ዐውደ ምሕረት
3.67K subscribers
932 photos
24 videos
271 files
195 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#በኩረ #ሙታን #ወትንሳኤ

👉👉ክፍል አንድ👈👈👈

ክርስቶስ ተንስዓ ሙታን
በአቢይ ኃይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አግአዞ ለዓዳም
ሰላም
እምይዜሰ
ኮነ
ፍስሐ ወሰላም

የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የአስራት ልጆች የቅዱሳን ወዳጆች እንደምን ቆያችሁ? አሜን የትንሳኤያችን በኩር አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከባሕሪይ አባቱ ከእግዚአብሔር አብ ከባሕሪይ ሕይወቱ ከእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጋር ዛሬም ዘውትርም እስከ ዘለዓለም ድረስ በፍጥረቱ አንደበት የከበረ የተመሰገነ ይሁን፡፡ እንኳን ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን፡፡

በኩር ማለት የመጀመሪያ ቀዳሚ አለቃ ሹም ማለት ነው፡፡ በኩረ ሙታን ወትንሳኤ ማለት ደግሞ የሙታን እና የትንሳኤ ሁሉ መጀመሪያ ቀዳሚ ማለት ነው፡፡ ይህም የአምላካችን የመድኃታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሞቱ እና ትንሳኤው በኩር እየተባለ ይጠራል፡፡ ይህ ሞት እና ትንሳኤ በኩር ለምን ተባለ የሚለውን ከማየታችን በፊት ራሱ ክርስቶስ በኩር ተብሎ እንደሚጠራ ማወቅ ይኖርብናል፡፡

ክርስቶስ በኩር የተባለው ቀዳሚ የሌለው ቀዳማዊ ማንም ያልሾመው አምላክ ማንም ሊሽረው የማይችል አለቃ እርሱ በመሆኑ በኩር ተብሏል፡፡ ኢሣ 9፡6 አንድም በኩር የእናቱን ማሕጸን የከፈተ የመጀሪያ ልጅ ማለት ነው፡፡ ጌታችንም የአብ ተቀዳሚም ተከታይ የሌለው አንድያ የባሕሪይ ልጁ በመሆኑ በኩር ተብሏል፡፡ አግዚአብሔር አብ ጌታችንን ሲወልደው በጊዜ ባለመቀዳደም በስልