ግጥም መፃፍ ምንም ነው
በፈጠርኩት አንዳች አለም
ለደረሰብኝ ግን ግጥም ሚባል የለም
ይገርመኛል አንዳንድ ግዜ
ግጥም ግጠም ስትይ ላንቺ
ጠንቋይ ለሱ አያውቅም ነው
አንቺም ለኔ አትመቺ
ይገርመኛል አንዳንድ ግዜ
እኔን ፃፈኝ ስትይ በቃል
ቃል ይከዳል
ቃል ይርቃል ለሚወዱት ይታወቃል
አንዱን ሃሳብ ለመጨበጥ
ሃሳብ የትም ባክኖ ይቀራል
ለሚወዱት ለልብ ወዳጅ
ግጥም መግጠም ያስቸግራል
የመውደዴን ትርጉም
በቃላት ሳልነግራት
ታውቀዋለች ካይኔ
ግጥም ምንም ነው
ቃላት ምንም ነው
ለእንደሷና እንደኔ
አስር ብንዋደድ ብንከንፍ በፍቅር
ቃል የለኝም ላንቺ ግጥሙም ተይው ይቅር
ዝም ብዬ ልውደድ
ዝም ብዬ ላፍቅር
ገጣሚ ብባልም በሃሳብ በመስጠም
ላንቺ ሲሆን ጊዜ
ሲከብድ ግጣም መግጠም
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
በፈጠርኩት አንዳች አለም
ለደረሰብኝ ግን ግጥም ሚባል የለም
ይገርመኛል አንዳንድ ግዜ
ግጥም ግጠም ስትይ ላንቺ
ጠንቋይ ለሱ አያውቅም ነው
አንቺም ለኔ አትመቺ
ይገርመኛል አንዳንድ ግዜ
እኔን ፃፈኝ ስትይ በቃል
ቃል ይከዳል
ቃል ይርቃል ለሚወዱት ይታወቃል
አንዱን ሃሳብ ለመጨበጥ
ሃሳብ የትም ባክኖ ይቀራል
ለሚወዱት ለልብ ወዳጅ
ግጥም መግጠም ያስቸግራል
የመውደዴን ትርጉም
በቃላት ሳልነግራት
ታውቀዋለች ካይኔ
ግጥም ምንም ነው
ቃላት ምንም ነው
ለእንደሷና እንደኔ
አስር ብንዋደድ ብንከንፍ በፍቅር
ቃል የለኝም ላንቺ ግጥሙም ተይው ይቅር
ዝም ብዬ ልውደድ
ዝም ብዬ ላፍቅር
ገጣሚ ብባልም በሃሳብ በመስጠም
ላንቺ ሲሆን ጊዜ
ሲከብድ ግጣም መግጠም
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
👍41❤9🔥3🎉2
ፍቺ በቃ ህይወት እመቤቴን
አከሰልሽው አይደል ሰውነቴን
በቃ ተዪኝ ህይወት አልሰማሽም
የ'ስካሁን ገተታው አልበቃሽም?
ይመራል ኪዲዬን እዘኚልኝ
እኔም ልቅመስ እንጂ
ከውበቱ
እኔም ልኑር እንጂ
ከድሎቱ
አግቺኝ ማርሽን
ባናት ባናት
አቱኚብኝ እንጂ
የእንጀራ እናት
አይደብርሽም ግን ላንቺ እራሱ
ቀን በቀን ፈተና መነስነሱ
ተዪው ጅራፍሽን ወዲያ ጣዪው
አንጃግራንጃ ነው አርቲቡርቲ
እኔም እንደሰዎ ተመችቶኝ
እግዚአብሄር ይመስገን ልበል እስቲ
አቦ ተመቺኛ የኔ ቅመም
ስህተት ሰራህ ብለሽ አታኩርፊ
ልበ ቢስነቴን እያስታወስሽ
ጥቂት ጥፋቶቼን በሼ እለፊ
እመቤቴን ህይወት
ተረጋጊ
በአመት አንዴ እንኳን
እረፍት አርጊ
የት ሄድብሻለው
ካንቺ ጉያ
እረገጥሺኝ እኮ
እንደ አህያ
እመቤቴን ህይወት ከፋኝ በጣም
አመቤቴን ህይወት ተሳቀኩኝ
ከመኖር በስተቀር ዝቅ ብዬ
ሌላ ክፉ ነገር ምን አረኩኝ
እንዴ...
ፍቺ በቃ ወደዛ አድቢልኝ
እንዳይኮረኩመኝ እጅሽ ታኮ
ብቻዬን አንጋለሽ አትደልቂኝ
እኔም ይከፋኛል ሰው ነኝ እኮ
እንዴ..
ተስፋ እንኳን አድዪኝ ምናለበት
ለመኖር ልጓጓ ብማረርም
እንደ ተልባ አትውቀጭ ሙከራዬን
ትዝብት ነው ትርፉ ሞት አይቀርም!
