እኔ ያለሁት ማርስ፣ አንቺ ቬነስ ማዶ
የውስጤን ነበልባል፣ ለመላክ ተስኖት፣ ልቤ አለቀ ነዶ።
፨ ፨ ፨
በእግሬ አልመጣ ነገር ፣ ያለሁት ማርስ ላይ
መልእክቴን የሚያደርስ ፣ ቢጠፋም አገልጋይ
ምንም ቢወላገድ ፣ ቋንቋዬም ባይጠራ
ቀንቶኝ እንደ ሰለሞን ፣ ንፋሱ ሲግራራ
ልጣፍ ቢያደርስልኝ ፣ ካለሺበት ሥፍራ።
፨ ፨ ፨
ብታዪኝ ሆድዬ
ሌጣዬን ቁጭ ብዬ፤
፤የማርሱ ኖሕ ሆኜ
ላለመስጠም ብዬ ፣ በናፍቆትሽ እንባ
ልሰራ ስል ጀልባ
ቁሳቁስ አጣሁኝ ፣ ለኔ የሚረባ።
፨ ፨ ፨
እኔ ያለሁት ማርስ፣ አንቺ ቬነስ ማዶ
የውስጤን ነበልባል፣ ለመላክ ተስኖት፣ ልቤ አለቀ ነዶ
መራራቁም ሰፋ ፣ በምንም ተጋርዶ።
፨ ፨ ፨
መንታ ጭንቅ ጥሎ ፣ የኮቴሽ መጥፋቱ
መራራ ሆነብኝ ፣ የማርስ ላይ ስደቱ
ቀኝ ቀኙን ሳስበው ፣ ያንቺ መበርታቱ
ስሜትሺን ሚረዳ ፣ ጓደኛ ማጣቱ።
፨ ፨ ፨
መንኮራኩር ባጣ ፣ መንገዱ ባይቀና
ሞገድ ልላክልሽ ፣ በሙዚቃ ቃና
"ሰላም ነሽ ወይ ጤና ፣ ድምፅሽ ጠፋ ምነው
ተስማማሽ ወይ ኑሮ?አገሩስ እንዴት ነው?"
፨ ፨ ፨
ዝምታሽ ሲበዛ ፣ ባሰብኝ ከመርዶ
እኔ ያለሁት ማርስ፣ አንቺ ቬነስ ማዶ
የውስጤን ነበልባል፣ ለመላክ ተስኖት፣ ልቤ አለቀ ነዶ
መራራቁም ሰፋ ፣ በምንም ተጋርዶ።
፨ ፨ ፨
ውዴ ከ(ካል)ተረዳሽየኔን የማርስ ቋንቋ
እንዳልኩት ንፋሱ አድርሶልኝ ካንቺ
በቃ ሁሉን እርሺው ስጪው ባዶ ፍቺ
ቁስልሺን ሊወጋሽ ፣ ላይሆንሽ መዳኛ
ቢገባሺም ተዪው
ከቁብ አትቁጠሪው
ይህን ፣ የማርስ ስደተኛ
~~~~~~ነውና ወረኛ።
ረያን አብዱ(@Rethepac)
ቀን 4:24~28-07-2011~
ደብረሲና
@getem
@getem
@getem
የውስጤን ነበልባል፣ ለመላክ ተስኖት፣ ልቤ አለቀ ነዶ።
፨ ፨ ፨
በእግሬ አልመጣ ነገር ፣ ያለሁት ማርስ ላይ
መልእክቴን የሚያደርስ ፣ ቢጠፋም አገልጋይ
ምንም ቢወላገድ ፣ ቋንቋዬም ባይጠራ
ቀንቶኝ እንደ ሰለሞን ፣ ንፋሱ ሲግራራ
ልጣፍ ቢያደርስልኝ ፣ ካለሺበት ሥፍራ።
፨ ፨ ፨
ብታዪኝ ሆድዬ
ሌጣዬን ቁጭ ብዬ፤
፤የማርሱ ኖሕ ሆኜ
ላለመስጠም ብዬ ፣ በናፍቆትሽ እንባ
ልሰራ ስል ጀልባ
ቁሳቁስ አጣሁኝ ፣ ለኔ የሚረባ።
፨ ፨ ፨
እኔ ያለሁት ማርስ፣ አንቺ ቬነስ ማዶ
የውስጤን ነበልባል፣ ለመላክ ተስኖት፣ ልቤ አለቀ ነዶ
መራራቁም ሰፋ ፣ በምንም ተጋርዶ።
፨ ፨ ፨
መንታ ጭንቅ ጥሎ ፣ የኮቴሽ መጥፋቱ
መራራ ሆነብኝ ፣ የማርስ ላይ ስደቱ
ቀኝ ቀኙን ሳስበው ፣ ያንቺ መበርታቱ
ስሜትሺን ሚረዳ ፣ ጓደኛ ማጣቱ።
፨ ፨ ፨
መንኮራኩር ባጣ ፣ መንገዱ ባይቀና
ሞገድ ልላክልሽ ፣ በሙዚቃ ቃና
"ሰላም ነሽ ወይ ጤና ፣ ድምፅሽ ጠፋ ምነው
ተስማማሽ ወይ ኑሮ?አገሩስ እንዴት ነው?"
