#የጻድቃንን_ሞት_እኔ_ልሙት_ፍጻሜዬም_እንደ_እርሱ_ፍጻሜ_ትሁን
ዘኁ 23:10
እንኳን አደረሳችሁ!!
ጠቢቡ ሰለሞን "ከመወለድ ቀን የሞት ቀን ይሻላል " መክ 7፡2
ብሎ እንደተናገረ ቅዱሳን ከተወለዱበት ቀን በክብር በሥጋ
የሞቱበት ቀን ዕለተ እረፍታቸው የከበረ ነው፡፡ቅዱስ ዳዊትም
«የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው» መዝ
115:15 ብሎ እንደተናገረም በእርሱ ዘንድ የከበረው ሞታቸው
እርሱን በሚያመልኩ ክርስቲያኖች ዘንድ ምንኛ ሊከበር እንደሚገባ
ለመረዳት አያዳግትም። እኛ ምንም ያህል ዕለተ እረፍታቸውን
ብናከብር እግዚአብሔር ባከበረበት መጠን ልናከብረው
አንችልም።እግዚአብሔር ያከበረው የጻድቁን የዕረፍት ቀን ማክበር
ደግሞ እግዚአብሔርን ማክበር ቀኑንም ማሰብ እግዚአብሔርን
ማሰብ ነው።በዓለም መልካም ያደረጉ ለሀገር ለወገን የሚበጅ
ሥራ የፈፀሙ ሰዎች በየዓመቱ ያረፉበት ቀን እየታሰበ ታሪካቸው
ይነገራል መልካም ሥራቸው ይታሰባል። በዓለም ያለን ሰዎች
መልካም ያደረጉትን እንዲህ ካሰብን እግዚአብሔር ሕጉን ትእዛዙን
የፈጸሙትን መንገዱን የተከተሉትን ደስ ያሰኙትን ወዳጆቹ
እንዳይከበሩ የማይፈቅድ ውለታንም የሚዘነጋ አምላክ አይደለም
ማቴ 7፡1 ::
የቅዱሳን ሞተ ሥጋ
፩. ቅዱሳን በሥጋ የሚሞቱበትን ቀንና ሁኔታ ያውቃሉ ።
ቅዱስ ጴጥሮስ በምን አይነት አሟሟት እንደሚሞት በጌታችን
ተነግሮታል።ዮሐ 21፡18-19 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም
ከኢየሩሳሌም ወደ ሮም ለሐዋርያዊ አገልግሎት ሲሄድ ምዕመናኑ
ዳግም እንደማያዩት ነግሯቸዋል። የሐዋ 20፡38 በወንጌል
ለወለደው ልጁ ለጢሞቴዎስም " በመሥዋዕት እንደሚደረግ የእኔ
ሕይወት ይሠዋልና ..." 2ጢሞ 4፡6-9 በማለት የተናገረው ቃል
ይህንን ያስረዳናል።
፪. በሚሞቱበት ቀን እግዚአብሔር ይገለጥላቸዋል።
ሊቀ ዲያቆናት ቀዳሜ ሰማእት ቅዱስ እስጢፋኖስ አይሁድ
በድንጋይ እየወገሩት ሞት አፋፍ ላይ ባደረሱት ጊዜ "እነሆ ሰማያት
ተከፍተው የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስ ክርስቶስንም በአብ ቀኝ
ሆኖ አየዋለሁ" እንዳለ የሐዋ 7፡59
፫. የምህረትና የይቅርታ ቃል ኪዳንን ይቀበላሉ መዝ 88፡2
ስለተቀበሉት የምሕረት ቃል ኪዳንም እግዚአብሔር ቁጣውን
በምሕረት በትእግሥት ይለውጣል:: ዘጸ 32:32 ኢሳ 37 :35
ማቴ 24 :22
፬.ከዚህ ዓለም ጋር ያላቸው ግኑኝነት አይቋረጥም ።
እነዚያ በግፍ በዓላውያን የተገደሉ ሰማዕታት በዚህ ዓለም ባሉ
ግፈኞች ላይ ለምነውባቸዋል ራእይ 6፡9 አቤልም በግፍ ተገድሎ
እስከዛሬ ድረስ እነሆ ይጮሃል ዕብ 11፡4 ፥ ሔኖክ 6፡26
አብርሃምም በሥጋ ካለፈ ከሺህ አመታት በኋላ የተነሱ የአልአዛርን
ደግነት የነዌን ክፉነት ያውቅ እንደነበር ተነግሮናል። ሉቃ 16፡
19-26 በፈርኦን ዘመን ያለፈች ራሔልም ጌታችን በተወለደ ጊዜ
በሔሮድስ ሰይፍ ስለተፈጁ ሕጻናት አልቅሳለች ማቴ 2፡17
፭. የድላቸው ቀን ነው
ክርስቲያኖች ሰይጣንን የሥጋ ፈቃዳቸውን ክፉ የሆነ የዓለም
ምኞትን ክፉ ህሊናትን አሸንፈው የድል አክሊል እንደሚቀዳጁ
የሚታወቅበት ቀን በሥጋ የሚሞቱበት ቀን ነው::ጌታችን በወዳጁ
በዮሐንስ ራእይ መጽሐፍ " እስከ ሞት ድረስ የታመንክ ሁን
የህይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ" ራእይ 2:9 ብሎ መናገሩም
ለዚህ ነው :: በሌላም ስፍራ " እስከመጨረሻ የሚጸና እርሱ
ይድናል" ተብሏል ማቴ 24:13 ::ኦርቶዶክሳውያንም የቅዱሳኑን
ዕለተ ሞት የምናከብረው ጠቢቡ ሰሎሞን "ጻድቃን ከሥጋ ድል
ባደረጉ ጊዜ ብዙ ክብር አለ " ምሳ 28:12 ብሏልና
ፈጣሪያቸውም አክብሯቸዋልና እኛም እርሱን ተከትለን ክብራቸውን
ለመግለጽ ነው:: "ክብር ለሚገባው ክብር ስጡ " ሮሜ 13:7
እንዲል መጽሐፍ ::
ከሥጋ ሞት በኋላ
፩. ቅዱሳን በዚህ ዓለም ሳሉ የሚያውቁት ዕውቀት የተከፈለ
ከሥጋ ሞታቸው በኋላ የሚያውቁት ዕውቀት ደግሞ እጅግ የረቀቀና
የመጠቀ ይሆናል 1ቆሮ 13፡12
፪. ከሥጋ ሞታቸው ቀን በኋላ አይራቡም አይጠሙም ፀሐይም
ትኩሳትም ሁሉ ከቶ አይወርድባቸውም እረኛቸው ፈጣሪያቸው
ክርስቶስም እንባዎቻቸውን ከዓይናቸው ያብሳል ራእይ 7፡16 ::
ጌታችንም ስለዚህ ነገር ሲያስተምር "ጻድቃን በአባታቸው
መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ" ማቴ 13፡43 ብሏል ።
፫. በስማቸው አብያተ ክርስቲያናት ይታነጻሉ ኢሳ 56:4
፬. ከሥጋ ሞታቸው በኋላም በሕያው ክርስቶስ ሕያዋን ሆነው
ከእርሱ ጋር ይኖራሉ ማቴ 22 :29-33 ዮሐ 8:51 እንግዲህ ምን
እንላለን ? ከኢትዮጵያዊው ጻድቅ ከአቡነ ተክለሃይማኖት የዕረፍት
በዓል ረድኤት በረከት ያሳትፈን አሜን!!
በመምህር ቢትወደድ ወርቁ
ነሐሴ 23\2010 ዓ ም
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
ዘኁ 23:10
እንኳን አደረሳችሁ!!
