ግጥም ብቻ 📘
67.4K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
174 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
ግጥም መፃፍ ምንም ነው
       በፈጠርኩት አንዳች አለም
ለደረሰብኝ ግን ግጥም ሚባል የለም

ይገርመኛል አንዳንድ ግዜ
     ግጥም ግጠም ስትይ ላንቺ
ጠንቋይ ለሱ አያውቅም ነው
             አንቺም ለኔ አትመቺ
ይገርመኛል አንዳንድ ግዜ
     እኔን ፃፈኝ ስትይ በቃል
ቃል ይከዳል
ቃል ይርቃል ለሚወዱት ይታወቃል
አንዱን ሃሳብ ለመጨበጥ
         ሃሳብ የትም ባክኖ ይቀራል
ለሚወዱት ለልብ ወዳጅ
     ግጥም መግጠም ያስቸግራል

የመውደዴን ትርጉም
በቃላት ሳልነግራት
    ታውቀዋለች ካይኔ
ግጥም ምንም ነው
ቃላት ምንም ነው
ለእንደሷና እንደኔ

አስር ብንዋደድ ብንከንፍ በፍቅር
ቃል የለኝም ላንቺ ግጥሙም ተይው ይቅር
ዝም ብዬ ልውደድ
ዝም ብዬ ላፍቅር

ገጣሚ ብባልም በሃሳብ በመስጠም
ላንቺ ሲሆን ጊዜ
ሲከብድ ግጣም መግጠም


ዮኒ
    ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
👍419🔥3🎉2
ፍቺ በቃ ህይወት  እመቤቴን
አከሰልሽው አይደል ሰውነቴን
በቃ ተዪኝ ህይወት አልሰማሽም
የ'ስካሁን ገተታው አልበቃሽም?

ይመራል ኪዲዬን እዘኚልኝ

እኔም ልቅመስ እንጂ
ከውበቱ
እኔም ልኑር እንጂ
ከድሎቱ
አግቺኝ ማርሽን
ባናት ባናት
አቱኚብኝ እንጂ
የእንጀራ እናት

አይደብርሽም ግን ላንቺ እራሱ
ቀን በቀን ፈተና መነስነሱ
ተዪው ጅራፍሽን ወዲያ ጣዪው
አንጃግራንጃ ነው አርቲቡርቲ
እኔም እንደሰዎ ተመችቶኝ
እግዚአብሄር ይመስገን  ልበል እስቲ

አቦ ተመቺኛ  የኔ ቅመም
ስህተት ሰራህ ብለሽ አታኩርፊ
ልበ ቢስነቴን እያስታወስሽ
ጥቂት ጥፋቶቼን በሼ እለፊ

እመቤቴን ህይወት
ተረጋጊ
በአመት አንዴ እንኳን
እረፍት አርጊ
የት ሄድብሻለው
ካንቺ ጉያ
እረገጥሺኝ እኮ
እንደ አህያ

እመቤቴን ህይወት ከፋኝ በጣም
አመቤቴን ህይወት ተሳቀኩኝ
ከመኖር በስተቀር ዝቅ ብዬ
ሌላ ክፉ ነገር ምን አረኩኝ

እንዴ...

ፍቺ በቃ ወደዛ  አድቢልኝ
እንዳይኮረኩመኝ እጅሽ ታኮ
ብቻዬን አንጋለሽ አትደልቂኝ
እኔም ይከፋኛል  ሰው ነኝ እኮ

እንዴ..

ተስፋ እንኳን አድዪኝ ምናለበት
ለመኖር ልጓጓ  ብማረርም
እንደ ተልባ አትውቀጭ ሙከራዬን
ትዝብት ነው ትርፉ ሞት አይቀርም!


ፍቺኝ በቃ ህይወት!

© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
37👍28🎉5🔥2
ሰባራ ልብ

ሰባራ ልብ የፃፈው ከንቱ ግጥም
ስሜትን ሰቅዞ ባይዝም እንኳ ባይጥም
ያፍቃሪን ሰው ህይዎት ባይለውጥም
እኔ ግን እፅፋለሁ ፊደልን አያይዤ
ከተውሽኝ ቦታ ሰባራ ልቤን ይዤ

የጨረቃ የክዋክብት ድብቅ መረብ
ሰማይ ወርዶ ከምድር ጋር ቢቀራረብ
የሌት ነፋስ
ብርድና ውርጭ ገላዬ ላይ ቢረባረብ
በዶፍ ዝናብ ምድር ቢጥለቀለቅ
እኔ እንደው ከተውሽኝ ከዛ ቦታ አለቅ
ታነሽኝ እንደው መተሽ አንሽኝ
እባክሽ ከሰው አታነሽኝ
መልኬ ቢገረጣም ባንቺ ፍቅር ደዝዤ
ብዙ መንገድን በሃሳቤ ተጉዤ
እጠብቅሽ አለሁ ሰባራ ልቤን ይዤ

By @Habtishe01

@getem
@getem
@getem
37👍15🔥8🤩1
( መጋረጃ ... )
==============

የልብሽ በር መስታወት ነው
ሠርክ የሚያሳይ ትላንትሽን
ዘውትር ከእርሱ እያፈጠጥሽ
አታበላሽ ተይ ነገሽን ....