፨ ፨ ፨
ዝምታሽ ሲበዛ ፣ ባሰብኝ ከመርዶ
እኔ ያለሁት ማርስ፣ አንቺ ቬነስ ማዶ
የውስጤን ነበልባል፣ ለመላክ ተስኖት፣ ልቤ አለቀ ነዶ
መራራቁም ሰፋ ፣ በምንም ተጋርዶ።
፨ ፨ ፨
ውዴ ከ(ካል)ተረዳሽየኔን የማርስ ቋንቋ
እንዳልኩት ንፋሱ አድርሶልኝ ካንቺ
በቃ ሁሉን እርሺው ስጪው ባዶ ፍቺ
ቁስልሺን ሊወጋሽ ፣ ላይሆንሽ መዳኛ
ቢገባሺም ተዪው
ከቁብ አትቁጠሪው
ይህን ፣ የማርስ ስደተኛ
~~~~~~ነውና ወረኛ።
ረያን አብዱ(@Rethepac)
ቀን 4:24~28-07-2011~
ደብረሲና
@getem
@getem
@getem
👍1
ክፉ እድሌ ነሽ
አዎ ያኔ ነበርሽ....ሰማይ ተከድኖብኝ
ምድር ስትዞርብኝ
ህያዋን ግዑዛን ሁሉ ሲከፉብኝ
አንቺ ግን ከጎኔ ላፍታ ሳትለዪኝ
ሁሉም ቀናቶች ላይ አሻራ አኖርሽልኝ፡፡
በድካም ዝለቴ
በጭንቀት ጥበቴ
ተከፍቼ ሳዝን
አዝኜ ስባዝን
በሁሉም ዉድቀቴ
በሁሉም ጉድለቴ
አንቺ አብረሺኝ ነበርሽ ውዷ እመቤቴ፡፡
መቼም ማረሳቸዉ ከዉስጤ ማይጠፉ
በልቤ ፅላት ላይ ደምቀው የተፃፉ
እነኛ አብሮነትሽ እንዳሸን የፈሉ
ነፍሴን ብሰዋትስ መች ይከፈላሉ ፤
አንቺ ኮ ልዩ ነሽሁሌ ትገኛለሽ
በክፉ በመጥፎ ቀናቶቼ አለሽ፡፡
ስሚኝማ ውዴ ያ ቀን ትዝ ይልሻል
ያኔ ተመርቄ እንዲያ ስፈነጥዝ
በደስታ ሰክሬ ጢንቢራዬ ሲጦዝ
አያትሽ ሞቱና ሄደሽ ወደ ገጠር
በደስታዬ ቀን ላይ አንቺ አዝነሽ ነበር፡፡
ደሞ ሚያዚያ ወር በአስራምስተኛው ቀን
ለልደቴ ድምቀት አንቺን ስተማመን
ሲበዛ በፅኑ ታመምሺብኝና
ሳስታምምሽ ዋልኩኝ ልደቱም ቀረና፡፡
እና እቴሜቴ አንቺ የኔመቤት
ሳስብ ሳሰላስል ዘልቄ በጥልቀት
እውነቱን ተረዳው እንዲ የሆንሽበት
በሰቆቃዬ ቀን ከጎኔ እየሆንሽ
ፍስሀ ሲሆንልኝ ከቶ ካልተገኘሽ
እንቅጩን ልንገርሽ
..............አንቺ ማለት ለኔ ክፉ እድሌ ነሽ
@selamfikadu
@getEm
@getem
አዎ ያኔ ነበርሽ....ሰማይ ተከድኖብኝ
ምድር ስትዞርብኝ
ህያዋን ግዑዛን ሁሉ ሲከፉብኝ
አንቺ ግን ከጎኔ ላፍታ ሳትለዪኝ
ሁሉም ቀናቶች ላይ አሻራ አኖርሽልኝ፡፡
በድካም ዝለቴ
በጭንቀት ጥበቴ
ተከፍቼ ሳዝን
አዝኜ ስባዝን
በሁሉም ዉድቀቴ
በሁሉም ጉድለቴ
አንቺ አብረሺኝ ነበርሽ ውዷ እመቤቴ፡፡
መቼም ማረሳቸዉ ከዉስጤ ማይጠፉ
በልቤ ፅላት ላይ ደምቀው የተፃፉ
እነኛ አብሮነትሽ እንዳሸን የፈሉ
ነፍሴን ብሰዋትስ መች ይከፈላሉ ፤
አንቺ ኮ ልዩ ነሽሁሌ ትገኛለሽ
በክፉ በመጥፎ ቀናቶቼ አለሽ፡፡
ስሚኝማ ውዴ ያ ቀን ትዝ ይልሻል
ያኔ ተመርቄ እንዲያ ስፈነጥዝ
በደስታ ሰክሬ ጢንቢራዬ ሲጦዝ
አያትሽ ሞቱና ሄደሽ ወደ ገጠር
በደስታዬ ቀን ላይ አንቺ አዝነሽ ነበር፡፡
ደሞ ሚያዚያ ወር በአስራምስተኛው ቀን
ለልደቴ ድምቀት አንቺን ስተማመን
ሲበዛ በፅኑ ታመምሺብኝና
ሳስታምምሽ ዋልኩኝ ልደቱም ቀረና፡፡
እና እቴሜቴ አንቺ የኔመቤት
ሳስብ ሳሰላስል ዘልቄ በጥልቀት
እውነቱን ተረዳው እንዲ የሆንሽበት
በሰቆቃዬ ቀን ከጎኔ እየሆንሽ
ፍስሀ ሲሆንልኝ ከቶ ካልተገኘሽ
እንቅጩን ልንገርሽ
..............አንቺ ማለት ለኔ ክፉ እድሌ ነሽ
@selamfikadu
@getEm
@getem
👍1
ላይሰጥ አያስችልም
(ቡሩክ ካሳሁን)
ከእንጨቶች ይልቅ አንገት ይበረታል
አንገት ይደነቃል
ከዝሆን የሚከብድ ሃሳብ ተሸክሞ መች ተሰብሮ ያውቃል
እፁብ ድንቅ እላለሁ ይህን ተመልክቼ
ዳግም አስባለሁ ባ'ንገቴ ፅኑነት ይበልጥ ተመክቼ
እሱ አያልቅበት እንበል እንጂ መገን
ፅኑ አንገት ሲሰጠን መች ሃሳብ ነፈገን?!
ቀድሞም አስቦ ነው ብርቱ አንገት የሰጠን
በሀሳብ አፍላቂነት ከአሸን ሊያወዳጀን
ስለዚህ አንተ ሰው ሰፊ ጫንቃ ካለህ
ሰፋፊ ችግሮች ትሸከማታለህ፡፡
ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል
@burukassahunC
@getem
@getem
(ቡሩክ ካሳሁን)
ከእንጨቶች ይልቅ አንገት ይበረታል
አንገት ይደነቃል
ከዝሆን የሚከብድ ሃሳብ ተሸክሞ መች ተሰብሮ ያውቃል
እፁብ ድንቅ እላለሁ ይህን ተመልክቼ
ዳግም አስባለሁ ባ'ንገቴ ፅኑነት ይበልጥ ተመክቼ
እሱ አያልቅበት እንበል እንጂ መገን
ፅኑ አንገት ሲሰጠን መች ሃሳብ ነፈገን?!