ፍቺኝ በቃ ህይወት!
© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
አከሰልሽው አይደል ሰውነቴን
በቃ ተዪኝ ህይወት አልሰማሽም
የ'ስካሁን ገተታው አልበቃሽም?
ይመራል ኪዲዬን እዘኚልኝ
እኔም ልቅመስ እንጂ
ከውበቱ
እኔም ልኑር እንጂ
ከድሎቱ
አግቺኝ ማርሽን
ባናት ባናት
አቱኚብኝ እንጂ
የእንጀራ እናት
አይደብርሽም ግን ላንቺ እራሱ
ቀን በቀን ፈተና መነስነሱ
ተዪው ጅራፍሽን ወዲያ ጣዪው
አንጃግራንጃ ነው አርቲቡርቲ
እኔም እንደሰዎ ተመችቶኝ
እግዚአብሄር ይመስገን ልበል እስቲ
አቦ ተመቺኛ የኔ ቅመም
ስህተት ሰራህ ብለሽ አታኩርፊ
ልበ ቢስነቴን እያስታወስሽ
ጥቂት ጥፋቶቼን በሼ እለፊ
እመቤቴን ህይወት
ተረጋጊ
በአመት አንዴ እንኳን
እረፍት አርጊ
የት ሄድብሻለው
ካንቺ ጉያ
እረገጥሺኝ እኮ
እንደ አህያ
እመቤቴን ህይወት ከፋኝ በጣም
አመቤቴን ህይወት ተሳቀኩኝ
ከመኖር በስተቀር ዝቅ ብዬ
ሌላ ክፉ ነገር ምን አረኩኝ
እንዴ...
ፍቺ በቃ ወደዛ አድቢልኝ
እንዳይኮረኩመኝ እጅሽ ታኮ
ብቻዬን አንጋለሽ አትደልቂኝ
እኔም ይከፋኛል ሰው ነኝ እኮ
እንዴ..
ተስፋ እንኳን አድዪኝ ምናለበት
ለመኖር ልጓጓ ብማረርም
እንደ ተልባ አትውቀጭ ሙከራዬን
ትዝብት ነው ትርፉ ሞት አይቀርም!
ፍቺኝ በቃ ህይወት!
© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
❤37👍28🎉5🔥2
ሰባራ ልብ
ሰባራ ልብ የፃፈው ከንቱ ግጥም
ስሜትን ሰቅዞ ባይዝም እንኳ ባይጥም
ያፍቃሪን ሰው ህይዎት ባይለውጥም
እኔ ግን እፅፋለሁ ፊደልን አያይዤ
ከተውሽኝ ቦታ ሰባራ ልቤን ይዤ
የጨረቃ የክዋክብት ድብቅ መረብ
ሰማይ ወርዶ ከምድር ጋር ቢቀራረብ
የሌት ነፋስ
ብርድና ውርጭ ገላዬ ላይ ቢረባረብ
በዶፍ ዝናብ ምድር ቢጥለቀለቅ
እኔ እንደው ከተውሽኝ ከዛ ቦታ አለቅ
ታነሽኝ እንደው መተሽ አንሽኝ
እባክሽ ከሰው አታነሽኝ
መልኬ ቢገረጣም ባንቺ ፍቅር ደዝዤ
ብዙ መንገድን በሃሳቤ ተጉዤ
እጠብቅሽ አለሁ ሰባራ ልቤን ይዤ
By @Habtishe01
@getem
@getem
@getem
ሰባራ ልብ የፃፈው ከንቱ ግጥም
ስሜትን ሰቅዞ ባይዝም እንኳ ባይጥም
ያፍቃሪን ሰው ህይዎት ባይለውጥም
እኔ ግን እፅፋለሁ ፊደልን አያይዤ
ከተውሽኝ ቦታ ሰባራ ልቤን ይዤ
የጨረቃ የክዋክብት ድብቅ መረብ
ሰማይ ወርዶ ከምድር ጋር ቢቀራረብ
የሌት ነፋስ
ብርድና ውርጭ ገላዬ ላይ ቢረባረብ
በዶፍ ዝናብ ምድር ቢጥለቀለቅ
እኔ እንደው ከተውሽኝ ከዛ ቦታ አለቅ
ታነሽኝ እንደው መተሽ አንሽኝ
እባክሽ ከሰው አታነሽኝ
መልኬ ቢገረጣም ባንቺ ፍቅር ደዝዤ
ብዙ መንገድን በሃሳቤ ተጉዤ
እጠብቅሽ አለሁ ሰባራ ልቤን ይዤ
By @Habtishe01
@getem
@getem
@getem
❤37👍15🔥8🤩1
በቀን እንደሞትኩ...