አትስበሪው አትቆልፊው
ከመታገል ላይቀር ፍርጃ
ተከልለሽ ምታርፊበት
እንኪ የፍቅሬን መጋረጃ !!

By Kiyorna

@getem
@getem
@paappii
38👍25🔥7🤩2
በቀን እንደሞትኩ...
(ሳሙኤል አለሙ)

ከአፈሩ አፈሩን ጥለነው
ከሰማዩ ሰማያቱን አልፈነው
ሄድን ሄድንና...
ከፈጣሪ የፍርድ መንበሩ ጋር ደረስን፤
ተረኛ ነበርና...
ደጃፉ ላይ ወንበር ስበን ተቀመጥን።
ተረኛ እስኪጠራ ፥ እስኪገባ ፈጣሪው ጋ
ትዝ ይለኛል ፥ ባንዲት ርዕስ ስናወጋ።

ሞትኩኝ...
የሚላስ የሚቀመስ አጥቼ
ሞትኩኝ...
"ትን" ብሎኝ ብፌ አሰናድቼ
ሞትኩኝ...
አልጋ ላይ ላመታት እንዳልነበርኩ ማቅቄ
ሞትኩኝ...
ስዝናና ውዬ ስመለስ ደክሞኝ መሪ ለቅቄ
ሞትኩኝ...
በተኛኹበት ወዳጄ ባልኩት በሰው ታንቄ
ሞትኩኝ...
ሞትኩኝ ሲሉ ፥ ኹሉ ኹሉም በየተራው
በቀኑ እንደሞተ ፥ ኹሉ ሰው ሚያወራው።

እኔ ግን...
እኔ ግን...
በቅጡ መኖሬን
በቅጡ መሞቴን ስላላወኩ
በቀኔ ሳይሆን በቀን እንደ ሞትኩ
አስታውሼ ነበር ፥ የተናገርኩ!


ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu

@getem
@getem
32👍28😱5🔥1
በመኖር አጸድ ውስጥ
(በእውቀቱ ስዩም)

ጊዜ ከሰው መሀል- መርጦ ሲያቀማጥል
ማጣት አለ ደሞ፥
የወለዱትን ልጅ፥ ጉድፍ ላይ የሚያስጥል
በተፈሰከ ቀን፥ ጾምን የሚያስቀጥል::

እድልና ትግል በሚጫወቱበት
በደልዳላው ስፍራ
አለቃና ጭፍራ-
-ቃል ሲለዋወጡ፥ ውልና መሀላ
“አብረን እናድጋለን” ቢባል ለይስሙላ
ወንዙን ሳያጎድል ፥ሐይቁ መች ሊሞላ፤

ጸሐይ ብትወጣ
ፍጥረት በጠቅላላው ጸጋዋን ቢቀበል
የደመናም ጠበል፥
ለሁሉ ቢደርስም
አንደኛው አያድግም፥ አንዱን ሳያከስም::

@getem
@getem
@paappii
👍5320😢7
አዲስ አበባ የምትገኙ ከ 38 - 43 አመት ያላቹ ወንዶች እና ሴቶች ለተለያዩ ማስታወቂያዎች እየመለመልን ስለሆነ በደንብ የሚታዩ ጥሩ 3 ፎቶዎችን ከስልካቹ ጋር @Ribki30 ላይ ላኩልን።

ስልክ ቁጥራችሁን መላክ አትርሱ!
👍61🔥1
ሰላም ይሄ ተስፋ የተጣለበት አዲስ airdrop ነው።

https://tttttt.me/nordom_gates_bot/open?startapp=Dp2sj2

እድሎን ይሞክሩ!!
👍2
, ዕ ድ ል

የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ከሁሉም በላይ ነው እና ያንቺ ማዕረግሽ
እስኪ ላግኝሽና ለእኔም ይድረሰኝ ወግሽ
ዕድል የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ

ፍጥረት በዕድሉ ሊኖር የተፃፈለትን ትቶ
ከማይሆነው ሊጋባ ከሚሆነው ተፋትቶ
ከአላህ ከእግዚሔሩ ጋር ተጋጭቶ
አንዱ ካንዱ ያለዕድል ከዕድል ተፋጭቶ
ተጎናትሮ ተሟሙቶ ላይፈጥር ዕድል
ዕልህን
ታጥቆ ይዘምታል ፅናትን በቅናት ሊገድል
ዕድል ዕድል ዕድል የት ነሽ ዕድል
አንቺን ስፈልግ እኔ እራሴን እዳልገድል
ዕድል የት ነሽ ዕድል የትስ ብዬ ልፈልግሽ
ከሁሉም በላይ ነው እና ያንቺ ማዕረግሽ
እስኪ ላግኝሽና ለእኔም ይድረሰኝ ወግሽ

By @Habtishe01

@getem
@getem
@getem
30👍24👎5😱1
ዓለም ዘጠኝ ዓለም በቃኝ
( ©እስራኤል )


በአፈኛ አንደበት ፥ ስሜን ሳላጎድፍ
ዘምቼ ሳልማርክ ፥ ወይ ጦሜ ሳልገድፍ
በነገስታት መንበር ፥ ተሹሜ ሳልነ'ግስ
ተጠርጌ ሳልወድቅ ፥ ልክ እንደ ግሳንግስ
መብቴን ለማስጠበቅ፥ ሹመኛ ሳልሞግት
ወይ ጥገት አስሬ ፥ ጠዋት ሳላልብ ግት
በአንገቴ ላይ ገመድ ፥ በደረቴ ሳንጃ
አጣማጅ አጥቼ ፥ ሆኜ ባልፍ ቀንጃ
እንደዚህ ባለ ፍርድ ፥ ለሞት ድግስ ቢያጩኝ
ዘብጥያ ጥለውኝ ፥ ጠጉሬን ካልላጩኝ
አቦ ምኑን ኖርኩኝ።
በአማላጅ ልመና ፥ ተነጥፎልኝ ኩታ
ሰርክ እጅ ካልነሱኝ ፥ ለእግዚሐር ሰላምታ
በመላ በጥበብ ፥ ለፍርድ በአደባባይ
አንዱን በተናጠል ፥ ሌላውን በጉባይ
እንደ አርያም መንግስት ፥ፍትህ እያሰፈንኩኝ
አንዴ ርትዕ ሆኜ ፥አንድየ እየበደልኩኝ
በነቃፊ ምላስ ፥እየተወደስኩኝ
በአፋቸው ሾተል ፥ካልተተረትርኩኝ
አቦ ምኑን ኖርኩኝ።

ጠፈር እንደሚያደምቅ ፥
እንደ ሶ'ብይ ሳቅ፣
በየአውራጃው ሁሉ ካልተወደስኩበት ፥
በተሰጠኝ አህላቅ፣
በዕምነት ተቀብዬ በክብር ካልመለስኩኝ
የወሰድሁትን ሃቅ፣
ዘመን በዘመን ላይ፥ ኮተቱን ቢደርብ
እንደ ንስር ሳል'ከንፍ ፥ እንደ አሳ ሳልሰ'ርብ
እንደ ጉልበተኛ ፥ደዌ ካልደቆሰኝ
ጎርሼ ለማደር ፥ ቤሳ ካላነሰኝ
አንጀቴ ካልላላ ፥ ትንንሹ ነገር
ሆዴን ካላባሰኝ፤
የሰው ፊት አይቼ ፥ ዕድሌን ካልረገምሁ
ካልተሸማቀቅሁኝ ፤
አቦ ምኑን ኖርኩኝ።


@AdamuReta
@AdamuReta


@getem
@getem
@getem
👍2412🔥5😢1
ዘመኑ የፅልመት የሚሰማው ሁከት
ሰላማችን ድፍርስ የሰፈነው እልቂት
የተመታ ህይወት
ላይቀየር ምንም ሁልጊዜ መጨነቅ
ይሄም ህይወት ሆኖ ዝንት አለም መቧጨቅ
ህዝቤ ሆይ ተጠንቀቅ
ሁሉም ነገር ይቅር ከፈጣሪህ ታረቅ
ከንቱ አለም ትተህ ስለእርሱ ተጨነቅ !!
                                  