ቀድሞም አስቦ ነው ብርቱ አንገት የሰጠን
በሀሳብ አፍላቂነት ከአሸን ሊያወዳጀን
ስለዚህ አንተ ሰው ሰፊ ጫንቃ ካለህ
ሰፋፊ ችግሮች ትሸከማታለህ፡፡
ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል
@burukassahunC
@getem
@getem
(Ati TaAdi)
❤️❤️እናቴ❤️❤️
"እናቴ" የኔ አመል ክፉ ነው😡
ማንም የማይችለው😔😔
ተነጫናጭ እና ብስጩ ፀባይ ነው
"እናቴ"ሁሉም አቅቶታል
ፀባዬን መሸከም😒😒😒
ሁሉም ይርቀኛል ክፉ ያደርገኛል😥
ሲያምረኝ ይቅር እንጂ "እማ"
ልክ እንዳንቺ ማን ያባብለኛል😕
እማ❤️ አንቺ ብትሆኚማ
ያ ብስጩ ፀባዬን ያ እሳት ፀባዬን
በፍቅርሽ አብርደሽ ያመናጨኩሽን
ያየጮውኩብሽን
ሁሉንም እረስተሽ ❤️❤️❤️
ናልኝ ልጄ እያልሽ ታባብይኛለሽ
እናቴ አንቺ ነሽ እረፍቴ
አንቺ ነሽ ሰላሜ
የመኖሬ ትርጉም ነሽ የዘላለሜ
እማ ናፍቀሽኛል😔😔😔
ለኔ ካንቺ ውጪ ሰው አስጠልቶኛል
ያመሌ ወዝ አደር የኔ ተሸካሚ😒
የፍቅር ዋሻዬ አይዞህ ልጄ ባዬ
ጥበብ አስተማሪ አንቺ የኔታዬ
አጥንቴ ይድቀቅልሽ
ስጋዬ ይፈጭልሽ
እኔ ባንቺ ቦታ ባዶ ልሁንልሽ🌓🌓
ያንቺን ቅጣት ለኔ ያርገው ፈጣሪዬ
አንቺ እናት አለሜ
ሰላምሽ ይብዛልኝ💋💋
የሚወድሽ አምላክ
በእድሜ ላይ እድሜ
በጤና ላይ ጤና
ጨምሮ ይስጥልኝ
ሌላምለው የለም
የምልሽ እሄው ነው
ብቻ አንድ ቃል አለኝ
ላንቺ የምሰጠው
ውቧ እናት አለሜ
የኔ ልዩ ፍጥረት
ሁሌም ወድሻለው 💋💋❤️❤️
ያምላኬ በረከት😔😔😔😔
Ati TaAdi
19-04-2011
4:50 PM
@getem
@getem
❤️❤️እናቴ❤️❤️
"እናቴ" የኔ አመል ክፉ ነው😡
ማንም የማይችለው😔😔
ተነጫናጭ እና ብስጩ ፀባይ ነው
"እናቴ"ሁሉም አቅቶታል
ፀባዬን መሸከም😒😒😒
ሁሉም ይርቀኛል ክፉ ያደርገኛል😥
ሲያምረኝ ይቅር እንጂ "እማ"
ልክ እንዳንቺ ማን ያባብለኛል😕
እማ❤️ አንቺ ብትሆኚማ
ያ ብስጩ ፀባዬን ያ እሳት ፀባዬን
በፍቅርሽ አብርደሽ ያመናጨኩሽን
ያየጮውኩብሽን
ሁሉንም እረስተሽ ❤️❤️❤️
ናልኝ ልጄ እያልሽ ታባብይኛለሽ
እናቴ አንቺ ነሽ እረፍቴ
አንቺ ነሽ ሰላሜ
የመኖሬ ትርጉም ነሽ የዘላለሜ
እማ ናፍቀሽኛል😔😔😔
ለኔ ካንቺ ውጪ ሰው አስጠልቶኛል
ያመሌ ወዝ አደር የኔ ተሸካሚ😒
የፍቅር ዋሻዬ አይዞህ ልጄ ባዬ
ጥበብ አስተማሪ አንቺ የኔታዬ
አጥንቴ ይድቀቅልሽ
ስጋዬ ይፈጭልሽ
እኔ ባንቺ ቦታ ባዶ ልሁንልሽ🌓🌓
ያንቺን ቅጣት ለኔ ያርገው ፈጣሪዬ
አንቺ እናት አለሜ
ሰላምሽ ይብዛልኝ💋💋
የሚወድሽ አምላክ
በእድሜ ላይ እድሜ
በጤና ላይ ጤና
ጨምሮ ይስጥልኝ
ሌላምለው የለም
የምልሽ እሄው ነው
ብቻ አንድ ቃል አለኝ
ላንቺ የምሰጠው
ውቧ እናት አለሜ
የኔ ልዩ ፍጥረት
ሁሌም ወድሻለው 💋💋❤️❤️
ያምላኬ በረከት😔😔😔😔
Ati TaAdi
19-04-2011
4:50 PM
@getem
@getem
👍4
አንቺ ና ስትዪኝ ፣ መንገዶች ቢያርጉ
መንገድ ጠራጊዎች ፣ መንገድ ቢፈልጉ
መንገድ በሚሰሩ ፣ መንገዶች ቢዘጉ
መንገድ የጀመሩ
ከመንገድ ቢቀሩ
መሔጃ ባይኖርም
ክንፍ አውጥቼ ባልበር ፣ እግሬ ቢሰበርም
መስዋእት ሆኜ ፣ ከፍዬልሽ ዋጋ
አልቀርም አንቺጋ
በህልምሽ መጣለሁ ፣ ህልሜ ካልተዘጋ
(በላይ በቀለ ወያ)
@getem
@getem
@lula_al_greeko
መንገድ ጠራጊዎች ፣ መንገድ ቢፈልጉ
መንገድ በሚሰሩ ፣ መንገዶች ቢዘጉ
መንገድ የጀመሩ
ከመንገድ ቢቀሩ
መሔጃ ባይኖርም
ክንፍ አውጥቼ ባልበር ፣ እግሬ ቢሰበርም
መስዋእት ሆኜ ፣ ከፍዬልሽ ዋጋ
አልቀርም አንቺጋ
በህልምሽ መጣለሁ ፣ ህልሜ ካልተዘጋ
(በላይ በቀለ ወያ)
@getem
@getem
@lula_al_greeko
*ላ'ንዲት ሴት የተፃፉ ሶስት የፍቅር*😍😜 ደብዳቤዎች
ለራስ ያለ እውነት
ልክ እንደ 'ፋውንቴን' ከውስጥ ገንፍሎ ለውጩ ይተርፋል
አፍቃሪ ሆዳም ሰው
ከሆዱ ላለች ሴት ከሆዱ ባለው ልክ የሆዱን ይፅፋል
"ዳሌሽ አገልግል ነው - ቅቅል ነው ደረትሽ
ባ'ስራ ሁለት ቅመም
ጣፍጦ የተሰራ ያ'በሻ ዶሮ ወጥ ይመስለኛል ፊትሽ
ክትፎ ነው ከንፈርሽ - ሽፍታ ጥብስ አንገትሽ
ኮተት ያልበዛበት ወገብሽ ሠላጣ