ጠቢቡ ሰለሞን "ከመወለድ ቀን የሞት ቀን ይሻላል " መክ 7፡2
ብሎ እንደተናገረ ቅዱሳን ከተወለዱበት ቀን በክብር በሥጋ
የሞቱበት ቀን ዕለተ እረፍታቸው የከበረ ነው፡፡ቅዱስ ዳዊትም
«የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው» መዝ
115:15 ብሎ እንደተናገረም በእርሱ ዘንድ የከበረው ሞታቸው
እርሱን በሚያመልኩ ክርስቲያኖች ዘንድ ምንኛ ሊከበር እንደሚገባ
ለመረዳት አያዳግትም። እኛ ምንም ያህል ዕለተ እረፍታቸውን
ብናከብር እግዚአብሔር ባከበረበት መጠን ልናከብረው
አንችልም።እግዚአብሔር ያከበረው የጻድቁን የዕረፍት ቀን ማክበር
ደግሞ እግዚአብሔርን ማክበር ቀኑንም ማሰብ እግዚአብሔርን
ማሰብ ነው።በዓለም መልካም ያደረጉ ለሀገር ለወገን የሚበጅ
ሥራ የፈፀሙ ሰዎች በየዓመቱ ያረፉበት ቀን እየታሰበ ታሪካቸው
ይነገራል መልካም ሥራቸው ይታሰባል። በዓለም ያለን ሰዎች
መልካም ያደረጉትን እንዲህ ካሰብን እግዚአብሔር ሕጉን ትእዛዙን
የፈጸሙትን መንገዱን የተከተሉትን ደስ ያሰኙትን ወዳጆቹ
እንዳይከበሩ የማይፈቅድ ውለታንም የሚዘነጋ አምላክ አይደለም
ማቴ 7፡1 ::
የቅዱሳን ሞተ ሥጋ
፩. ቅዱሳን በሥጋ የሚሞቱበትን ቀንና ሁኔታ ያውቃሉ ።
ቅዱስ ጴጥሮስ በምን አይነት አሟሟት እንደሚሞት በጌታችን
ተነግሮታል።ዮሐ 21፡18-19 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም
ከኢየሩሳሌም ወደ ሮም ለሐዋርያዊ አገልግሎት ሲሄድ ምዕመናኑ
ዳግም እንደማያዩት ነግሯቸዋል። የሐዋ 20፡38 በወንጌል
ለወለደው ልጁ ለጢሞቴዎስም " በመሥዋዕት እንደሚደረግ የእኔ
ሕይወት ይሠዋልና ..." 2ጢሞ 4፡6-9 በማለት የተናገረው ቃል
ይህንን ያስረዳናል።
፪. በሚሞቱበት ቀን እግዚአብሔር ይገለጥላቸዋል።
ሊቀ ዲያቆናት ቀዳሜ ሰማእት ቅዱስ እስጢፋኖስ አይሁድ
በድንጋይ እየወገሩት ሞት አፋፍ ላይ ባደረሱት ጊዜ "እነሆ ሰማያት
ተከፍተው የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስ ክርስቶስንም በአብ ቀኝ
ሆኖ አየዋለሁ" እንዳለ የሐዋ 7፡59
፫. የምህረትና የይቅርታ ቃል ኪዳንን ይቀበላሉ መዝ 88፡2
ስለተቀበሉት የምሕረት ቃል ኪዳንም እግዚአብሔር ቁጣውን
በምሕረት በትእግሥት ይለውጣል:: ዘጸ 32:32 ኢሳ 37 :35
ማቴ 24 :22
፬.ከዚህ ዓለም ጋር ያላቸው ግኑኝነት አይቋረጥም ።
እነዚያ በግፍ በዓላውያን የተገደሉ ሰማዕታት በዚህ ዓለም ባሉ
ግፈኞች ላይ ለምነውባቸዋል ራእይ 6፡9 አቤልም በግፍ ተገድሎ
እስከዛሬ ድረስ እነሆ ይጮሃል ዕብ 11፡4 ፥ ሔኖክ 6፡26
አብርሃምም በሥጋ ካለፈ ከሺህ አመታት በኋላ የተነሱ የአልአዛርን
ደግነት የነዌን ክፉነት ያውቅ እንደነበር ተነግሮናል። ሉቃ 16፡
19-26 በፈርኦን ዘመን ያለፈች ራሔልም ጌታችን በተወለደ ጊዜ
በሔሮድስ ሰይፍ ስለተፈጁ ሕጻናት አልቅሳለች ማቴ 2፡17