BY: LIONEL

@getem
@getem
@paappii
👍3912🔥3🤩3😁2
ባዶ እስኪሆን ድረስ
(ሚካኤል አስጨናቂ)

እንባውን ይሰፍራል ፣ ኑሮ ያሻመደው
ጥርሶቹን ይገልጣል ፣ ምቾት የታደለው።
ሰፍረን እናውቃለን ፣ እንባን በኩባያ
ሀጫ ጥርስ ዘግነናል ፣ ስጥ ሆኖ ገበያ ።

ይሄን እናውቃለን ፣ ጥንትም ነበር ድሮ
የሷ ግን ገረመን ፣ ውል ሳትን ዘንድሮ ።

ትስቅ ነበር እኮ ፣ ሆዷን በእጇ ይዛ
ከጨዋታ መኃል ፣ አንዱን ሰበዝ መ’ዛ
አንድም አልሰማንም ፣ ሀዘን እንጉርጉሮ
አንገት አልደፋንም ፣ ቀኖቿ ተቆጥሮ
እንዲህ በሳቅ ውሀ ፣ ገፅዋ ተሸርሽሮ…
እስክናጣት ድረስ ፣ ያቺን መልካም እንስት
ከቶም አላየንም ፣ ቁዝሚያ ና ምልክት
ሳቅ እንዴት ይሆናል ?
የመታመም ቅኔ
………………. ዝግ ያለ ስንብት?

@getem
@getem
@getem
29👍21😢13
Audio
9👍3😢1
እንቅልፌን ላውስሽ
እስከ ጠዋት ተኝ
ለችግርሽ እንደው
እኔ ልብከንከን ፣
ከቀን ባላድንሽ
የሌት ህልሜ ከሆን
ባንቺ ይታለም ፣

ከንፈርሽ ስር ያለች ነጥብ
ማሪያም ስማሽ ከሆነ ግን ፣
እንዴት አየህ አትበይ
ከእግሬ ስር ተኝተሽ
በሌሊት ወጋግን፣

(ነውና ያየሁሽ )

ካይንሽ ስር ላይ ገደል አለ
ግፋኝ ልውደቅ እያነባሽ ፣
እኔ ከታች ልውደቅ ቆይ
የዱር እሾህ እንዳይወጋሽ ፣

ደረቴ ጋር ጥብቅ በይ
ይጠፍሩኝ በልጥ ዛፍ ፣
ጡቶችሽ ጋር ካሳደረኝ
ከተራራው ጎጆ አፍ ፣

ከሰው መንጋ ተገንጥለን
ከጫጩት ድምፅ ተነጥለን ፣
በባዶ እግር ጫካ አልፈን
ተራራው ጫፍ ጎጆ ሰርተን
በጫካ ዛፍ ተከልለን ፣

ከሰሜን ንፋስ ሲ ነ ፍ ስ
ደመናው ሰማይ ሲ ወ ር ስ

በምስራቅ ጎን
የድንቢጥ ድምፅ
በምዕራብ ታች
የአንበሳም...፣
በቀስታ ተቃቅፈን
በዝምታ ስንሳሳም ፣

በጣቶቼ ወገብሽን
ክንዴ ሞልቶት ዞሮ ሲደርስ ፣
ከሰማዬ ነጫጭ ውሃ
ዝናብ ሚሉት ከእኛ ሲፈስ ፣

ተቃቅፈን ከአልጋችን
ዶፉ ሲወርድ ከጎጆ ውጭ ፣
በሳቅሽ እየታጀብኩ
በብልጭታው እያየሁሽ
በነጎድጓድ ስትደነግጭ ፣
በጣቶችሽ ጣቴን
በጭንቀት ስትጨብጭ ፣

ድንግጥ ስትይ አንገቴ ስር
ትንፋሽሽ ላይ ሙቀት ሳገኝ ፣
በግርብታ ያልጠበቀ
በቀ..ስ..ታ..ከንፈርሽ እንደሳመኝ

ከሩቅ ላይም የአራዊት ድምፅ
ከክንዴ ላይ ያንቺ ነፍስ ፣
ከንፈርሽ ስር ባለው ሀይቅ
ዋኝተንበት እንፍሰስ ፣

ከዚህ ጩኸት እንደበቅ
ከጫጫታው እንሰወር
በጨለማው ፍቅር ወበቅ
እንደ ድር እንደወር
ህልም ማለት..?እስኪ እንወቅ...?


