ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዘመናቱን በአራቱ ወንጌላውያን ከፍላ ዓመቱን ደግሞ በአራቱ ወቅቶች ሰድራ ወቅቱን ተንተርሳ ለልጆቿ ለአምሯቸው በተመቸ ልባቸውን በማረከ መልኩ ቃለ ወንጌልን ትመግባቸዋለች።
ዛሬ ግን በሰው ልጆች ሕይወት ውስጥ ብዙ ግዜ ስለማይስተዋሉ ተጨማሪ ሁለት ዘመኑችን እንመለከታለን ዘመነ ሳውል እና ዘመነ ጳውሎስን።
#የዘመነ_ሳውል መገለጫዎች
*ጭፍን ጥላቻ
*መደብደብ
*ማስደብደብ
*መግደል
*ማስገደል መንግሥት ሥልጣንን በመጠቀም የግድያ ደብዳቤ በክርስቲያኖች ላይ ማጻፍ
*ሰው ስለ እምነቱ እና ስለ አመለካከቱ ማሳደድ ማፈናቀል ንብረቱን ማውደም
“ሳውል ግን ቤተ ክርስቲያንን ያፈርስ ነበር፤ ወደ ሁሉም ቤት እየገባ ወንዶችንም ሴቶችንም እየጐተተ ወደ ወኅኒ አሳልፎ ይሰጥ ነበር።”
— #ሐዋ 8፥3
ሳውል ግን የጌታን ደቀ መዛሙርት እንዲገድላቸው ገና እየዛተ ወደ ሊቀ ካህናት ሄደ፥ በዚህ መንገድ ያሉትንም ሰዎች ወንዶችንም ሴቶችንም ቢያገኝ፥ እያሰረ ወደ ኢየሩሳሌም ያመጣቸው ዘንድ በደማስቆ ላሉት ምኵራቦች ደብዳቤ ከእርሱ ለመነ። ሲሄድም ወደ ደማስቆ በቀረበ ጊዜ ድንገት በእርሱ ዙሪያ ከሰማይ ብርሃን አንጸባረቀ፤ በምድርም ላይ ወድቆ ሳለ፦ ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ ሰማ። ጌታ ሆይ፥ ማን ነህ? አለው። እርሱም፦ አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል አለው። #ሐዋ 9÷15
#የዘመነ_ጳውሎስ መገለጫዎች
*መደብደብ
*መሰደድ
*መታሰር
*መታረድ
" እንደ እብድ ሰው እላለሁ፤ እኔ እበልጣለሁ፤ በድካም አብዝቼ፥ በመገረፍ አብዝቼ፥ በመታሰር አትርፌ፥ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ። አይሁድ አንድ ሲጎድል አርባ ግርፋት አምስት ጊዜ ገረፉኝ። ሦስት ጊዜ በበትር ተመታሁ፤ አንድ ጊዜ በድንጋይ ተወገርሁ፤ መርከቤ ሦስት ጊዜ ተሰበረ፤ ሌሊትና ቀን በባሕር ውስጥ ኖርሁ።
#2ኛ_ቆሮ 11÷23-25
እንባቢ ሆይ ዘመንህ የማነው? የሳውል ወይስ የጳውሎስ ዘመን?
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፮ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ /ዓ.ም
ዛሬ ግን በሰው ልጆች ሕይወት ውስጥ ብዙ ግዜ ስለማይስተዋሉ ተጨማሪ ሁለት ዘመኑችን እንመለከታለን ዘመነ ሳውል እና ዘመነ ጳውሎስን።
#የዘመነ_ሳውል መገለጫዎች
*ጭፍን ጥላቻ
*መደብደብ
*ማስደብደብ
*መግደል
*ማስገደል መንግሥት ሥልጣንን በመጠቀም የግድያ ደብዳቤ በክርስቲያኖች ላይ ማጻፍ
*ሰው ስለ እምነቱ እና ስለ አመለካከቱ ማሳደድ ማፈናቀል ንብረቱን ማውደም
“ሳውል ግን ቤተ ክርስቲያንን ያፈርስ ነበር፤ ወደ ሁሉም ቤት እየገባ ወንዶችንም ሴቶችንም እየጐተተ ወደ ወኅኒ አሳልፎ ይሰጥ ነበር።”
— #ሐዋ 8፥3
ሳውል ግን የጌታን ደቀ መዛሙርት እንዲገድላቸው ገና እየዛተ ወደ ሊቀ ካህናት ሄደ፥ በዚህ መንገድ ያሉትንም ሰዎች ወንዶችንም ሴቶችንም ቢያገኝ፥ እያሰረ ወደ ኢየሩሳሌም ያመጣቸው ዘንድ በደማስቆ ላሉት ምኵራቦች ደብዳቤ ከእርሱ ለመነ። ሲሄድም ወደ ደማስቆ በቀረበ ጊዜ ድንገት በእርሱ ዙሪያ ከሰማይ ብርሃን አንጸባረቀ፤ በምድርም ላይ ወድቆ ሳለ፦ ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ ሰማ። ጌታ ሆይ፥ ማን ነህ? አለው። እርሱም፦ አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል አለው። #ሐዋ 9÷15
#የዘመነ_ጳውሎስ መገለጫዎች
*መደብደብ
*መሰደድ
*መታሰር
*መታረድ
" እንደ እብድ ሰው እላለሁ፤ እኔ እበልጣለሁ፤ በድካም አብዝቼ፥ በመገረፍ አብዝቼ፥ በመታሰር አትርፌ፥ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ። አይሁድ አንድ ሲጎድል አርባ ግርፋት አምስት ጊዜ ገረፉኝ። ሦስት ጊዜ በበትር ተመታሁ፤ አንድ ጊዜ በድንጋይ ተወገርሁ፤ መርከቤ ሦስት ጊዜ ተሰበረ፤ ሌሊትና ቀን በባሕር ውስጥ ኖርሁ።
#2ኛ_ቆሮ 11÷23-25
እንባቢ ሆይ ዘመንህ የማነው? የሳውል ወይስ የጳውሎስ ዘመን?
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፮ ቀን /፳ ፻ ፲ ፫ /ዓ.ም