(ሳሙኤል አለሙ)
ከአፈሩ አፈሩን ጥለነው
ከሰማዩ ሰማያቱን አልፈነው
ሄድን ሄድንና...
ከፈጣሪ የፍርድ መንበሩ ጋር ደረስን፤
ተረኛ ነበርና...
ደጃፉ ላይ ወንበር ስበን ተቀመጥን።
ተረኛ እስኪጠራ ፥ እስኪገባ ፈጣሪው ጋ
ትዝ ይለኛል ፥ ባንዲት ርዕስ ስናወጋ።
ሞትኩኝ...
የሚላስ የሚቀመስ አጥቼ
ሞትኩኝ...
"ትን" ብሎኝ ብፌ አሰናድቼ
ሞትኩኝ...
አልጋ ላይ ላመታት እንዳልነበርኩ ማቅቄ
ሞትኩኝ...
ስዝናና ውዬ ስመለስ ደክሞኝ መሪ ለቅቄ
ሞትኩኝ...
በተኛኹበት ወዳጄ ባልኩት በሰው ታንቄ
ሞትኩኝ...
ሞትኩኝ ሲሉ ፥ ኹሉ ኹሉም በየተራው
በቀኑ እንደሞተ ፥ ኹሉ ሰው ሚያወራው።
እኔ ግን...
እኔ ግን...
በቅጡ መኖሬን
በቅጡ መሞቴን ስላላወኩ
በቀኔ ሳይሆን በቀን እንደ ሞትኩ
አስታውሼ ነበር ፥ የተናገርኩ!
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@getem
@getem
(ሳሙኤል አለሙ)
ከአፈሩ አፈሩን ጥለነው
ከሰማዩ ሰማያቱን አልፈነው
ሄድን ሄድንና...
ከፈጣሪ የፍርድ መንበሩ ጋር ደረስን፤
ተረኛ ነበርና...
ደጃፉ ላይ ወንበር ስበን ተቀመጥን።
ተረኛ እስኪጠራ ፥ እስኪገባ ፈጣሪው ጋ
ትዝ ይለኛል ፥ ባንዲት ርዕስ ስናወጋ።
ሞትኩኝ...
የሚላስ የሚቀመስ አጥቼ
ሞትኩኝ...
"ትን" ብሎኝ ብፌ አሰናድቼ
ሞትኩኝ...
አልጋ ላይ ላመታት እንዳልነበርኩ ማቅቄ
ሞትኩኝ...
ስዝናና ውዬ ስመለስ ደክሞኝ መሪ ለቅቄ
ሞትኩኝ...
በተኛኹበት ወዳጄ ባልኩት በሰው ታንቄ
ሞትኩኝ...
ሞትኩኝ ሲሉ ፥ ኹሉ ኹሉም በየተራው
በቀኑ እንደሞተ ፥ ኹሉ ሰው ሚያወራው።
እኔ ግን...
እኔ ግን...
በቅጡ መኖሬን
በቅጡ መሞቴን ስላላወኩ
በቀኔ ሳይሆን በቀን እንደ ሞትኩ
አስታውሼ ነበር ፥ የተናገርኩ!
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@getem
@getem
❤32👍28😱5🔥1
በመኖር አጸድ ውስጥ
(በእውቀቱ ስዩም)
ጊዜ ከሰው መሀል- መርጦ ሲያቀማጥል
ማጣት አለ ደሞ፥
የወለዱትን ልጅ፥ ጉድፍ ላይ የሚያስጥል
በተፈሰከ ቀን፥ ጾምን የሚያስቀጥል::
እድልና ትግል በሚጫወቱበት
በደልዳላው ስፍራ
አለቃና ጭፍራ-
-ቃል ሲለዋወጡ፥ ውልና መሀላ
“አብረን እናድጋለን” ቢባል ለይስሙላ
ወንዙን ሳያጎድል ፥ሐይቁ መች ሊሞላ፤
ጸሐይ ብትወጣ
ፍጥረት በጠቅላላው ጸጋዋን ቢቀበል
የደመናም ጠበል፥
ለሁሉ ቢደርስም
አንደኛው አያድግም፥ አንዱን ሳያከስም::
@getem
@getem
@paappii
(በእውቀቱ ስዩም)
ጊዜ ከሰው መሀል- መርጦ ሲያቀማጥል
ማጣት አለ ደሞ፥
የወለዱትን ልጅ፥ ጉድፍ ላይ የሚያስጥል
በተፈሰከ ቀን፥ ጾምን የሚያስቀጥል::
እድልና ትግል በሚጫወቱበት
በደልዳላው ስፍራ
አለቃና ጭፍራ-
-ቃል ሲለዋወጡ፥ ውልና መሀላ
“አብረን እናድጋለን” ቢባል ለይስሙላ
ወንዙን ሳያጎድል ፥ሐይቁ መች ሊሞላ፤
ጸሐይ ብትወጣ
ፍጥረት በጠቅላላው ጸጋዋን ቢቀበል
የደመናም ጠበል፥
ለሁሉ ቢደርስም
አንደኛው አያድግም፥ አንዱን ሳያከስም::
@getem
@getem
@paappii
👍53❤20😢7
ሰላም ይሄ ተስፋ የተጣለበት አዲስ airdrop ነው።
https://tttttt.me/nordom_gates_bot/open?startapp=Dp2sj2
እድሎን ይሞክሩ!!
https://tttttt.me/nordom_gates_bot/open?startapp=Dp2sj2
እድሎን ይሞክሩ!!
