እኔ ቅብዝ ቅብዝብዚት
ችኩል ችኩልኩሊት
ወረት ወርትሪትሪት
አቋም አልባ ሽክርክሪት
ቀን ለሰላት የምፋጠን
ጎህ ሲቀዳድ የ'እግዜር መቅደሱን የማጥን።
ድንጉጥ ድንጉጥጉጢት
ፓስተር ይዞኝ መፅሀፍ ሲገልጥ
የጌታ ነኝ ብዬ ማቀልጥ።
እኔ ልጂት
ጅላ ጅሊት
ቂላ ቂሊት
ያዋቂ ቤት ተንበርካኪ
የ'አትሮንሱ ፊት ሰባኪ
ቀን የሚያምረኝ ቲሪኪሚሪኪ
ማታ ሚያምረኝ መጠጥ ዉስኪ
የማለዳዉ ቅዱስ ባሪያ
የከሰዓት የ'አላህ ባሪያ
የፓስተሩ አማካሪ
ድምብር ደምበርባሪ።
💕ትዝታ ወልዴ(@Tizita21)
@getem
@getem
ችኩል ችኩልኩሊት
ወረት ወርትሪትሪት
አቋም አልባ ሽክርክሪት
ቀን ለሰላት የምፋጠን
ጎህ ሲቀዳድ የ'እግዜር መቅደሱን የማጥን።
ድንጉጥ ድንጉጥጉጢት
ፓስተር ይዞኝ መፅሀፍ ሲገልጥ
የጌታ ነኝ ብዬ ማቀልጥ።
እኔ ልጂት
ጅላ ጅሊት
ቂላ ቂሊት
ያዋቂ ቤት ተንበርካኪ
የ'አትሮንሱ ፊት ሰባኪ
ቀን የሚያምረኝ ቲሪኪሚሪኪ
ማታ ሚያምረኝ መጠጥ ዉስኪ
የማለዳዉ ቅዱስ ባሪያ
የከሰዓት የ'አላህ ባሪያ
የፓስተሩ አማካሪ
ድምብር ደምበርባሪ።
💕ትዝታ ወልዴ(@Tizita21)
@getem
@getem
🤩38👍33❤12🔥3😢2
#የእንቢታሽ ሱሰኛ!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
አንቺን በማሰብ ውስጥ መደሰት ለምጄ
ፍቅርሽ ሱስ ሆኖብኝ ... ማንነቴን ክጄ
ባንቺ መወድስ ስም ክታብ አሰርቼ
ስምሽን አንግቼ …
እንደ አሞራ ዙሬሽ ፣ አንዣብቤ በላይ
አንቺን ሳይሽ ፣ ‘ዋይ ፣ ዋይ …’
አጃኢብ ነው መቼም!
ስትሄጅ ተራመድሁ... ስትቆሚ ቆሜ
ባንቺ ስፍር ልኬት.. .በጠርዝ ተመድሜ
ከዕድሜ ከዘመኔ ፣ ዓመታት ቆንጥሬ
ከእንቢታሽ ጋራ ፣ በእልህ ሰክሬ
ስንኞችን ጭሬ.. .
አንቺን በመጀንጀንጀን ፣ ልማድ ተጠፍሬ
በሚጣፍጥ ህመም ...
ብቻዬን በአርምሞ ፣ ስብሰለስል ኖሬ
ከሀሳቤ ማግስት ... በስንኜ ድርድር
ቃላት ድል ነስተውሽ ፣ በኃይላቸው በትር
እኔም በተራዬ ፣ መፈቀር ስጀምር
“ፍቅርህን ተቀበልሁ” ያልሽኝ ጊዜ ‘ለታ
ፍቅርሽ ጥሎኝ ጠፋ ፣ ትዝታሽ ተረታ።
(እንቢ በይኝ ዳግም
እልህን ላጣጥም ። )
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
አንቺን በማሰብ ውስጥ መደሰት ለምጄ
ፍቅርሽ ሱስ ሆኖብኝ ... ማንነቴን ክጄ
ባንቺ መወድስ ስም ክታብ አሰርቼ
ስምሽን አንግቼ …
እንደ አሞራ ዙሬሽ ፣ አንዣብቤ በላይ
አንቺን ሳይሽ ፣ ‘ዋይ ፣ ዋይ …’
አጃኢብ ነው መቼም!