የእኛን ኑሮ ካልጠበቁት
ከገፉን ስር ከሚስሙት
አድበስብሰው ከሚቀብሩት
ተራራ ስር ካለው ጎጆ
ዘላለም ነጥለን
ዘላለም ተቃቅፈን
ዘላለም እንሙት

@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት

@getem
@getem
@getem
👍43🔥1311😱2🤩2👎1😢1
ስርቻ የጣለህን ሰንካላ ዕድልህን ፥
አትርገመው የትም ፣
አምነህ ብቻ ቀና ቀን ይለዋወጣል ፥
ህይወት ሳታከትም ፣
ሲገፉህ ተገፋ ወደ አምባው አናት ፥
ወደ ተራራው ጫፍ ፣
ሊያደርቁት ሲጥሩ ሲቀነጣጥቡት ፥
ይበዛል ቅርንጫፍ ፣
በዕምነት የያዝከውን ትልምህን አትጣለው ፥
አያምልጥህ ከእጅህ ፣
እንደ ክረምት ወንዝ ይሞላል ጎተራህ
ይባረካል ደጅህ።


( ©እስራኤል )

@AdamuReta
@AdamuReta


@getem
@getem
@getem
👍383👎2😱1
Forwarded from Studio Anaya (Ribka Sisay)
አዲስ አበባ የምትገኙ በፅዳት የተያዘ ቆንጆ ቤት ያላቹ ለተለያዩ ማስታወቂያዎች ቤቶችን እያየን ስለሆነ የኪችን የሳሎን እና የመኝታ ቤት በደንብ የሚታዩ ጥሩ ፎቶዎችን ከእያንዳንዱ 3 ከስልካቹ ጋር @Ribki30 ላይ ላኩልን።
👍31
እ ግ ዜ ር...አትቆጣን
እ ኛ ን.....እንዳታጣን






,

@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት

@getem
@getem
@getem
👎3618🔥2😁2🤩2👍1
ስለወደድኩሽ ነው ፥ ወይስ ?

የሚውረገረገው ፥ ሽንጥሽ
እንቅስቃሴና ፥ ዳንስሽ
የአረማመድሽ ፥ አጣጣል
ከሁሉም ነገር ይበልጣል ?

ዓለሜ ከሆንሽ 'ኋላ ፥
ዓለም ሆናለች ፥ ምንም !
ቆይ ይሄ ነገር አይገርምም ?!

እንዲህ የገዘፍሽብኝ ፥ ከአዕምሮዬና ከልቤ
በእርግጥ አንቺ ሰፍተሽ ነው ፥ ወይስ እኔ ጠብቤ ?

By HAB HD

@getem
@getem
@paappii
36👍19😁12👎1🔥1😱1🤩1
የተዘጋች እልፍኝ
(ሚካኤል አስጨናቂ)

አንደኛው ሲያንኳኳ
በሌት በቀን ሳያርፍ…
ላንዳንዱ ተከፍቷል የትኛውም በራፍ።

ያን ጊዜ ተንጋለልሁ ፣ አረፍ አልሁ ባልጋ
እግዜር ያላትን ቀን ፣ እሷኑ ፍለጋ ፤
ዛሬም ግን ጠብ አይልም ፣ ቢመሽም ቢነጋ።

ዕድል የቀናለት ፣
ቃታ ቢፈቱበት ፣ ቆመው ፊት ለፊቱ
ዕድል አልባ ይሞታል ፣ ሳይወጣ ከቤቱ።

አልሆነም ተኝቼም ፣
አልቀናም ነቅቼም ፣
ፍዝ ሆኜ በረታሁ ፣ ዳግም ለማንኳኳት
በሯን ማን ይክፈታት ?
ፍዝ ሆኜ በረታሁ ፣ ሰለስኩ ሆኜ ጥሩ
ተከፈተ በሩ …
ጓጓሁኝ ለመዝለቅ
ተስፋዎቼ በሩ…
አየሁት ያን እልፍኝ - አየሁት ያን ጓዳ
እንዲህ እንዲያ እያልኩኝ ፣ ብዙ ሳወላዳ
ያቺ ክፉ ሳሎን ፣ ብዙ ነፍሶች ማግዳ
ባገኛት ተከፋሁ…
መመኘቴን ጠላሁ።

ምናለ ባልጓጓሁ ?
እጄን ባላነሳሁ?
ለኔ ያላለውን ፣ እልፍኝ ለመቃኘት ፤
ለካስ ዕድል ኖሯል
ዕድለ ቢስ ሆኖ ፣ ውጪም ላይ መገኘት።

@getem
@getem
@getem
👍2320🔥3👎2
እሆናለሁ አመስጋኝ

እንደው ቀለህ ወተህ
ቀንሶልኝ ፍቅርህ
ልቤም ረጋ ብሎ
ስምህ ከአፌ ወቶ
የማይበት ቀኑ ለኔም ሲመጣልኝ
እኔም እንደሌላው እሆናለሁ አመስጋኝ

@Eltene937
@getem
@getem
@getem
👍138🤩3