👍2
, ዕ ድ ል
የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ከሁሉም በላይ ነው እና ያንቺ ማዕረግሽ
እስኪ ላግኝሽና ለእኔም ይድረሰኝ ወግሽ
ዕድል የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ፍጥረት በዕድሉ ሊኖር የተፃፈለትን ትቶ
ከማይሆነው ሊጋባ ከሚሆነው ተፋትቶ
ከአላህ ከእግዚሔሩ ጋር ተጋጭቶ
አንዱ ካንዱ ያለዕድል ከዕድል ተፋጭቶ
ተጎናትሮ ተሟሙቶ ላይፈጥር ዕድል
ዕልህን
ታጥቆ ይዘምታል ፅናትን በቅናት ሊገድል
ዕድል ዕድል ዕድል የት ነሽ ዕድል
አንቺን ስፈልግ እኔ እራሴን እዳልገድል
ዕድል የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ከሁሉም በላይ ነው እና ያንቺ ማዕረግሽ
እስኪ ላግኝሽና ለእኔም ይድረሰኝ ወግሽ
By @Habtishe01
@getem
@getem
@getem
የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ከሁሉም በላይ ነው እና ያንቺ ማዕረግሽ
እስኪ ላግኝሽና ለእኔም ይድረሰኝ ወግሽ
ዕድል የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ፍጥረት በዕድሉ ሊኖር የተፃፈለትን ትቶ
ከማይሆነው ሊጋባ ከሚሆነው ተፋትቶ
ከአላህ ከእግዚሔሩ ጋር ተጋጭቶ
አንዱ ካንዱ ያለዕድል ከዕድል ተፋጭቶ
ተጎናትሮ ተሟሙቶ ላይፈጥር ዕድል
ዕልህን
ታጥቆ ይዘምታል ፅናትን በቅናት ሊገድል
ዕድል ዕድል ዕድል የት ነሽ ዕድል
አንቺን ስፈልግ እኔ እራሴን እዳልገድል
ዕድል የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ከሁሉም በላይ ነው እና ያንቺ ማዕረግሽ
እስኪ ላግኝሽና ለእኔም ይድረሰኝ ወግሽ
By @Habtishe01
@getem
@getem
@getem
❤30👍24👎5😱1
ዓለም ዘጠኝ ዓለም በቃኝ
( ©እስራኤል )
በአፈኛ አንደበት ፥ ስሜን ሳላጎድፍ
ዘምቼ ሳልማርክ ፥ ወይ ጦሜ ሳልገድፍ
በነገስታት መንበር ፥ ተሹሜ ሳልነ'ግስ
ተጠርጌ ሳልወድቅ ፥ ልክ እንደ ግሳንግስ
መብቴን ለማስጠበቅ፥ ሹመኛ ሳልሞግት
ወይ ጥገት አስሬ ፥ ጠዋት ሳላልብ ግት
በአንገቴ ላይ ገመድ ፥ በደረቴ ሳንጃ
አጣማጅ አጥቼ ፥ ሆኜ ባልፍ ቀንጃ
እንደዚህ ባለ ፍርድ ፥ ለሞት ድግስ ቢያጩኝ
ዘብጥያ ጥለውኝ ፥ ጠጉሬን ካልላጩኝ
አቦ ምኑን ኖርኩኝ።
በአማላጅ ልመና ፥ ተነጥፎልኝ ኩታ
ሰርክ እጅ ካልነሱኝ ፥ ለእግዚሐር ሰላምታ
በመላ በጥበብ ፥ ለፍርድ በአደባባይ
አንዱን በተናጠል ፥ ሌላውን በጉባይ
እንደ አርያም መንግስት ፥ፍትህ እያሰፈንኩኝ
አንዴ ርትዕ ሆኜ ፥አንድየ እየበደልኩኝ
በነቃፊ ምላስ ፥እየተወደስኩኝ
በአፋቸው ሾተል ፥ካልተተረትርኩኝ