ስትሄጅ ተራመድሁ... ስትቆሚ ቆሜ
ባንቺ ስፍር ልኬት.. .በጠርዝ ተመድሜ
ከዕድሜ ከዘመኔ ፣ ዓመታት ቆንጥሬ
ከእንቢታሽ ጋራ ፣ በእልህ ሰክሬ
ስንኞችን ጭሬ.. .
አንቺን በመጀንጀንጀን ፣ ልማድ ተጠፍሬ
በሚጣፍጥ ህመም ...
ብቻዬን በአርምሞ ፣ ስብሰለስል ኖሬ
ከሀሳቤ ማግስት ... በስንኜ ድርድር
ቃላት ድል ነስተውሽ ፣ በኃይላቸው በትር
እኔም በተራዬ ፣ መፈቀር ስጀምር
“ፍቅርህን ተቀበልሁ” ያልሽኝ ጊዜ ‘ለታ
ፍቅርሽ ጥሎኝ ጠፋ ፣ ትዝታሽ ተረታ።
(እንቢ በይኝ ዳግም
እልህን ላጣጥም ። )
@getem
@getem
@getem
👍42❤17😁7🔥3😱3🤩1
ወደድኩሽ ካለኝ በኃላ......
ስደዉል ስልኩን ቢዘጋም
ስቀጥረዉ ቢቀርብኝ
መልዕክቴን አይቶ ዝምቢል
በድንገት ባገኘዉ እንኳ በፍጥነት ከኔ ገሸሽ ቢል....
እኔ ልሙት ይወደኛል.......
ቢፈራኝ ነዉ እንጂ ፍቅሬ ቢያስጨንቀዉ
ምን እላት እያለ ስለሚ'ያሳስበዉ
ስልኩን የማይመልስ ትቶኝ የሚሮጠዉ
ሌላ ጊዜ እድል ቀንቶኝ
በአንዲቷ ቀን ካፌ ቀጥሮኝ
አይኖቹ ከስልኩ
አያየኝም ብዬ ያልኩ
ሌላ ሴት እያየ በድንገት ሲጠቅሳት
አይኔ ካይኑ ተገጫጨ
የያዘዉ ብርጭቆ ከእጆቹ አሟለጨ
ፈገግ አልኩ ደነገጠ
ምንን ያህል ቢወደኝ ልቡ የቀለጠ?
አወይ አጋጣሚ ብዬ ተገረምኩ
ይሄኔ ሲያየኝ ደንግጦ ነዉ አልኩ
እኔን ይንሳኝ ይወደኛል ስላችሁ
ደግሞ የዛሬዉን ጉዱን ልንገራችሁ
መጥሪያ አምጥቶ እጆቼ ላይ አስቀመጠ
ላገባ ነዉ ብሎ ልክ እንደ ልማዱ ደሞ ፈረጠጠ
ገለጥኩት.......
የልቤ ከምላት ከኔዉ ጓደኛ ጋር
የሚሆናት አጋር
ምን ያክል ቢወደኝ
እንዴት ቢሳሳልኝ
አወይ የሱ ፍቅር
የልቤ ምላትን እንደ ልቡ አድርጐ
እኔን ለማስደሰት ሚያገባት ሰርጐ
ይወደኝ አይደለ?
💕ትዝታ ወልዴ(@Tizita21)
@getem
@getem
ስደዉል ስልኩን ቢዘጋም
ስቀጥረዉ ቢቀርብኝ
መልዕክቴን አይቶ ዝምቢል
በድንገት ባገኘዉ እንኳ በፍጥነት ከኔ ገሸሽ ቢል....
እኔ ልሙት ይወደኛል.......