ጡቶችሽ ክሬም ኬክ - ጭኖችሽ ሚጥሚጣ
ተርቤአለሁ ባንቺ እሺ በይኝ ልምጣ"
ለሆዳም አፍቃሪ - የሚያፈቅራት እንስት - ቡፌ ነው ውበቷ
ለመብል የታጨ በ'ያይነት ነው ፊቷ
ለራስ ያለ እውነት
ልክ እንደ 'ፋውንቴን' ከውስጥ ገንፍሎ ለውጩ ይተርፋል
አፍቃሪ ሰካራም
ከሆዱ ላለች ሴት ከሆዱ ባለው ልክ የሆዱን ይፅፋል
"ዳሌሽ ብላክ ሌብል - ሻምፓኝ ነው ደረትሽ
የፈረንሳይን ወይን ያስታውሰኛል ፊትሽ
ከንፈርሽ ጊዮርጊስ - ዳሽን ነው አንገትሽ
ጡቶችሽ ቄንጠኛ የወይን መጠጫ
የጠጅ ብርሌ ክብ መቀመጫ
አረቂ ፈገግታሽ ነፍስ ያንቀጠቅጣል
ደረቅ ጅን ነው ጭንሽ
ባንድ እይታ ብቻ አናት ላይ ይወጣል
እባክሽ ፍቅሬ ሆይ
እሺ በይኝና ዓለምን እንቅጫት
ነፍሴን ከፍቅርሽ ወይን ቀድተሽ አጠጫት"
ለጠጪ አፍቃሪ - የሚያፈቅራት እንስት - ኪወስክ ነው ፊቷ
ቢራ ነው ቁመቷ - አረቂ ነው መልኳ - ወይን ነው ውበቷ
ለራስ ያለ እውነት
ልክ እንደ 'ፋውንቴን' ከውስጥ ገንፍሎ ለውጩ ይተርፋል
አፍቃሪ ደራሲ
ከልቡ ላለች ሴት ከልቡ ባለው ልክ የልቡን ይፅፋል
"ጭኖችሽ ትኩሳት - ፈገግታሽ ዙቤይዳ
ልብ የሚያንጠለጥል ወሬሽ ዴርቶጋዳ
የልም ዣት ነው ዳሌሽ - ደረትሽ አደፍርስ
ዓይኖችሽ የንስር ኑ ግድግዳ እናፍርስ
ውበትሽ ረቂቅ እሳት ወይ አበባ
የልብ ማኅተም አንገትሽ ወለባ
አንብቢኝ ላንብብሽ ተረጃት እውነቴን
ዡልየቴ ሁኝልኝ ሮሜዎሽ ልሁን ውሰጃት ህይዎቴን"
ላፍቃሪ ደራሲ - የሚያፈቅራት እንስት - ድርሰት ነው ውበቷ
ቅኔ ነው ቀለሟ - ቴአትር ነው መልኳ - ልብ ወለድ ነው ፊቷ
እሷ ግን እሷ ነች
ምግብም መጠጥም መፅሐፍም አይደለች
(ደሱ ፍቅረኤል)😍😂
@getem👈
@getem👈
@kaleab_1888
ለራስ ያለ እውነት
ልክ እንደ 'ፋውንቴን' ከውስጥ ገንፍሎ ለውጩ ይተርፋል
አፍቃሪ ሆዳም ሰው
ከሆዱ ላለች ሴት ከሆዱ ባለው ልክ የሆዱን ይፅፋል
"ዳሌሽ አገልግል ነው - ቅቅል ነው ደረትሽ
ባ'ስራ ሁለት ቅመም
ጣፍጦ የተሰራ ያ'በሻ ዶሮ ወጥ ይመስለኛል ፊትሽ
ክትፎ ነው ከንፈርሽ - ሽፍታ ጥብስ አንገትሽ
ኮተት ያልበዛበት ወገብሽ ሠላጣ
ጡቶችሽ ክሬም ኬክ - ጭኖችሽ ሚጥሚጣ
ተርቤአለሁ ባንቺ እሺ በይኝ ልምጣ"
ለሆዳም አፍቃሪ - የሚያፈቅራት እንስት - ቡፌ ነው ውበቷ
ለመብል የታጨ በ'ያይነት ነው ፊቷ
ለራስ ያለ እውነት
ልክ እንደ 'ፋውንቴን' ከውስጥ ገንፍሎ ለውጩ ይተርፋል
አፍቃሪ ሰካራም
ከሆዱ ላለች ሴት ከሆዱ ባለው ልክ የሆዱን ይፅፋል
"ዳሌሽ ብላክ ሌብል - ሻምፓኝ ነው ደረትሽ
የፈረንሳይን ወይን ያስታውሰኛል ፊትሽ
ከንፈርሽ ጊዮርጊስ - ዳሽን ነው አንገትሽ
ጡቶችሽ ቄንጠኛ የወይን መጠጫ
የጠጅ ብርሌ ክብ መቀመጫ
አረቂ ፈገግታሽ ነፍስ ያንቀጠቅጣል
ደረቅ ጅን ነው ጭንሽ
ባንድ እይታ ብቻ አናት ላይ ይወጣል
እባክሽ ፍቅሬ ሆይ
እሺ በይኝና ዓለምን እንቅጫት
ነፍሴን ከፍቅርሽ ወይን ቀድተሽ አጠጫት"
ለጠጪ አፍቃሪ - የሚያፈቅራት እንስት - ኪወስክ ነው ፊቷ
ቢራ ነው ቁመቷ - አረቂ ነው መልኳ - ወይን ነው ውበቷ
ለራስ ያለ እውነት
ልክ እንደ 'ፋውንቴን' ከውስጥ ገንፍሎ ለውጩ ይተርፋል
አፍቃሪ ደራሲ
ከልቡ ላለች ሴት ከልቡ ባለው ልክ የልቡን ይፅፋል
"ጭኖችሽ ትኩሳት - ፈገግታሽ ዙቤይዳ
ልብ የሚያንጠለጥል ወሬሽ ዴርቶጋዳ
የልም ዣት ነው ዳሌሽ - ደረትሽ አደፍርስ
ዓይኖችሽ የንስር ኑ ግድግዳ እናፍርስ
ውበትሽ ረቂቅ እሳት ወይ አበባ
የልብ ማኅተም አንገትሽ ወለባ
አንብቢኝ ላንብብሽ ተረጃት እውነቴን
ዡልየቴ ሁኝልኝ ሮሜዎሽ ልሁን ውሰጃት ህይዎቴን"
ላፍቃሪ ደራሲ - የሚያፈቅራት እንስት - ድርሰት ነው ውበቷ
ቅኔ ነው ቀለሟ - ቴአትር ነው መልኳ - ልብ ወለድ ነው ፊቷ
እሷ ግን እሷ ነች
ምግብም መጠጥም መፅሐፍም አይደለች
(ደሱ ፍቅረኤል)😍😂
@getem👈
@getem👈
@kaleab_1888
❤1👍1
ናማ ! እንዋቀስ
--------------
ስልቻህን ጭነህ ፥ በግልገሏ ጥጃ
በዝግማኔ ጉዞ ፣ በኤሊ እርምጃ
ላትጠጋ ዝንዝር ፥ ላትሔድ እርቀህ
በመዳሰስ እምነት ፣ በቀልን ሸምቀህ
በጎሣ ስካሪ ፣ እሽክርክሪት ናውዘህ
አያትህ ባኘኩ...