አቦ ምኑን ኖርኩኝ።
ጠፈር እንደሚያደምቅ ፥
እንደ ሶ'ብይ ሳቅ፣
በየአውራጃው ሁሉ ካልተወደስኩበት ፥
በተሰጠኝ አህላቅ፣
በዕምነት ተቀብዬ በክብር ካልመለስኩኝ
የወሰድሁትን ሃቅ፣
ዘመን በዘመን ላይ፥ ኮተቱን ቢደርብ
እንደ ንስር ሳል'ከንፍ ፥ እንደ አሳ ሳልሰ'ርብ
እንደ ጉልበተኛ ፥ደዌ ካልደቆሰኝ
ጎርሼ ለማደር ፥ ቤሳ ካላነሰኝ
አንጀቴ ካልላላ ፥ ትንንሹ ነገር
ሆዴን ካላባሰኝ፤
የሰው ፊት አይቼ ፥ ዕድሌን ካልረገምሁ
ካልተሸማቀቅሁኝ ፤
አቦ ምኑን ኖርኩኝ።
@AdamuReta
@AdamuReta
@getem
@getem
@getem
( ©እስራኤል )
በአፈኛ አንደበት ፥ ስሜን ሳላጎድፍ
ዘምቼ ሳልማርክ ፥ ወይ ጦሜ ሳልገድፍ
በነገስታት መንበር ፥ ተሹሜ ሳልነ'ግስ
ተጠርጌ ሳልወድቅ ፥ ልክ እንደ ግሳንግስ
መብቴን ለማስጠበቅ፥ ሹመኛ ሳልሞግት
ወይ ጥገት አስሬ ፥ ጠዋት ሳላልብ ግት
በአንገቴ ላይ ገመድ ፥ በደረቴ ሳንጃ
አጣማጅ አጥቼ ፥ ሆኜ ባልፍ ቀንጃ
እንደዚህ ባለ ፍርድ ፥ ለሞት ድግስ ቢያጩኝ
ዘብጥያ ጥለውኝ ፥ ጠጉሬን ካልላጩኝ
አቦ ምኑን ኖርኩኝ።
በአማላጅ ልመና ፥ ተነጥፎልኝ ኩታ
ሰርክ እጅ ካልነሱኝ ፥ ለእግዚሐር ሰላምታ
በመላ በጥበብ ፥ ለፍርድ በአደባባይ
አንዱን በተናጠል ፥ ሌላውን በጉባይ
እንደ አርያም መንግስት ፥ፍትህ እያሰፈንኩኝ
አንዴ ርትዕ ሆኜ ፥አንድየ እየበደልኩኝ
በነቃፊ ምላስ ፥እየተወደስኩኝ
በአፋቸው ሾተል ፥ካልተተረትርኩኝ
አቦ ምኑን ኖርኩኝ።
ጠፈር እንደሚያደምቅ ፥
እንደ ሶ'ብይ ሳቅ፣
በየአውራጃው ሁሉ ካልተወደስኩበት ፥
በተሰጠኝ አህላቅ፣
በዕምነት ተቀብዬ በክብር ካልመለስኩኝ
የወሰድሁትን ሃቅ፣
ዘመን በዘመን ላይ፥ ኮተቱን ቢደርብ
እንደ ንስር ሳል'ከንፍ ፥ እንደ አሳ ሳልሰ'ርብ
እንደ ጉልበተኛ ፥ደዌ ካልደቆሰኝ
ጎርሼ ለማደር ፥ ቤሳ ካላነሰኝ
አንጀቴ ካልላላ ፥ ትንንሹ ነገር
ሆዴን ካላባሰኝ፤
የሰው ፊት አይቼ ፥ ዕድሌን ካልረገምሁ
ካልተሸማቀቅሁኝ ፤
አቦ ምኑን ኖርኩኝ።
@AdamuReta
@AdamuReta
@getem
@getem
@getem
👍24❤12🔥5😢1
ባዶ እስኪሆን ድረስ
(ሚካኤል አስጨናቂ)
እንባውን ይሰፍራል ፣ ኑሮ ያሻመደው
ጥርሶቹን ይገልጣል ፣ ምቾት የታደለው።
ሰፍረን እናውቃለን ፣ እንባን በኩባያ
ሀጫ ጥርስ ዘግነናል ፣ ስጥ ሆኖ ገበያ ።
ይሄን እናውቃለን ፣ ጥንትም ነበር ድሮ
የሷ ግን ገረመን ፣ ውል ሳትን ዘንድሮ ።
ትስቅ ነበር እኮ ፣ ሆዷን በእጇ ይዛ
ከጨዋታ መኃል ፣ አንዱን ሰበዝ መ’ዛ
አንድም አልሰማንም ፣ ሀዘን እንጉርጉሮ
አንገት አልደፋንም ፣ ቀኖቿ ተቆጥሮ
እንዲህ በሳቅ ውሀ ፣ ገፅዋ ተሸርሽሮ…
እስክናጣት ድረስ ፣ ያቺን መልካም እንስት
ከቶም አላየንም ፣ ቁዝሚያ ና ምልክት
ሳቅ እንዴት ይሆናል ?