ቢፈራኝ ነዉ እንጂ ፍቅሬ ቢያስጨንቀዉ
ምን እላት እያለ ስለሚ'ያሳስበዉ
ስልኩን የማይመልስ ትቶኝ የሚሮጠዉ
ሌላ ጊዜ እድል ቀንቶኝ
በአንዲቷ ቀን ካፌ ቀጥሮኝ
አይኖቹ ከስልኩ
አያየኝም ብዬ ያልኩ
ሌላ ሴት እያየ በድንገት ሲጠቅሳት
አይኔ ካይኑ ተገጫጨ
የያዘዉ ብርጭቆ ከእጆቹ አሟለጨ
ፈገግ አልኩ ደነገጠ
ምንን ያህል ቢወደኝ ልቡ የቀለጠ?
አወይ አጋጣሚ ብዬ ተገረምኩ
ይሄኔ ሲያየኝ ደንግጦ ነዉ አልኩ
እኔን ይንሳኝ ይወደኛል ስላችሁ
ደግሞ የዛሬዉን ጉዱን ልንገራችሁ
መጥሪያ አምጥቶ እጆቼ ላይ አስቀመጠ
ላገባ ነዉ ብሎ ልክ እንደ ልማዱ ደሞ ፈረጠጠ
ገለጥኩት.......
የልቤ ከምላት ከኔዉ ጓደኛ ጋር
የሚሆናት አጋር
ምን ያክል ቢወደኝ
እንዴት ቢሳሳልኝ
አወይ የሱ ፍቅር
የልቤ ምላትን እንደ ልቡ አድርጐ
እኔን ለማስደሰት ሚያገባት ሰርጐ
ይወደኝ አይደለ?
💕ትዝታ ወልዴ(@Tizita21)
@getem
@getem
😁71❤32👍19😢19😱3🤩1
እንደምትወዳት ንገራት,
(በእውቀቱ ስዩም)
ሕይወት የብድር በሬ፥መቼ ሁሌ ይጠመዳል
ለጊዜው ብቻ የመጣ፥ ጊዜው ሲደርስ ይሄዳል
የተሰጠህ ጸጋ ሁሉ፥ ደሞ ካንተ ይወሰዳል::
ቀለበት፥ አምባር አይደሉም
እጅህ ላይ ሁልጊዜ የሉም
-ቀናት ሳምንታት ወራት
ዛሬውኑ ፥አሁኑኑ፥ እንደምትወዳት ንገራት::
አበቦች ሁሉ ሳይረግፉ
ምኡዝ ሽታዎች ሳይጠፉ
ያጸድ በሮች ሳይቆለፉ
በንቦች ጎዳና ላይ፥ተርቦች ሳይሰለፉ
በንፋስ ክንፍ ሳይመታ
ሕይወት የላምባ መብራት
አሁንኑ ዛሬውኑ ፥እንደምትወዳት ንገራት፤
ርቃ ሳትገሰግስ
ገና ስንቋን ስትደግስ
እንዲሁ እንዳማረባት
ቀልብህ እንደቀረባት
መቃብር በመዳፉ
እንደጠጠር ሳይቀልባት
አፈሩን ሳትዛመድ
ወደማትቀባው አመድ
ወደማትስበው አየር
ሳትቀየር
አንትም አንደበት ሳለህ፥ እሷም ጆሮ ሳያጥራት
ዛሬውኑ! አሁኑኑ! እንደምትወዳት ንገራት።
@getem
@getem
@paappii
(በእውቀቱ ስዩም)
ሕይወት የብድር በሬ፥መቼ ሁሌ ይጠመዳል
ለጊዜው ብቻ የመጣ፥ ጊዜው ሲደርስ ይሄዳል
የተሰጠህ ጸጋ ሁሉ፥ ደሞ ካንተ ይወሰዳል::
ቀለበት፥ አምባር አይደሉም
እጅህ ላይ ሁልጊዜ የሉም
-ቀናት ሳምንታት ወራት
ዛሬውኑ ፥አሁኑኑ፥ እንደምትወዳት ንገራት::
አበቦች ሁሉ ሳይረግፉ
ምኡዝ ሽታዎች ሳይጠፉ