ያንተ ጥርስ ይቦርቦር ፣ ለምን ትለኛለህ ?
.
በ' ጠል ከመረስረስ ፣ አንተን ከከለለህ
ከሞላው ሳር ክዳን፥አንዲት ሙጃ መዘህ
ስለ ሙሉ ጎጆ ፣ ለምን ታውራለህ?
እንኳንስ በሐገር ፥ በትልቋ መድረክ
ከቤተሰብህ ስር ፣ አንተም ነጠላ ነክ
አባትህ በበላው ፣ የማይሞላ ሆድክ
.
አይታመም ጥርስህ ፣ ባያትህ እኝካት
ጭንቅላትህ አይዙር
በከረመች ድፍድፍ ፣ አባትህ በጠጣት
በልሐ ልበልህ ፥ ናማ ! እንዋቀስ
በስልጡን እይታ በቃላት እንገስግስ
እንደ ላሜ ቦራ...
ከታች እየታለብክ ፥ አሞሌን አትላስ
በስሜት ብዕርህ ፣ ታሪክን አትውቀስ
እንደ ጠላ አሻሮ
ለቆላህ ሰው ሁሉ ፥ በገፍ አትታመስ
በላ መልስልኝ…
እነሱን ባባላች ፣ በድፍርስ አተላ
አባትህ አባቴ ፣ ባነገቧት ዱላ
እንደምን አድርጌ ፣ ካንተ ጋር ልጣላ?
.
ከእርሻው መስክ ላይ፥ከውድማው ራስ
ከወጣህ በኋላ ፥ እርፍ ይዘህ አትመለስ
እንደ ደጀን በሬ ፣ እፊት…ፊቱን እረስ
ኋሊትን ላትይዘው...
ጠርበህ ላትሞርደው…
ታሪክ እንደ መንገድ ፥ ላይታደስ ጅናው
ተሰርቶ ያለፈን ፣ አትውቀስ ከኋላው
እግርህ የዛለ ቀን ፥ ከምታርፍባት ጥድ
ከዛሬዋ ጥላ ፣ ቅጠልን አትመድምድ
እንደ ውሃ ድፋት...
በቁልቁለት ፈፋ፥ተስገምግመህ አትንጎድ
ላንዲት መናኛ ቃል…
አተን የገነቡ ፥ .....'ሺ' ገፆች አትቅደድ
ቅን አውጣ ከክፋት
ከስድብ ምርቃት
ትምርትን ግለጣት፥ከታሪክህ እልፈት
ከተልወሰወሱት፥ከቦኩት እንደ ሸጥ*
ተከትለሃቸው ፣ አትነከር ከድጥ
አጥር ተቀብለህ ፣ ሃገርህን አትስጥ
ያንተን ግዙፍ ዳቦ፥በጢቢኛ አትለውጥ
ለበይ እንዲቀለው
አንተም እንዳትቦካ፥ሙዝ ልጠህ አትሽጥ
.
«ሚኪ እንዳለ»
@MMiku
ማንፀሪያ፦ * ሸጥ ማለት ውሃ የሚወርድበት ፈረፈር ፤ ሁሌም ከጭቃነት እና ከርጥበት የማይለይ መሬት መለት ነው፡፡
@getem
@getem
@gebriel_19
--------------
ስልቻህን ጭነህ ፥ በግልገሏ ጥጃ
በዝግማኔ ጉዞ ፣ በኤሊ እርምጃ
ላትጠጋ ዝንዝር ፥ ላትሔድ እርቀህ
በመዳሰስ እምነት ፣ በቀልን ሸምቀህ
በጎሣ ስካሪ ፣ እሽክርክሪት ናውዘህ
አያትህ ባኘኩ...
ያንተ ጥርስ ይቦርቦር ፣ ለምን ትለኛለህ ?
.
በ' ጠል ከመረስረስ ፣ አንተን ከከለለህ
ከሞላው ሳር ክዳን፥አንዲት ሙጃ መዘህ
ስለ ሙሉ ጎጆ ፣ ለምን ታውራለህ?
እንኳንስ በሐገር ፥ በትልቋ መድረክ
ከቤተሰብህ ስር ፣ አንተም ነጠላ ነክ
አባትህ በበላው ፣ የማይሞላ ሆድክ
.
አይታመም ጥርስህ ፣ ባያትህ እኝካት
ጭንቅላትህ አይዙር
በከረመች ድፍድፍ ፣ አባትህ በጠጣት
በልሐ ልበልህ ፥ ናማ ! እንዋቀስ
በስልጡን እይታ በቃላት እንገስግስ
እንደ ላሜ ቦራ...
ከታች እየታለብክ ፥ አሞሌን አትላስ
በስሜት ብዕርህ ፣ ታሪክን አትውቀስ
እንደ ጠላ አሻሮ
ለቆላህ ሰው ሁሉ ፥ በገፍ አትታመስ
በላ መልስልኝ…
እነሱን ባባላች ፣ በድፍርስ አተላ
አባትህ አባቴ ፣ ባነገቧት ዱላ
እንደምን አድርጌ ፣ ካንተ ጋር ልጣላ?
.
ከእርሻው መስክ ላይ፥ከውድማው ራስ
ከወጣህ በኋላ ፥ እርፍ ይዘህ አትመለስ
እንደ ደጀን በሬ ፣ እፊት…ፊቱን እረስ
ኋሊትን ላትይዘው...
ጠርበህ ላትሞርደው…
ታሪክ እንደ መንገድ ፥ ላይታደስ ጅናው
ተሰርቶ ያለፈን ፣ አትውቀስ ከኋላው
እግርህ የዛለ ቀን ፥ ከምታርፍባት ጥድ
ከዛሬዋ ጥላ ፣ ቅጠልን አትመድምድ
እንደ ውሃ ድፋት...
