቡናል፣
ፍራፍሬው ይከበናል፤
ሕይወት ጉንጯ ሲንቆረቆር ይሰማናል።
ወፎቹ!
እኔና አንቺን አይተው ተቃቅፈው በረሩ፤
ከጨረቃ ታርቀው በምሽት በረሩ።
ኮከቦቹ!
" ጨረቃ ወለደች! " እየተባባሉ፤
ከእኛ ተጠግተው ብርሀን ተሞሉ።
በቀቀኖች እንኳን!
ከፃድቃን ቃል ውጭ መድገም የማይችሉ፤
ከእኛ ሳቅ በሁዋላ " ድምፅ ሰማን! " አሉ።
‘ ባክሽ እንዳይገርምሽ!
በእኛ ሲከፋፈት ~ የምድር የሰማይ በር፣
እንዲህ ቀልቡን ሲሰጥ ~ የአዕዋፍ የአራዊተ ዘር ፣
ሁሉን ይሸምታል ~ ፍቅር ሲዘረዘር።
@getem
@getem
@getem
❤1
የማምሻ ዱብ ዕዳ!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።።
ዓይኔ ሲቀላውጥ
አፌ ሰርቆ ሲውጥ
ዝም ያለኝ ልጋጋም
የግዜር እሾህ አጋም
ቀን እየጠበቀ.. .
ጊዜ እየሰረቀ..
እልፍ ዓመታት ቆጥሮ ፣ ሸንግሎ በዘመን
ብሎ እንኖራለን!
ገና ብዙ ስፍር.. . የዓመት ብዝሀ
አንዱ ለሀጥያት ፣ አንዱ ለንሰሃ
በሚል ከንቱ ምኞት.. .
ጉም እያስጨበጠ ፣ ቀናት እያስገፋ
በከሰመ ተስፋ
ዝም ብሎ ዝም ብሎ
መንፈሴን ሸንግሎ
ኗሪ ነኝ እያልሁኝ.. .
ስዘርፍ ፣ ስሳረር
ስሰርቅ ፣ ስናገር
ስገድል.. .ስቀጣ
እጆቼን ለበደል ፥ ዘርግቼ ስቃጣ
ዝም ብሎኝ የነበር ...
የሞቴ መልዐክ ፥ ሰተት ብሎ መጣ።
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።።
ዓይኔ ሲቀላውጥ
አፌ ሰርቆ ሲውጥ
ዝም ያለኝ ልጋጋም
የግዜር እሾህ አጋም
ቀን እየጠበቀ.. .
ጊዜ እየሰረቀ..
እልፍ ዓመታት ቆጥሮ ፣ ሸንግሎ በዘመን
ብሎ እንኖራለን!
ገና ብዙ ስፍር.. . የዓመት ብዝሀ
አንዱ ለሀጥያት ፣ አንዱ ለንሰሃ
በሚል ከንቱ ምኞት.. .
ጉም እያስጨበጠ ፣ ቀናት እያስገፋ
በከሰመ ተስፋ
ዝም ብሎ ዝም ብሎ
መንፈሴን ሸንግሎ
ኗሪ ነኝ እያልሁኝ.. .
ስዘርፍ ፣ ስሳረር
ስሰርቅ ፣ ስናገር
ስገድል.. .ስቀጣ
እጆቼን ለበደል ፥ ዘርግቼ ስቃጣ
ዝም ብሎኝ የነበር ...
የሞቴ መልዐክ ፥ ሰተት ብሎ መጣ።
@getem
@getem
@getem