ያጸድ በሮች ሳይቆለፉ
በንቦች ጎዳና ላይ፥ተርቦች ሳይሰለፉ
በንፋስ ክንፍ ሳይመታ
ሕይወት የላምባ መብራት
አሁንኑ ዛሬውኑ ፥እንደምትወዳት ንገራት፤
ርቃ ሳትገሰግስ
ገና ስንቋን ስትደግስ
እንዲሁ እንዳማረባት
ቀልብህ እንደቀረባት
መቃብር በመዳፉ
እንደጠጠር ሳይቀልባት
አፈሩን ሳትዛመድ
ወደማትቀባው አመድ
ወደማትስበው አየር
ሳትቀየር
አንትም አንደበት ሳለህ፥ እሷም ጆሮ ሳያጥራት
ዛሬውኑ! አሁኑኑ! እንደምትወዳት ንገራት።
@getem
@getem
@paappii
❤60👍28🔥6🤩4😱1
መናፈቅ ማለት …
ከወትሮው በድንገት
ከከተማ ግፊያ
ከሰፊው ገበያ
ከሰው ትርምስ
ከህይወት ግብስብስ
አረፍ ብለው ባልጋ
ከራስ ጋር ሲወጋ
የአስቴር እና ኤፍሬም
አባባይ ሙዚቃ ...
አንጀትንን ሲገርፍ
ትዝታን ሲያነቃ
እንዲህ ይመስለኛል !
..
መናፈቅ ማለት..
በቡሄ አመሻሽ
እርግት ባለ ሰማይ
ልጅነት ሲወያይ
ሲሸት የኩበት ጭስ
የአሪቲ ቃና መንደርን ሲዳብስ
ውብ አደይ አበባ ምድሪቷን ሲያነግስ
እንዲህ ይመስለኛል !
..
መናፈቅ ማለት ..
እኔና አንቺ አፍረን
ከዓይን ተሸሽገን
ከመስቀል ዳመራ
ሸሽተን ከጓደኞች
ፈልገን ሰዋራ ...
ተቃቅፈን እየሄድን
ውሎን ስንጋራ
ስትሰጪኝ ፖፖቲን
‘’ፖስት ካርዴስ ?’’ ብለሽ
ኪሴን ስትዳብሽኝ
እንዲህ ይመስለኛል ።
..
መናፈቅ ማለት …
ትምህርት ሊዘጋ ወቅት
ድራማ ተውነን
በሰኔ ሰላሳ ለመታየት ደምቀን
በድራማው መኃል
ፈልገን ስህተት
ከልብ የሳቅን ዕለት
ከሳቅን በኋላ
ኩሪፊያ ሲከተለን ...
ድፍን ሶስት ወራትን
ያለመገናኘት ፍርሀት ሲውጠን
ስትሰናበችኝ በጥልቁ ዝምታ
ዓይንሽን እያየሁ
ዓይኖቼን እያየሽ
የቆዘምን ለታ …..
እንዲህ ይመስለኛል ።
..
መናፈቅ ማለት …
የሽፍታ ፍርሀት
ነፍስያን ሳይንጣት
በ አራት እግር ጉዞ
የመኪናን መስኮት
በራስ ተመርኩዞ
የገጠርን መስመር
አንዱን መንገድ ይዞ
ተራራውን ማየት
እሸቱን መጎምዠት
ከገበሬ ቁና
በቆሎ መሸመት
የፀሀይዋን ግባት
አሻግሮ መቃኘት
እንዲህ ይመስለኛል።
…
መናፈቅ ማለት …
(ሚካኤል አ )
@getem
@getem
@getem
ከወትሮው በድንገት
ከከተማ ግፊያ
ከሰፊው ገበያ
ከሰው ትርምስ
ከህይወት ግብስብስ
አረፍ ብለው ባልጋ
ከራስ ጋር ሲወጋ
የአስቴር እና ኤፍሬም
አባባይ ሙዚቃ ...