በቁልቁለት ፈፋ፥ተስገምግመህ አትንጎድ
ላንዲት መናኛ ቃል…
አተን የገነቡ ፥ .....'ሺ' ገፆች አትቅደድ
ቅን አውጣ ከክፋት
ከስድብ ምርቃት
ትምርትን ግለጣት፥ከታሪክህ እልፈት
ከተልወሰወሱት፥ከቦኩት እንደ ሸጥ*
ተከትለሃቸው ፣ አትነከር ከድጥ
አጥር ተቀብለህ ፣ ሃገርህን አትስጥ
ያንተን ግዙፍ ዳቦ፥በጢቢኛ አትለውጥ
ለበይ እንዲቀለው
አንተም እንዳትቦካ፥ሙዝ ልጠህ አትሽጥ
.
«ሚኪ እንዳለ»
@MMiku
ማንፀሪያ፦ * ሸጥ ማለት ውሃ የሚወርድበት ፈረፈር ፤ ሁሌም ከጭቃነት እና ከርጥበት የማይለይ መሬት መለት ነው፡፡
@getem
@getem
@gebriel_19
❤1
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ናፍቆት
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
እንዲህ እንደዛሬ...
በመሀከላችን
ንፋስ ሳይግባብን ፣ ፍጥረት ሳይፈጠር
በኔና አንቺ መሀል...
የነበረው ክፍተት ፣ አንድ ስንዝር ነበር።
አንቺ ሰማይ ሆነሽ እኔ ደግሞ ምድር!!!
............................................
በዚህ ስንዝር መሀል....
እስትንፋስ ያላቸው ሰዎች ተፈጠሩ
እነዚህ ሰዎችም....
ቅርብ ላለች ሰማይ
የምድርን ሀጥያት ይነግሯት ጀመሩ።
"ምድር ዘማዊ ነው
ምድር ሀጣዊ ነው
ብትሸሺው ይሻላል ይህ ዓለም ጠፊ ነው"
እያሉ ሲነግሯት የሰው ወሬ ሰምታ
ሰማይ ፊኛ ሆና...
ትለጠጥ ጀመረ ከኔ ተለይትል
በሰዎች እስትንፋስ...
ወደ ላይ ተነፍታ
ወደጎንም ሰፍታ።
.......................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
................................................
እንደውም እንደውም...
በዛ ስንዝር መሀል ያኔ የተፈጠሩ
እዛሬ ላይ ሆነው..
"ሰማይ ቅርብ ነበር" እያሉ ሚያወሩ
እድሜ የሰጣቸው
ጥቂት ሰዎች አሉ
የኔና ያንቺ ፍቅር የሚመሰክሩ።
.............................................
እንደውም እንደውም....
ሌላ አይነት ማስረጃ ሌላ አይነት ምስክር
ሰማይ ቅርብ ሳለሽ ምጣድ ሆኜ ምድር
እንዲህ እንደዛሬው...
ነፋስ አቀጣጥሎት
ነፋስ የሚያጠፋው እሳት ሳይፈጠር
የሰው ልጆች ሁሉ
በፀሐይ በርሀን ምግብ ያበስሉ ነበር።
.............................................
ፀሐይ ውበትሽ ነው ጠዋት የምሞቀው
ቀን ተቃጥዬበት ሌት የምናፍቀው።
ለሊት ላይ ያመኛል ህመሜም አንቺው ነሽ
ቀኑ ጨለማ ነው...
ነግቶ እስካይሽ ድረስ ትናፍቂኛለሽ።
...........................................
መቼ ነው ሚነጋው?
ፀሐዩ ውበትሽ ምድርን የሚከድነው
መርዙ መድሀኒትሽ...
በሽታዬን ገድሎ ህመሜን ሚያድነው
ካፈቀሩት ጋራ....
እንኳን ላንድ ለሊት
ላፍታ ያህል እንኳን መለያየት ሞት ነው።
.............................................
መቼ ነው ሚነጋው ልቤን ይበርደኛል
ንጋት ላይ የሚሸሽ..
ወረተኛ ፍቅር ጤዛው በዝቶብኛል
አንቺ የሌለሽበት...
ራሴን ሳስበው ራሴን ያዞረኛል።
ለራስ ምታት ህመም..
መድሀኒት እንዲሆን
በሽታን የሚገድል መርዝ ነው ሚቀመም።
...................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ.
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
........................
እየሔዱ መጠበቅ
@getem
@getem
@gebriel_19
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
እንዲህ እንደዛሬ...
በመሀከላችን
ንፋስ ሳይግባብን ፣ ፍጥረት ሳይፈጠር
በኔና አንቺ መሀል...
የነበረው ክፍተት ፣ አንድ ስንዝር ነበር።
አንቺ ሰማይ ሆነሽ እኔ ደግሞ ምድር!!!
............................................
በዚህ ስንዝር መሀል....
እስትንፋስ ያላቸው ሰዎች ተፈጠሩ
እነዚህ ሰዎችም....
ቅርብ ላለች ሰማይ
የምድርን ሀጥያት ይነግሯት ጀመሩ።
"ምድር ዘማዊ ነው
ምድር ሀጣዊ ነው
ብትሸሺው ይሻላል ይህ ዓለም ጠፊ ነው"
እያሉ ሲነግሯት የሰው ወሬ ሰምታ
ሰማይ ፊኛ ሆና...
ትለጠጥ ጀመረ ከኔ ተለይትል
በሰዎች እስትንፋስ...
ወደ ላይ ተነፍታ
ወደጎንም ሰፍታ።
.......................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
................................................
እንደውም እንደውም...
በዛ ስንዝር መሀል ያኔ የተፈጠሩ
እዛሬ ላይ ሆነው..
"ሰማይ ቅርብ ነበር" እያሉ ሚያወሩ
እድሜ የሰጣቸው
ጥቂት ሰዎች አሉ
የኔና ያንቺ ፍቅር የሚመሰክሩ።
.............................................
እንደውም እንደውም....
ሌላ አይነት ማስረጃ ሌላ አይነት ምስክር
ሰማይ ቅርብ ሳለሽ ምጣድ ሆኜ ምድር
እንዲህ እንደዛሬው...
ነፋስ አቀጣጥሎት
ነፋስ የሚያጠፋው እሳት ሳይፈጠር
የሰው ልጆች ሁሉ
በፀሐይ በርሀን ምግብ ያበስሉ ነበር።
.............................................