የመታመም ቅኔ
………………. ዝግ ያለ ስንብት?
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
እንባውን ይሰፍራል ፣ ኑሮ ያሻመደው
ጥርሶቹን ይገልጣል ፣ ምቾት የታደለው።
ሰፍረን እናውቃለን ፣ እንባን በኩባያ
ሀጫ ጥርስ ዘግነናል ፣ ስጥ ሆኖ ገበያ ።
ይሄን እናውቃለን ፣ ጥንትም ነበር ድሮ
የሷ ግን ገረመን ፣ ውል ሳትን ዘንድሮ ።
ትስቅ ነበር እኮ ፣ ሆዷን በእጇ ይዛ
ከጨዋታ መኃል ፣ አንዱን ሰበዝ መ’ዛ
አንድም አልሰማንም ፣ ሀዘን እንጉርጉሮ
አንገት አልደፋንም ፣ ቀኖቿ ተቆጥሮ
እንዲህ በሳቅ ውሀ ፣ ገፅዋ ተሸርሽሮ…
እስክናጣት ድረስ ፣ ያቺን መልካም እንስት
ከቶም አላየንም ፣ ቁዝሚያ ና ምልክት
ሳቅ እንዴት ይሆናል ?
የመታመም ቅኔ
………………. ዝግ ያለ ስንብት?
@getem
@getem
@getem
❤29👍21😢13
እንቅልፌን ላውስሽ
እስከ ጠዋት ተኝ
ለችግርሽ እንደው
እኔ ልብከንከን ፣
ከቀን ባላድንሽ
የሌት ህልሜ ከሆን
ባንቺ ይታለም ፣
ከንፈርሽ ስር ያለች ነጥብ
ማሪያም ስማሽ ከሆነ ግን ፣
እንዴት አየህ አትበይ
ከእግሬ ስር ተኝተሽ
በሌሊት ወጋግን፣
(ነውና ያየሁሽ )
ካይንሽ ስር ላይ ገደል አለ
ግፋኝ ልውደቅ እያነባሽ ፣
እኔ ከታች ልውደቅ ቆይ
የዱር እሾህ እንዳይወጋሽ ፣
ደረቴ ጋር ጥብቅ በይ
ይጠፍሩኝ በልጥ ዛፍ ፣
ጡቶችሽ ጋር ካሳደረኝ
ከተራራው ጎጆ አፍ ፣
ከሰው መንጋ ተገንጥለን
ከጫጩት ድምፅ ተነጥለን ፣
በባዶ እግር ጫካ አልፈን
ተራራው ጫፍ ጎጆ ሰርተን
በጫካ ዛፍ ተከልለን ፣
ከሰሜን ንፋስ ሲ ነ ፍ ስ
ደመናው ሰማይ ሲ ወ ር ስ
በምስራቅ ጎን
የድንቢጥ ድምፅ
በምዕራብ ታች
የአንበሳም...፣
በቀስታ ተቃቅፈን
በዝምታ ስንሳሳም ፣
በጣቶቼ ወገብሽን
ክንዴ ሞልቶት ዞሮ ሲደርስ ፣
ከሰማዬ ነጫጭ ውሃ
ዝናብ ሚሉት ከእኛ ሲፈስ ፣
ተቃቅፈን ከአልጋችን
ዶፉ ሲወርድ ከጎጆ ውጭ ፣
በሳቅሽ እየታጀብኩ
በብልጭታው እያየሁሽ
በነጎድጓድ ስትደነግጭ ፣
በጣቶችሽ ጣቴን
በጭንቀት ስትጨብጭ ፣
ድንግጥ ስትይ አንገቴ ስር
ትንፋሽሽ ላይ ሙቀት ሳገኝ ፣
በግርብታ ያልጠበቀ
በቀ..ስ..ታ..ከንፈርሽ እንደሳመኝ
ከሩቅ ላይም የአራዊት ድምፅ
ከክንዴ ላይ ያንቺ ነፍስ ፣
ከንፈርሽ ስር ባለው ሀይቅ
ዋኝተንበት እንፍሰስ ፣
ከዚህ ጩኸት እንደበቅ
ከጫጫታው እንሰወር
በጨለማው ፍቅር ወበቅ
እንደ ድር እንደወር
ህልም ማለት..?እስኪ እንወቅ...?