አንጀትንን ሲገርፍ
ትዝታን ሲያነቃ
እንዲህ ይመስለኛል !
..
መናፈቅ ማለት..
በቡሄ አመሻሽ
እርግት ባለ ሰማይ
ልጅነት ሲወያይ
ሲሸት የኩበት ጭስ
የአሪቲ ቃና መንደርን ሲዳብስ
ውብ አደይ አበባ ምድሪቷን ሲያነግስ
እንዲህ ይመስለኛል !
..
መናፈቅ ማለት ..
እኔና አንቺ አፍረን
ከዓይን ተሸሽገን
ከመስቀል ዳመራ
ሸሽተን ከጓደኞች
ፈልገን ሰዋራ ...
ተቃቅፈን እየሄድን
ውሎን ስንጋራ
ስትሰጪኝ ፖፖቲን
‘’ፖስት ካርዴስ ?’’ ብለሽ
ኪሴን ስትዳብሽኝ
እንዲህ ይመስለኛል ።
..
መናፈቅ ማለት …
ትምህርት ሊዘጋ ወቅት
ድራማ ተውነን
በሰኔ ሰላሳ ለመታየት ደምቀን
በድራማው መኃል
ፈልገን ስህተት
ከልብ የሳቅን ዕለት
ከሳቅን በኋላ
ኩሪፊያ ሲከተለን ...
ድፍን ሶስት ወራትን
ያለመገናኘት ፍርሀት ሲውጠን
ስትሰናበችኝ በጥልቁ ዝምታ
ዓይንሽን እያየሁ
ዓይኖቼን እያየሽ
የቆዘምን ለታ …..
እንዲህ ይመስለኛል ።
..
መናፈቅ ማለት …
የሽፍታ ፍርሀት
ነፍስያን ሳይንጣት
በ አራት እግር ጉዞ
የመኪናን መስኮት
በራስ ተመርኩዞ
የገጠርን መስመር
አንዱን መንገድ ይዞ
ተራራውን ማየት
እሸቱን መጎምዠት
ከገበሬ ቁና
በቆሎ መሸመት
የፀሀይዋን ግባት
አሻግሮ መቃኘት
እንዲህ ይመስለኛል።
…
መናፈቅ ማለት …
(ሚካኤል አ )
@getem
@getem
@getem
❤48👍43🔥4🤩1
።።።።።።።።ቃል የለኝም።።።።።።።።
አልቆጭም በማፍቀሬ ፣
አልተጎዳሁ በማረሬ።
ዉስጤን ቢያመኝ ብትርቂኝም፣
አንቺን የግል ማድረግ ብያቅተኝም።
።።።። ለመሄድሽ ቃል የለኝም።።።።።
ልቤ ቆስሎ ባያገግም፣
ለፍቅርሽም ባያስደግም።
አንቺን ለማየት ብታደልም፣
በመድረክሽ ብታደምም።
።።።።።ሄድሽ ብዬ አልገግምም።።።።
የሄድሽ እለት ልቤ ቢተክዝም፣
ለሌላ ሴት እንዲህ አልፈዝም።
የምር ከፍቶኝ በነበረ ሰዐት የተፃፈ ግጥም
ቀን አርብ 03:24 ማታ
ማጀቢያ ሙዚቃ : ዳዊት ፅጌ ( ልቤ ሰዉ )
ምንጭ: እሷ ( ግራ ለገባት )
ገጣሚ: እኔ ( መሄዷን እያወቀ ላፈቀረ )
ገጣሚ : @papiel16
@getem
@getem
@getem
አልቆጭም በማፍቀሬ ፣
አልተጎዳሁ በማረሬ።
ዉስጤን ቢያመኝ ብትርቂኝም፣
አንቺን የግል ማድረግ ብያቅተኝም።
።።።። ለመሄድሽ ቃል የለኝም።።።።።
ልቤ ቆስሎ ባያገግም፣
ለፍቅርሽም ባያስደግም።
አንቺን ለማየት ብታደልም፣