ፀሐይ ውበትሽ ነው ጠዋት የምሞቀው
ቀን ተቃጥዬበት ሌት የምናፍቀው።
ለሊት ላይ ያመኛል ህመሜም አንቺው ነሽ
ቀኑ ጨለማ ነው...
ነግቶ እስካይሽ ድረስ ትናፍቂኛለሽ።
...........................................
መቼ ነው ሚነጋው?
ፀሐዩ ውበትሽ ምድርን የሚከድነው
መርዙ መድሀኒትሽ...
በሽታዬን ገድሎ ህመሜን ሚያድነው
ካፈቀሩት ጋራ....
እንኳን ላንድ ለሊት
ላፍታ ያህል እንኳን መለያየት ሞት ነው።
.............................................
መቼ ነው ሚነጋው ልቤን ይበርደኛል
ንጋት ላይ የሚሸሽ..
ወረተኛ ፍቅር ጤዛው በዝቶብኛል
አንቺ የሌለሽበት...
ራሴን ሳስበው ራሴን ያዞረኛል።
ለራስ ምታት ህመም..
መድሀኒት እንዲሆን
በሽታን የሚገድል መርዝ ነው ሚቀመም።
...................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ.
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
........................
እየሔዱ መጠበቅ
@getem
@getem
@gebriel_19
🚭ክብሪትን ለሻማ🚭
ያኔ
እሳት ምግባችን እንዳልነበር
በጭስ በአልኮል እንዳልተጨፈረ
አሁን
ያ ጊዜ ሕልም ሆኖ ከመቃብር ቀረ
አንዳንዴ ሳስበው
በጣም ይገርመኛል
ያጊዜ ያ ሰዓት የሞኝነት አለም
የጅልነት መንደር መስሎ ይሰማኛል
እስቲ ምን ይሉታል
ጭስን እየሳቡ
በሀሳብ መብሰልሰል
ደሞ ቅጠል መብላት
ሚገርም አለመብሰል
በኛ ቤት አራዳ አርደን ሞተናል
ጭስ ነው ሰላማችን
ቅጠል ነው ምግባችን
እንላለን ደሞ አለማፈራችን
የሚገርም ቂልነት
የሚገርም ሞኝነት
አፍን ዋሻ አድርጎ
እድሜን ቀነጣጥቦ
እያወቁ መሞት
አሁን
ጊዜ ተቀይሮ ያ ሁሉ አለፈና
ለመጠቀም በቃን
ክብሪትን ለሻማ😂😂😁
=====//====
💍Ati Ta Adi💍
3:55 Pm
@AtiTaAdi
@getem
@getem
@getem
ያኔ
እሳት ምግባችን እንዳልነበር
በጭስ በአልኮል እንዳልተጨፈረ
አሁን
ያ ጊዜ ሕልም ሆኖ ከመቃብር ቀረ
አንዳንዴ ሳስበው
በጣም ይገርመኛል
ያጊዜ ያ ሰዓት የሞኝነት አለም
የጅልነት መንደር መስሎ ይሰማኛል
እስቲ ምን ይሉታል
ጭስን እየሳቡ
በሀሳብ መብሰልሰል
ደሞ ቅጠል መብላት
ሚገርም አለመብሰል
በኛ ቤት አራዳ አርደን ሞተናል
ጭስ ነው ሰላማችን
ቅጠል ነው ምግባችን
እንላለን ደሞ አለማፈራችን
የሚገርም ቂልነት
የሚገርም ሞኝነት
አፍን ዋሻ አድርጎ
እድሜን ቀነጣጥቦ
እያወቁ መሞት
አሁን
ጊዜ ተቀይሮ ያ ሁሉ አለፈና
ለመጠቀም በቃን
ክብሪትን ለሻማ😂😂😁
=====//====
💍Ati Ta Adi💍
3:55 Pm
@AtiTaAdi
@getem
@getem
@getem
"ኑ ሀገር እንስፋ!"
።።።።።።።።።።።
ክፍፍል መችነበር፥
በአምላክ አሰራር ፥በቅድመ አፈጣጠር
ሰው ሰው ብቻ ነበር ፥ዘሩ ሳይቆጠር።
ሰውነት ተንዶ፥
እንዲህ እንደዛሬ ፥ ሳይኖር መበታተን
የመቆጣጠር ዛር ፥ መቃብር ሳይከተን
አንድ እናት ነበረን ፥
ቀሚሷ እንደኪዳን ፥ ሁላችን ምንለብሰው
ዛሬ ተለያይተን፥
ክብሯን እንደ እቃቃ ፥ ዳቦ ሳንቆርሰው።
ሻህላ ወረሰን፥
ውስጣችን ተበላ ፥
ፍቅር የጠመቅንበት ፥ ተሰበረ ጋኑ
ለናታችን ቀሚስ፥
ጥጥ የነደፍንበት ፥ ተጣለ ደጋኑ።
ሰው ተተነተነ፥ ሰው ተቆራረሰ
ዘር ስንቆጣጠር ፥ ሀገር ፈራረሰ።
ፍቅር እንደቁና ፥ አርጅቶ ተጣለ
ጥላቻ ድንኳኑን ፥ በላያችን ጣለ።
የናታችን ቀሚስ፥
ባለሶስ ቀለሙ ፥
በሰማይ ዳስ ሲጥል ፥ ለምድር የሚያጠላው
ትውልድ ሲናጠቅ፥
በ"የኔ ነው !" "የኔ " ፥ የጥል እሳት በላው።
ይኼው እና ዛሬ…!
ያች ሙሉ እመቤት
ያቺ ሸዋ ግርድሽ፥
በክፍፍል ክናድ ፥
ከፍቅር ሰገነት ፥ከርማ ስትገፋ
እርቃኗን ቆማለች፥
የቃልኪዳን ልብሷን ፥ ቀሚሷን ተገፋ።
ያ ብልህ አያቴ
ትውልድ በሽሚያ ፥ የቀደደው ልብሷን
ሊሰፋ ይጥራል ፥ የክብር ቀሚሷን።
ስሩ ተቀምጬ፥
በልጅ አእምሮዬ ፥ ጥያቄ ይዘንባል
በቦዘዙ ዐይኖቹ፥
ክሩ ከመርፌው ጫፍ ፥ ላይገባ ይዛባል።
(እንዲህ ጠይቃለሁ?
ምን ነካህ አባባ ፥
ይኼ ቅዳች ቀሚስ ፥ ዳግም ተጠግኖ
እንደቀድሞው አይጥል ፥ ውበቱ ጀግኖ?"