፭. የድላቸው ቀን ነው
ክርስቲያኖች ሰይጣንን የሥጋ ፈቃዳቸውን ክፉ የሆነ የዓለም
ምኞትን ክፉ ህሊናትን አሸንፈው የድል አክሊል እንደሚቀዳጁ
የሚታወቅበት ቀን በሥጋ የሚሞቱበት ቀን ነው::ጌታችን በወዳጁ
በዮሐንስ ራእይ መጽሐፍ " እስከ ሞት ድረስ የታመንክ ሁን
የህይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ" ራእይ 2:9 ብሎ መናገሩም
ለዚህ ነው :: በሌላም ስፍራ " እስከመጨረሻ የሚጸና እርሱ
ይድናል" ተብሏል ማቴ 24:13 ::ኦርቶዶክሳውያንም የቅዱሳኑን
ዕለተ ሞት የምናከብረው ጠቢቡ ሰሎሞን "ጻድቃን ከሥጋ ድል
ባደረጉ ጊዜ ብዙ ክብር አለ " ምሳ 28:12 ብሏልና
ፈጣሪያቸውም አክብሯቸዋልና እኛም እርሱን ተከትለን ክብራቸውን
ለመግለጽ ነው:: "ክብር ለሚገባው ክብር ስጡ " ሮሜ 13:7
እንዲል መጽሐፍ ::
ከሥጋ ሞት በኋላ
፩. ቅዱሳን በዚህ ዓለም ሳሉ የሚያውቁት ዕውቀት የተከፈለ
ከሥጋ ሞታቸው በኋላ የሚያውቁት ዕውቀት ደግሞ እጅግ የረቀቀና
የመጠቀ ይሆናል 1ቆሮ 13፡12
፪. ከሥጋ ሞታቸው ቀን በኋላ አይራቡም አይጠሙም ፀሐይም
ትኩሳትም ሁሉ ከቶ አይወርድባቸውም እረኛቸው ፈጣሪያቸው
ክርስቶስም እንባዎቻቸውን ከዓይናቸው ያብሳል ራእይ 7፡16 ::
ጌታችንም ስለዚህ ነገር ሲያስተምር "ጻድቃን በአባታቸው
መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ" ማቴ 13፡43 ብሏል ።
፫. በስማቸው አብያተ ክርስቲያናት ይታነጻሉ ኢሳ 56:4
፬. ከሥጋ ሞታቸው በኋላም በሕያው ክርስቶስ ሕያዋን ሆነው
ከእርሱ ጋር ይኖራሉ ማቴ 22 :29-33 ዮሐ 8:51 እንግዲህ ምን
እንላለን ? ከኢትዮጵያዊው ጻድቅ ከአቡነ ተክለሃይማኖት የዕረፍት
በዓል ረድኤት በረከት ያሳትፈን አሜን!!
በመምህር ቢትወደድ ወርቁ
ነሐሴ 23\2010 ዓ ም
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
“#እግዚአብሔር በጻድቁ እንደ ተገለጠ እወቁ።”
መዝ 4፥3
ብዙዎች እግዚአብሔር በጻድቃን እንደሚገለጥ ባለማወቅ የቅዱሳኑ ነገር የእግዚአብሔርን ነገር በልጦ የሸፈነው ይመስላቸዋል :: ግን ነገሩ እንዲህ አይደለም ውኃን ከጥሩ (ከጠራው) ነገርን ከሥሩ እንዲሉ የጻድቅን ትርጉም በመጀመሪያ በአጭሩ እንመልከት::
ጻድቅ የሚለው ግሥ እውነተኛ የሚል ትርጉም ያለው ሲሆን ለብዙ ቁጥር ስንጠቀመው ጻድቃን ብለን ማናበብ እንችላለን እውነተኞች ማለታችን ነው!::
በእውነቱ "ጻድቅ" የሚለውን መቀጽል በመጀመሪያ በተገባ የሚገባው ለልዑል እግዚአብሔር ብቻ ነው :: እግዚአብሔር አምላክ እቀደስ አይል ቅዱስ እጸድቅም አይል ነገር ጻድቅ ነው ጽድቁም እንደ ቅዱሳን የጸጋ (የስጦታ) እንደ ሰይጣንም የሐሰት ሳይሆን ማንም ያልሰጠው ማንም የማይቀማው በባህሪው ጻድቅ እውነተኛ ቅዱስም አምላክ ነው ::“እንደ እግዚአብሔር ቅዱስ የለምና፥ እንደ #አምላካችንም_ጻድቅ የለምና፤ ከአንተ በቀር ቅዱስ የለም።” እንዲል መጽሐፍ 1ኛ ሳሙ 2፥2