በመድረክሽ ብታደምም።
።።።።።ሄድሽ ብዬ አልገግምም።።።።
የሄድሽ እለት ልቤ ቢተክዝም፣
ለሌላ ሴት እንዲህ አልፈዝም።
የምር ከፍቶኝ በነበረ ሰዐት የተፃፈ ግጥም
ቀን አርብ 03:24 ማታ
ማጀቢያ ሙዚቃ : ዳዊት ፅጌ ( ልቤ ሰዉ )
ምንጭ: እሷ ( ግራ ለገባት )
ገጣሚ: እኔ ( መሄዷን እያወቀ ላፈቀረ )
ገጣሚ : @papiel16
@getem
@getem
@getem
❤43👍32😁11😢11👎4🤩2
...ቃሌን
ውበት እረጋፊ አላቂና አብቂ
ስስትን ማልሻ አፍቃሪህ ናፍቂ
ገደብ የማላውቀው እኔ ያንተ ጠባቂ
አርጅተን እስክንሔድ በሽበት ተከበን
ቃሌን አላጥፈውም አፈቅራለው አንተን
BY
@Hanipia
@getem
@getem
@Hanipiagetem
ውበት እረጋፊ አላቂና አብቂ
ስስትን ማልሻ አፍቃሪህ ናፍቂ
ገደብ የማላውቀው እኔ ያንተ ጠባቂ
አርጅተን እስክንሔድ በሽበት ተከበን
ቃሌን አላጥፈውም አፈቅራለው አንተን
BY
@Hanipia
@getem
@getem
@Hanipiagetem
❤20👍13🎉3👎2😱2
👍26❤13😱3
ፍካሬ ዓለም
_____
(እሳት ወይ በረዶ)
የዓለምን ፍፃሜ.. ቀድመውን ያሰሉ
ትንቢት ተናጋሪ.. ብዙ ፃፎች አሉ፣
ምድር የምትጠፋው
በእሳት ነው የሚሉ።
ሌሎች በፊናቸው.. ጥልቅ የመረመሩ
የእሳቱን ፍፃሜ.. የተጠራጠሩ፣
የምድሪቱን መጥፊያ.. በውል ሲቀምሩ
በረዶ ይላሉ።
በፍካሬ ዓለም.. እጅግ ተመስጬ
ልመርጥ ብሞክር.. መፅሐፍ ገልጬ...
አንዴ በነበልባል... ደግሞ በአመዳይ፣
ምድር ስትከፈን.. ሲደረመስ ሠማይ፣
በትኩስ ቀዝቃዛው.. ዓለሙ ተንዶ...
መጥፊያችን ቸገረኝ... እሳት ወይ በረዶ?
ካየሁት ከማውቀው፣
ነገሩን ሳስበው....
ከነበልባል ስሜት.. ምኞት ካልተገራ፣
ከሚንቀለቀለው... የቁጣ ገሞራ፣
ከደምፍላት ግልቢያው
ልጓም ካላበጀ
እየገነፈለ ሀገሩን ከፈጀ... ፣
ካየሁ ከሰማሁት..
ነገሩን ሳስበው...
አላወላውልም እመሠክራለሁ፣
እሳት ኃይለኛ ነው!
በእሳት ትጠፋለች ዓለም በፍፃሜ፣
ከሚሉትም ጋራ ይሠምራል አቋሜ።
ነገር ግን ምድሪቱ
የምትጠፋበቱ፣
ሁለቴ ደጋግሞ ይሁን ከተባለ፣
ለመጥፊያ፣ ለመጥፊያ...
ሌላም መንገድ አለ፦
በቀዘቀዘ ልብ... ጥላቻ ሲነግስ...
በቀል ሲያንሠራራ.. ቂሙ ሲወራረስ...፣
ጥላቻ በርክቶ.. ማዕበል ሲያስነሳ
ሰውን ሰው ሲበላ፣ ዘመንን ሲነሳ...