የእኛን ኑሮ ካልጠበቁት
ከገፉን ስር ከሚስሙት
አድበስብሰው ከሚቀብሩት
ተራራ ስር ካለው ጎጆ
ዘላለም ነጥለን
ዘላለም ተቃቅፈን
ዘላለም እንሙት
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት
@getem
@getem
@getem
እስከ ጠዋት ተኝ
ለችግርሽ እንደው
እኔ ልብከንከን ፣
ከቀን ባላድንሽ
የሌት ህልሜ ከሆን
ባንቺ ይታለም ፣
ከንፈርሽ ስር ያለች ነጥብ
ማሪያም ስማሽ ከሆነ ግን ፣
እንዴት አየህ አትበይ
ከእግሬ ስር ተኝተሽ
በሌሊት ወጋግን፣
(ነውና ያየሁሽ )
ካይንሽ ስር ላይ ገደል አለ
ግፋኝ ልውደቅ እያነባሽ ፣
እኔ ከታች ልውደቅ ቆይ
የዱር እሾህ እንዳይወጋሽ ፣
ደረቴ ጋር ጥብቅ በይ
ይጠፍሩኝ በልጥ ዛፍ ፣
ጡቶችሽ ጋር ካሳደረኝ
ከተራራው ጎጆ አፍ ፣
ከሰው መንጋ ተገንጥለን
ከጫጩት ድምፅ ተነጥለን ፣
በባዶ እግር ጫካ አልፈን
ተራራው ጫፍ ጎጆ ሰርተን
በጫካ ዛፍ ተከልለን ፣
ከሰሜን ንፋስ ሲ ነ ፍ ስ
ደመናው ሰማይ ሲ ወ ር ስ
በምስራቅ ጎን
የድንቢጥ ድምፅ
በምዕራብ ታች
የአንበሳም...፣
በቀስታ ተቃቅፈን
በዝምታ ስንሳሳም ፣
በጣቶቼ ወገብሽን
ክንዴ ሞልቶት ዞሮ ሲደርስ ፣
ከሰማዬ ነጫጭ ውሃ
ዝናብ ሚሉት ከእኛ ሲፈስ ፣
ተቃቅፈን ከአልጋችን
ዶፉ ሲወርድ ከጎጆ ውጭ ፣
በሳቅሽ እየታጀብኩ
በብልጭታው እያየሁሽ
በነጎድጓድ ስትደነግጭ ፣
በጣቶችሽ ጣቴን
በጭንቀት ስትጨብጭ ፣
ድንግጥ ስትይ አንገቴ ስር
ትንፋሽሽ ላይ ሙቀት ሳገኝ ፣
በግርብታ ያልጠበቀ
በቀ..ስ..ታ..ከንፈርሽ እንደሳመኝ
ከሩቅ ላይም የአራዊት ድምፅ
ከክንዴ ላይ ያንቺ ነፍስ ፣
ከንፈርሽ ስር ባለው ሀይቅ
ዋኝተንበት እንፍሰስ ፣
ከዚህ ጩኸት እንደበቅ
ከጫጫታው እንሰወር
በጨለማው ፍቅር ወበቅ
እንደ ድር እንደወር
ህልም ማለት..?እስኪ እንወቅ...?
የእኛን ኑሮ ካልጠበቁት
ከገፉን ስር ከሚስሙት
አድበስብሰው ከሚቀብሩት
ተራራ ስር ካለው ጎጆ
ዘላለም ነጥለን
ዘላለም ተቃቅፈን
ዘላለም እንሙት
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት
@getem
@getem
@getem
👍43🔥13❤11😱2🤩2👎1😢1
ስርቻ የጣለህን ሰንካላ ዕድልህን ፥
አትርገመው የትም ፣
አምነህ ብቻ ቀና ቀን ይለዋወጣል ፥
ህይወት ሳታከትም ፣
ሲገፉህ ተገፋ ወደ አምባው አናት ፥
ወደ ተራራው ጫፍ ፣
ሊያደርቁት ሲጥሩ ሲቀነጣጥቡት ፥
ይበዛል ቅርንጫፍ ፣
በዕምነት የያዝከውን ትልምህን አትጣለው ፥
አያምልጥህ ከእጅህ ፣
እንደ ክረምት ወንዝ ይሞላል ጎተራህ
ይባረካል ደጅህ።
( ©እስራኤል )
@AdamuReta
@AdamuReta
@getem
@getem
@getem
አትርገመው የትም ፣
አምነህ ብቻ ቀና ቀን ይለዋወጣል ፥
ህይወት ሳታከትም ፣
ሲገፉህ ተገፋ ወደ አምባው አናት ፥
ወደ ተራራው ጫፍ ፣
ሊያደርቁት ሲጥሩ ሲቀነጣጥቡት ፥
ይበዛል ቅርንጫፍ ፣
በዕምነት የያዝከውን ትልምህን አትጣለው ፥
አያምልጥህ ከእጅህ ፣
እንደ ክረምት ወንዝ ይሞላል ጎተራህ
ይባረካል ደጅህ።
( ©እስራኤል )
@AdamuReta
@AdamuReta
@getem
@getem
@getem
👍38❤3👎2😱1
Forwarded from Studio Anaya (Ribka Sisay)
አዲስ አበባ የምትገኙ በፅዳት የተያዘ ቆንጆ ቤት ያላቹ ለተለያዩ ማስታወቂያዎች ቤቶችን እያየን ስለሆነ የኪችን የሳሎን እና የመኝታ ቤት በደንብ የሚታዩ ጥሩ ፎቶዎችን ከእያንዳንዱ 3 ከስልካቹ ጋር @Ribki30 ላይ ላኩልን።
👍3❤1
👎36❤18🔥2😁2🤩2👍1
የተዘጋች እልፍኝ
(ሚካኤል አስጨናቂ)
አንደኛው ሲያንኳኳ
በሌት በቀን ሳያርፍ…
ላንዳንዱ ተከፍቷል የትኛውም በራፍ።
ያን ጊዜ ተንጋለልሁ ፣ አረፍ አልሁ ባልጋ
እግዜር ያላትን ቀን ፣ እሷኑ ፍለጋ ፤
ዛሬም ግን ጠብ አይልም ፣ ቢመሽም ቢነጋ።
ዕድል የቀናለት ፣
ቃታ ቢፈቱበት ፣ ቆመው ፊት ለፊቱ
ዕድል አልባ ይሞታል ፣ ሳይወጣ ከቤቱ።
አልሆነም ተኝቼም ፣
አልቀናም ነቅቼም ፣
ፍዝ ሆኜ በረታሁ ፣ ዳግም ለማንኳኳት
በሯን ማን ይክፈታት ?