ጻድቅ ወይም እውነተኛ ለመሆን በእውነት ማመን ፣ ስለ እውነት መናገር፣ ስለ እውነት ማስተማር፣ ስለ እውነት መኖር ይጠይቃል :: ታዲያ ይህ እውነት ማነው ካልን እግዚአብሔር ነው:: “እኔ መንገድና #እውነት ሕይወትም ነኝ፤ ” ዮሐ14፥6
ከእነዚህ እውነተኞቹ ጻድቃን መካከል የጽላሎሹ ኮከብ የእግዚ አርያ ዐይን ማረፊያ የፀጋ ዘአብ አብራክ የምመናን እረኛ የወንጌል አርበኛ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ግምባር ቀደም ናቸው:: ድካምን በማብዛት እንደ ነቢያት ወንጌልን በማስተማር እንደ ሐዋርያት በመገረፍ እንደ ሰማዕታት መሰለ ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪቆጠር በጻም በድካም ሌት ተቀን ተጉ 22ዓመት በሁለት እግራቸው ከቆሙ በኃላ ከመቆም ብዛት አንዲቱ የእግራቸው አገዳ ተሰብራ ወደቀች በዚህም ለአፍታ ሳይዘናጉ ለ7ዓመታት በአንድ እግራቸው ቆመው በትዕግሥት 29 ዓመት በጸሎት ተጋደሉ :: መጻሕፍ “እነሆ፥ በትዕግሥት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን” ያዕ5፥11 ብሏልና " #ብፁህ " አልናቸው :: የሥራዬን ጽናት የሃይማኖቴን ደግነት ግለጥ እያሉ በሕይወት ዘመናቸው በሙሉ ክርስቶስን ሲሰብኩ ቆይተዋል እንዲያውም በከተታ አውራጃ በዚህ በታመኑለት በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሲያስተምሩ ሀገሪው ሰምቶ ለዛፍ መስገድን ሊያስቆሙን ነው ከፈጣሪያችን ሊያጣሉን ነው ብለው እንደ አንበሳ ሊውጧቸው ተነሱ አባታችን ግን በልበ ሰፊነት በነገር አሳላፊነት እያለዛዘበ አስተማሯቸው ወደ ቀናች ሃይማኖትም መለሷቸው:: ይህ እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ምን ያክል ድንቅ እንደሆነ የሚያመላክት ነው እንጂ የቅዱሳኑ ሕይወት የእግዚአብሔር ነገር ነገረ እግዚአብሔርን የሸፈነ አይደለም ጻድቃን ቅዱሳን “እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፥” የሚሉ ናቸውና 1ኛ ቆሮ1፥23
እንደ ልቤ የተባለውም ቅዱስ ዳዊትም “እግዚአብሔር #በቅዱሳኑ_ላይ_ድንቅ ነው፤ የእስራኤል አምላክ እርሱ ኃይልን ብርታትንም ለሕዝቡ ይሰጣል፤ እግዚአብሔርም ይመስገን።”መዝ 67(68)፥35 ሲል የጻድቃን ሕይወት ሙሉ በሙሉ እግዚአብሔር የተገለጠበት ድንቅም የሚያደርግበት ለሕዝብም ኃይልን የሚያድልበት መሆኑን መስክሮልናል በዚህም ነገር እግዚአብሔር ይመሰገንበታል :: “መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።” ብሎ ያዘዛቸውም በእነርሱ መልካም ሕይወት የሰማይ አባታቸው እግዚአብሔር ስለሚገለጥበት ነው። ማቴ 5፥16