ይህንም አውቃለሁ...
እመሠክራለሁ...፣
ለመቅሰፍት ለመቅሰፍት..
ለመጥፊያ ለመጥፊያ፣
በረዶም በቂ ነው
ዓለምን ለማጥፊያ
እንደ እሳት ቋያ።
— ሮበርት ፍሮስት፣ Fire and Ice (1920)፣
/ዝርው ትርጉም የራሴ/
@getem
@getem
@paappii
_____
(እሳት ወይ በረዶ)
የዓለምን ፍፃሜ.. ቀድመውን ያሰሉ
ትንቢት ተናጋሪ.. ብዙ ፃፎች አሉ፣
ምድር የምትጠፋው
በእሳት ነው የሚሉ።
ሌሎች በፊናቸው.. ጥልቅ የመረመሩ
የእሳቱን ፍፃሜ.. የተጠራጠሩ፣
የምድሪቱን መጥፊያ.. በውል ሲቀምሩ
በረዶ ይላሉ።
በፍካሬ ዓለም.. እጅግ ተመስጬ
ልመርጥ ብሞክር.. መፅሐፍ ገልጬ...
አንዴ በነበልባል... ደግሞ በአመዳይ፣
ምድር ስትከፈን.. ሲደረመስ ሠማይ፣
በትኩስ ቀዝቃዛው.. ዓለሙ ተንዶ...
መጥፊያችን ቸገረኝ... እሳት ወይ በረዶ?
ካየሁት ከማውቀው፣
ነገሩን ሳስበው....
ከነበልባል ስሜት.. ምኞት ካልተገራ፣
ከሚንቀለቀለው... የቁጣ ገሞራ፣
ከደምፍላት ግልቢያው
ልጓም ካላበጀ
እየገነፈለ ሀገሩን ከፈጀ... ፣
ካየሁ ከሰማሁት..
ነገሩን ሳስበው...
አላወላውልም እመሠክራለሁ፣
እሳት ኃይለኛ ነው!
በእሳት ትጠፋለች ዓለም በፍፃሜ፣
ከሚሉትም ጋራ ይሠምራል አቋሜ።
ነገር ግን ምድሪቱ
የምትጠፋበቱ፣
ሁለቴ ደጋግሞ ይሁን ከተባለ፣
ለመጥፊያ፣ ለመጥፊያ...
ሌላም መንገድ አለ፦
በቀዘቀዘ ልብ... ጥላቻ ሲነግስ...
በቀል ሲያንሠራራ.. ቂሙ ሲወራረስ...፣
ጥላቻ በርክቶ.. ማዕበል ሲያስነሳ
ሰውን ሰው ሲበላ፣ ዘመንን ሲነሳ...
ይህንም አውቃለሁ...
እመሠክራለሁ...፣
ለመቅሰፍት ለመቅሰፍት..
ለመጥፊያ ለመጥፊያ፣
በረዶም በቂ ነው
ዓለምን ለማጥፊያ
እንደ እሳት ቋያ።
— ሮበርት ፍሮስት፣ Fire and Ice (1920)፣
/ዝርው ትርጉም የራሴ/
@getem
@getem
@paappii
❤28👍27🔥2👎1
( አግዘኝ ...)
=============
ጌታ .....
አየህልኝ አይደል
ክንዴን ተንተርሳ ይህችን ደግ ሴት
አቅፈዋት ይቅርና ገና ስትታሰብ
የምትሞላ በሀሴት !!
እውነቷን ውበቷን ሰጥታ ለእኔነቴ
ከአንተ በታች አምናኝ ስትገባ ቤቴ
አመሌ እሾህ ሆኖ ወግቶ እንዳያደማት
ነገዬ ጨልሞ ረዝሞ እንዳይደክማት
ሰላም እንዳትራብ መውደድ እንዳይጠማት
አበርታኝ አደራ ...