ለምን ትለፋለህ ፥? ብዬ ስጠይቀው
አያቴ እንዲህ አለኝ፥ እንባው እያነቀው።
ልጄ ሆይ አድምጪ፥
መስፋቴ ቅኔ ነው ፥ እንደወርቅ እንደሰም
አላዳውር አይል ፥ ስንጥቅ ኖሮት ቀሰም።
አስተውይ ልጄ፥
መርፌ ማለት ፍቅር ፥ ሰርስሮ ሚገባ
ክር ማለት ሰላም፥
ቀዳዳን ጠግኖ ፥ ዳግም ሚገነባ።
ይለኛል አያቴ፥
ፍቅር ባለው መርፌ፥ ነፍሱ እየተወጋች
ክር ላለው ሰላም፥ ደጀን እየተጋች
የእናቴን ቀሚስ
ሲጠግን ስላየሁ…፥
እንሆኝ አንድ ቃል…!
የናት ክበር ወድቆ፥
የለምና ለክብር ፥ የሚሰነቅ ተስፋ
ኑ እርቃን እንሸፍን፥ ኑ ሀገር እንስፋ።
።።።
በገጣሚት ዳግም ህይወት
ሰዕል በ Yohannese T Degu
@getem
@getem
@gebriel_19
።።።።።።።።።።።
ክፍፍል መችነበር፥
በአምላክ አሰራር ፥በቅድመ አፈጣጠር
ሰው ሰው ብቻ ነበር ፥ዘሩ ሳይቆጠር።
ሰውነት ተንዶ፥
እንዲህ እንደዛሬ ፥ ሳይኖር መበታተን
የመቆጣጠር ዛር ፥ መቃብር ሳይከተን
አንድ እናት ነበረን ፥
ቀሚሷ እንደኪዳን ፥ ሁላችን ምንለብሰው
ዛሬ ተለያይተን፥
ክብሯን እንደ እቃቃ ፥ ዳቦ ሳንቆርሰው።
ሻህላ ወረሰን፥
ውስጣችን ተበላ ፥
ፍቅር የጠመቅንበት ፥ ተሰበረ ጋኑ
ለናታችን ቀሚስ፥
ጥጥ የነደፍንበት ፥ ተጣለ ደጋኑ።
ሰው ተተነተነ፥ ሰው ተቆራረሰ
ዘር ስንቆጣጠር ፥ ሀገር ፈራረሰ።
ፍቅር እንደቁና ፥ አርጅቶ ተጣለ
ጥላቻ ድንኳኑን ፥ በላያችን ጣለ።
የናታችን ቀሚስ፥
ባለሶስ ቀለሙ ፥
በሰማይ ዳስ ሲጥል ፥ ለምድር የሚያጠላው
ትውልድ ሲናጠቅ፥
በ"የኔ ነው !" "የኔ " ፥ የጥል እሳት በላው።
ይኼው እና ዛሬ…!
ያች ሙሉ እመቤት
ያቺ ሸዋ ግርድሽ፥
በክፍፍል ክናድ ፥
ከፍቅር ሰገነት ፥ከርማ ስትገፋ
እርቃኗን ቆማለች፥
የቃልኪዳን ልብሷን ፥ ቀሚሷን ተገፋ።
ያ ብልህ አያቴ
ትውልድ በሽሚያ ፥ የቀደደው ልብሷን
ሊሰፋ ይጥራል ፥ የክብር ቀሚሷን።
ስሩ ተቀምጬ፥
በልጅ አእምሮዬ ፥ ጥያቄ ይዘንባል
በቦዘዙ ዐይኖቹ፥
ክሩ ከመርፌው ጫፍ ፥ ላይገባ ይዛባል።
(እንዲህ ጠይቃለሁ?
ምን ነካህ አባባ ፥
ይኼ ቅዳች ቀሚስ ፥ ዳግም ተጠግኖ
እንደቀድሞው አይጥል ፥ ውበቱ ጀግኖ?"
ለምን ትለፋለህ ፥? ብዬ ስጠይቀው
አያቴ እንዲህ አለኝ፥ እንባው እያነቀው።
ልጄ ሆይ አድምጪ፥
መስፋቴ ቅኔ ነው ፥ እንደወርቅ እንደሰም
አላዳውር አይል ፥ ስንጥቅ ኖሮት ቀሰም።
አስተውይ ልጄ፥
መርፌ ማለት ፍቅር ፥ ሰርስሮ ሚገባ
ክር ማለት ሰላም፥
ቀዳዳን ጠግኖ ፥ ዳግም ሚገነባ።
ይለኛል አያቴ፥
ፍቅር ባለው መርፌ፥ ነፍሱ እየተወጋች
ክር ላለው ሰላም፥ ደጀን እየተጋች
የእናቴን ቀሚስ
ሲጠግን ስላየሁ…፥
እንሆኝ አንድ ቃል…!
የናት ክበር ወድቆ፥
የለምና ለክብር ፥ የሚሰነቅ ተስፋ
ኑ እርቃን እንሸፍን፥ ኑ ሀገር እንስፋ።
።።።
በገጣሚት ዳግም ህይወት
ሰዕል በ Yohannese T Degu
@getem
@getem
@gebriel_19
**** ቅደሚኝ ****
።።። @Johny_Debx ።።። ✍
ሰው ቢኖርሽ ... የታል?
ከኔ ፊት እረፊ ~
ብንኖር ... ተፋቅረን!
ሁሉም ሰው አላፊ!
*
ማን ያለቅስ ... እንደ'ኔ?
ቆሜ ቅደሚ ና
ከ'ኔ ፊት ሙቺ ና !
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
@getem
@getem
@getem
።።። @Johny_Debx ።።። ✍
ሰው ቢኖርሽ ... የታል?
ከኔ ፊት እረፊ ~
ብንኖር ... ተፋቅረን!
ሁሉም ሰው አላፊ!
*
ማን ያለቅስ ... እንደ'ኔ?
ቆሜ ቅደሚ ና
ከ'ኔ ፊት ሙቺ ና !
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
@getem
@getem
@getem
👍1
Forwarded from SPACE COMPUTER
ፍቅር ፍልስፍና :ትዝብት ፖለቲካ
እዉነት እና ሀሰት :እምነት ፅናት ተስፋ
ባደሩበት ግርግም
በነሱ ምርኮኛ የተፃፈ ግጥም!!
#በጂማ ዶሎሎ international hotel
#በሀዋሳ rori internatinal hotel
ይመረቃል!
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
እዉነት እና ሀሰት :እምነት ፅናት ተስፋ
ባደሩበት ግርግም
በነሱ ምርኮኛ የተፃፈ ግጥም!!
#በጂማ ዶሎሎ international hotel
#በሀዋሳ rori internatinal hotel
ይመረቃል!
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
👍1