ፍዝ ሆኜ በረታሁ ፣ ሰለስኩ ሆኜ ጥሩ
ተከፈተ በሩ …
ጓጓሁኝ ለመዝለቅ
ተስፋዎቼ በሩ…
አየሁት ያን እልፍኝ - አየሁት ያን ጓዳ
እንዲህ እንዲያ እያልኩኝ ፣ ብዙ ሳወላዳ
ያቺ ክፉ ሳሎን ፣ ብዙ ነፍሶች ማግዳ
ባገኛት ተከፋሁ…
መመኘቴን ጠላሁ።
ምናለ ባልጓጓሁ ?
እጄን ባላነሳሁ?
ለኔ ያላለውን ፣ እልፍኝ ለመቃኘት ፤
ለካስ ዕድል ኖሯል
ዕድለ ቢስ ሆኖ ፣ ውጪም ላይ መገኘት።
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
አንደኛው ሲያንኳኳ
በሌት በቀን ሳያርፍ…
ላንዳንዱ ተከፍቷል የትኛውም በራፍ።
ያን ጊዜ ተንጋለልሁ ፣ አረፍ አልሁ ባልጋ
እግዜር ያላትን ቀን ፣ እሷኑ ፍለጋ ፤
ዛሬም ግን ጠብ አይልም ፣ ቢመሽም ቢነጋ።
ዕድል የቀናለት ፣
ቃታ ቢፈቱበት ፣ ቆመው ፊት ለፊቱ
ዕድል አልባ ይሞታል ፣ ሳይወጣ ከቤቱ።
አልሆነም ተኝቼም ፣
አልቀናም ነቅቼም ፣
ፍዝ ሆኜ በረታሁ ፣ ዳግም ለማንኳኳት
በሯን ማን ይክፈታት ?
ፍዝ ሆኜ በረታሁ ፣ ሰለስኩ ሆኜ ጥሩ
ተከፈተ በሩ …
ጓጓሁኝ ለመዝለቅ
ተስፋዎቼ በሩ…
አየሁት ያን እልፍኝ - አየሁት ያን ጓዳ
እንዲህ እንዲያ እያልኩኝ ፣ ብዙ ሳወላዳ
ያቺ ክፉ ሳሎን ፣ ብዙ ነፍሶች ማግዳ
ባገኛት ተከፋሁ…
መመኘቴን ጠላሁ።
ምናለ ባልጓጓሁ ?
እጄን ባላነሳሁ?
ለኔ ያላለውን ፣ እልፍኝ ለመቃኘት ፤
ለካስ ዕድል ኖሯል
ዕድለ ቢስ ሆኖ ፣ ውጪም ላይ መገኘት።
@getem
@getem
@getem
👍23❤20🔥3👎2
እሆናለሁ አመስጋኝ
እንደው ቀለህ ወተህ
ቀንሶልኝ ፍቅርህ
ልቤም ረጋ ብሎ
ስምህ ከአፌ ወቶ
የማይበት ቀኑ ለኔም ሲመጣልኝ
እኔም እንደሌላው እሆናለሁ አመስጋኝ
@Eltene937
@getem
@getem
@getem
እንደው ቀለህ ወተህ
ቀንሶልኝ ፍቅርህ
ልቤም ረጋ ብሎ
ስምህ ከአፌ ወቶ
የማይበት ቀኑ ለኔም ሲመጣልኝ
እኔም እንደሌላው እሆናለሁ አመስጋኝ
@Eltene937
@getem
@getem
@getem
👍13❤8🤩3