ከፊት ይልቅ ዛሬ አትለይ ከጎኔ
ከሌለኸኝ በቀር ፍቅሯን ለብቻዬ
አልችለውም እኔ !!!
By @kiyorna
@getem
@getem
@paappii
=============
ጌታ .....
አየህልኝ አይደል
ክንዴን ተንተርሳ ይህችን ደግ ሴት
አቅፈዋት ይቅርና ገና ስትታሰብ
የምትሞላ በሀሴት !!
እውነቷን ውበቷን ሰጥታ ለእኔነቴ
ከአንተ በታች አምናኝ ስትገባ ቤቴ
አመሌ እሾህ ሆኖ ወግቶ እንዳያደማት
ነገዬ ጨልሞ ረዝሞ እንዳይደክማት
ሰላም እንዳትራብ መውደድ እንዳይጠማት
አበርታኝ አደራ ...
ከፊት ይልቅ ዛሬ አትለይ ከጎኔ
ከሌለኸኝ በቀር ፍቅሯን ለብቻዬ
አልችለውም እኔ !!!
By @kiyorna
@getem
@getem
@paappii
❤49👍13🤩4🔥3👎2
ከእባብ ቆዳ ትል ይውጣ
የሰው ህሊና በቁም ይፍሰስ
እየተላጠ ቆዳው በደም
የአምላክ ዙፋን በሰው ይርከስ ፣
ሌት አጋንንት ይሰማሩ
መናፍስት ነፍስን ይግዙ
ክዋክብት ይረጋግፉ
በአምላክ ፊት ይጠልዝዙ
ጥንቆላ ገደል ይግባ
ገደል ገብቶ ቤቱን ይስራ
መተት ሁሉ ይንሰራፋ
የጠንቋይ ስም ባለም ይብራ
ሰማዬ ደም ይልበስ
ትል ይትፋ ምድር ሁሉ
ዳቢሎስ ነጭ ይልበስ
በሰው እቅፍ ይታለሉ
ሳር ቅጠሉ እባብ ይሁን
ወንዙ ሙሉ ጫካ መንፈስ
ንፁሃን ይደራመስ
እባብ ባለም ነጥቆ ይንገስ
ያለንበት ባለም ሁሉ፥
እኛ ሁሉ የምንሆነው
እባብ ልንገል ምናሴረው
ለእባብ ነበር የምንወልደው ፣
እንዲህ ነበር ያገሬ ሰው ፣
ከሰይጣን ጋር ሚዋሰበው
እንዲህ ነው ያገሬ ሰው...
ራሱን ነው ያረከሰው...
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት
@getem
@getem
@paappii
የሰው ህሊና በቁም ይፍሰስ
እየተላጠ ቆዳው በደም
የአምላክ ዙፋን በሰው ይርከስ ፣
ሌት አጋንንት ይሰማሩ
መናፍስት ነፍስን ይግዙ
ክዋክብት ይረጋግፉ
በአምላክ ፊት ይጠልዝዙ
ጥንቆላ ገደል ይግባ
ገደል ገብቶ ቤቱን ይስራ
መተት ሁሉ ይንሰራፋ
የጠንቋይ ስም ባለም ይብራ
ሰማዬ ደም ይልበስ
ትል ይትፋ ምድር ሁሉ
ዳቢሎስ ነጭ ይልበስ
በሰው እቅፍ ይታለሉ
ሳር ቅጠሉ እባብ ይሁን
ወንዙ ሙሉ ጫካ መንፈስ
ንፁሃን ይደራመስ
እባብ ባለም ነጥቆ ይንገስ
ያለንበት ባለም ሁሉ፥
እኛ ሁሉ የምንሆነው
እባብ ልንገል ምናሴረው
ለእባብ ነበር የምንወልደው ፣
እንዲህ ነበር ያገሬ ሰው ፣
ከሰይጣን ጋር ሚዋሰበው
እንዲህ ነው ያገሬ ሰው...
ራሱን ነው ያረከሰው...
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት
@getem
@getem
@paappii
👍24😢19👎11❤4😱4🔥3