አንዳንድ አካላት ግን ይህን ባለ መገንዘብ ቤተክርስቲያን ከክርስቶስ ይልቅ ቅዱስ ጳውሎስን ከነገረ እግዚአብሔር ይልቅም ነገረ ቅዱሳንን አስበልጣ ትሰብካለች ይላሉ:: ነገሩ ከፈረሱ ጋሪውን እንደማስቀደም ያለ ነገር ነውና የትም አያደርስም :: ይህ ዓይነቱ አካሄድ የዋልዮሽ አካሄድ በመሆኑ መጨረሻው ገደል ነው:: የዚህ ትምህርት ምንጭም ክርስቶስ ብቻ በቂዬ ነው የምትለው የመናፍቁ ዓለም ጨዋታ ነች :: ለክርስቶስ የተቆረቆሩ በማስመሰል ምርጦቹ ቅዱሳኑን ለማራቅ አያስፈልጉም ለማለት የሚደረግ ዳርዳርታ ነች :: ቅዱሳን ማሰብ በስማቸው ዝክር ማዘከር ስማቸውን መጥራት ገድላቸውን መስማት ማሰማት የተገባ ደገኛ ሥርዓት ነው ሙሽራው ክርስቶስ ብቻ ሳይሆን ሚዜዎቹ ቅዱሳንንም መቀበል ይገባል::
እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል። ማቴ 10፥40-41 መቀበል ከነ ሚዜዎቹ ነው ማነው? እስቲ ከውጪ የመጣ ወዳጁን አንተ ና ወደ ቤቴ ግባ የያዝከው የሻንጣ ገንዘብ ግን ከቤቴ አይገባም ብሎ ወዳጁን ስለ ገንዘቡ አልቀበልም የሚለው? ቅዱሳን የክርስቶስ ገንዘቡ ናቸው :: ያለ እነርሱ ልንቀበለው አንችልም::
“የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን #ዋኖቻችሁን_አስቡ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው።”ዕብ 13፥7 እንግዚህ እግዚአብሔር ያከበረውን ማን ያቀለዋል ?
“በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ” ብሎ በቤቱና በቅጥሩ የማይጠፋ የዘላለም የመታሰቢያ ስም የሰጣቸው እራሱ ባለቤቱ ነው ኢሳይ56፥5
እግዚአብሔር ለጻድቃን የሰጣቸው ወይም የሚሰጣቸው ክብር በሕይወተ ሥጋ ብቻ ሳሉ አይደለም ለሞታቸውና ለአጸደ ነፍሳቸውም ጭምር የሚሆን ከብረው የሚያከብሩበት ዘላለማዊ ሥጦታ ጭምር ነው እንጂ:: “የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” መዝ116፥15
ጻድቁም ወደ ሰማዕታት አደባባይ ሄጄ በስምህ ሰማዕትነትን እቀበል ዘንድ አውዳለውና ያን እንዳደርግ እዘዝ አሉት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም መቀዳደምክን ጨረስክ ከሞት በቀር የቀረህ የለም ሁሉን ፈጽመሃል ሞትህንም እንደ ሰማዕታት ሙት አድርጌ እቀበለዋለው አላቸው :: ብዙ ቃል ኪዳንም ከሰጣቸው በኃላ አባታችን ነሐሴ 24 ቀን በ99 ዓመት ከ10ወር 10ቀናቸው ቅዱስት ነፍሳቸው ከቅዱስ ሥጋቸው ተለየች::
#የአባታችን የቅዱስ ተክለ ሃይማኖት እረድኤት በረከታቸው ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትሁን !::አሜን!
“#የጻድቃንን ሞት እኔ ልሙት፥ ፍጻሜዬም እንደ እርሱ ፍጻሜ ትሁን።” ዘኍልቁ 23፥10
.............#ይቆየን..........
ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
ነሐሴ 24 ቀን 2012ዓም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
መዝ 4፥3
ብዙዎች እግዚአብሔር በጻድቃን እንደሚገለጥ ባለማወቅ የቅዱሳኑ ነገር የእግዚአብሔርን ነገር በልጦ የሸፈነው ይመስላቸዋል :: ግን ነገሩ እንዲህ አይደለም ውኃን ከጥሩ (ከጠራው) ነገርን ከሥሩ እንዲሉ የጻድቅን ትርጉም በመጀመሪያ በአጭሩ እንመልከት::
ጻድቅ የሚለው ግሥ እውነተኛ የሚል ትርጉም ያለው ሲሆን ለብዙ ቁጥር ስንጠቀመው ጻድቃን ብለን ማናበብ እንችላለን እውነተኞች ማለታችን ነው!::
በእውነቱ "ጻድቅ" የሚለውን መቀጽል በመጀመሪያ በተገባ የሚገባው ለልዑል እግዚአብሔር ብቻ ነው :: እግዚአብሔር አምላክ እቀደስ አይል ቅዱስ እጸድቅም አይል ነገር ጻድቅ ነው ጽድቁም እንደ ቅዱሳን የጸጋ (የስጦታ) እንደ ሰይጣንም የሐሰት ሳይሆን ማንም ያልሰጠው ማንም የማይቀማው በባህሪው ጻድቅ እውነተኛ ቅዱስም አምላክ ነው ::“እንደ እግዚአብሔር ቅዱስ የለምና፥ እንደ #አምላካችንም_ጻድቅ የለምና፤ ከአንተ በቀር ቅዱስ የለም።” እንዲል መጽሐፍ 1ኛ ሳሙ 2፥2
ጻድቅ ወይም እውነተኛ ለመሆን በእውነት ማመን ፣ ስለ እውነት መናገር፣ ስለ እውነት ማስተማር፣ ስለ እውነት መኖር ይጠይቃል :: ታዲያ ይህ እውነት ማነው ካልን እግዚአብሔር ነው:: “እኔ መንገድና #እውነት ሕይወትም ነኝ፤ ” ዮሐ14፥6
ከእነዚህ እውነተኞቹ ጻድቃን መካከል የጽላሎሹ ኮከብ የእግዚ አርያ ዐይን ማረፊያ የፀጋ ዘአብ አብራክ የምመናን እረኛ የወንጌል አርበኛ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ግምባር ቀደም ናቸው:: ድካምን በማብዛት እንደ ነቢያት ወንጌልን በማስተማር እንደ ሐዋርያት በመገረፍ እንደ ሰማዕታት መሰለ ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪቆጠር በጻም በድካም ሌት ተቀን ተጉ 22ዓመት በሁለት እግራቸው ከቆሙ በኃላ ከመቆም ብዛት አንዲቱ የእግራቸው አገዳ ተሰብራ ወደቀች በዚህም ለአፍታ ሳይዘናጉ ለ7ዓመታት በአንድ እግራቸው ቆመው በትዕግሥት 29 ዓመት በጸሎት ተጋደሉ :: መጻሕፍ “እነሆ፥ በትዕግሥት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን” ያዕ5፥11 ብሏልና " #ብፁህ " አልናቸው :: የሥራዬን ጽናት የሃይማኖቴን ደግነት ግለጥ እያሉ በሕይወት ዘመናቸው በሙሉ ክርስቶስን ሲሰብኩ ቆይተዋል እንዲያውም በከተታ አውራጃ በዚህ በታመኑለት በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሲያስተምሩ ሀገሪው ሰምቶ ለዛፍ መስገድን ሊያስቆሙን ነው ከፈጣሪያችን ሊያጣሉን ነው ብለው እንደ አንበሳ ሊውጧቸው ተነሱ አባታችን ግን በልበ ሰፊነት በነገር አሳላፊነት እያለዛዘበ አስተማሯቸው ወደ ቀናች ሃይማኖትም መለሷቸው:: ይህ እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ምን ያክል ድንቅ እንደሆነ የሚያመላክት ነው እንጂ የቅዱሳኑ ሕይወት የእግዚአብሔር ነገር ነገረ እግዚአብሔርን የሸፈነ አይደለም ጻድቃን ቅዱሳን “እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፥” የሚሉ ናቸውና 1ኛ ቆሮ1፥23
እንደ ልቤ የተባለውም ቅዱስ ዳዊትም “እግዚአብሔር #በቅዱሳኑ_ላይ_ድንቅ ነው፤ የእስራኤል አምላክ እርሱ ኃይልን ብርታትንም ለሕዝቡ ይሰጣል፤ እግዚአብሔርም ይመስገን።”መዝ 67(68)፥35 ሲል የጻድቃን ሕይወት ሙሉ በሙሉ እግዚአብሔር የተገለጠበት ድንቅም የሚያደርግበት ለሕዝብም ኃይልን የሚያድልበት መሆኑን መስክሮልናል በዚህም ነገር እግዚአብሔር ይመሰገንበታል :: “መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።” ብሎ ያዘዛቸውም በእነርሱ መልካም ሕይወት የሰማይ አባታቸው እግዚአብሔር ስለሚገለጥበት ነው። ማቴ 5፥16
አንዳንድ አካላት ግን ይህን ባለ መገንዘብ ቤተክርስቲያን ከክርስቶስ ይልቅ ቅዱስ ጳውሎስን ከነገረ እግዚአብሔር ይልቅም ነገረ ቅዱሳንን አስበልጣ ትሰብካለች ይላሉ:: ነገሩ ከፈረሱ ጋሪውን እንደማስቀደም ያለ ነገር ነውና የትም አያደርስም :: ይህ ዓይነቱ አካሄድ የዋልዮሽ አካሄድ በመሆኑ መጨረሻው ገደል ነው:: የዚህ ትምህርት ምንጭም ክርስቶስ ብቻ በቂዬ ነው የምትለው የመናፍቁ ዓለም ጨዋታ ነች :: ለክርስቶስ የተቆረቆሩ በማስመሰል ምርጦቹ ቅዱሳኑን ለማራቅ አያስፈልጉም ለማለት የሚደረግ ዳርዳርታ ነች :: ቅዱሳን ማሰብ በስማቸው ዝክር ማዘከር ስማቸውን መጥራት ገድላቸውን መስማት ማሰማት የተገባ ደገኛ ሥርዓት ነው ሙሽራው ክርስቶስ ብቻ ሳይሆን ሚዜዎቹ ቅዱሳንንም መቀበል ይገባል::
እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል።ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል። ማቴ 10፥40-41 መቀበል ከነ ሚዜዎቹ ነው ማነው? እስቲ ከውጪ የመጣ ወዳጁን አንተ ና ወደ ቤቴ ግባ የያዝከው የሻንጣ ገንዘብ ግን ከቤቴ አይገባም ብሎ ወዳጁን ስለ ገንዘቡ አልቀበልም የሚለው? ቅዱሳን የክርስቶስ ገንዘቡ ናቸው :: ያለ እነርሱ ልንቀበለው አንችልም::
“የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን #ዋኖቻችሁን_አስቡ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው።”ዕብ 13፥7 እንግዚህ እግዚአብሔር ያከበረውን ማን ያቀለዋል ?
“በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ” ብሎ በቤቱና በቅጥሩ የማይጠፋ የዘላለም የመታሰቢያ ስም የሰጣቸው እራሱ ባለቤቱ ነው ኢሳይ56፥5
እግዚአብሔር ለጻድቃን የሰጣቸው ወይም የሚሰጣቸው ክብር በሕይወተ ሥጋ ብቻ ሳሉ አይደለም ለሞታቸውና ለአጸደ ነፍሳቸውም ጭምር የሚሆን ከብረው የሚያከብሩበት ዘላለማዊ ሥጦታ ጭምር ነው እንጂ:: “የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” መዝ116፥15
ጻድቁም ወደ ሰማዕታት አደባባይ ሄጄ በስምህ ሰማዕትነትን እቀበል ዘንድ አውዳለውና ያን እንዳደርግ እዘዝ አሉት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም መቀዳደምክን ጨረስክ ከሞት በቀር የቀረህ የለም ሁሉን ፈጽመሃል ሞትህንም እንደ ሰማዕታት ሙት አድርጌ እቀበለዋለው አላቸው :: ብዙ ቃል ኪዳንም ከሰጣቸው በኃላ አባታችን ነሐሴ 24 ቀን በ99 ዓመት ከ10ወር 10ቀናቸው ቅዱስት ነፍሳቸው ከቅዱስ ሥጋቸው ተለየች::
#የአባታችን የቅዱስ ተክለ ሃይማኖት እረድኤት በረከታቸው ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትሁን !::አሜን!
“#የጻድቃንን ሞት እኔ ልሙት፥ ፍጻሜዬም እንደ እርሱ ፍጻሜ ትሁን።” ዘኍልቁ 23፥10
.............#ይቆየን..........
ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
ነሐሴ 24 ቀን 2012ዓም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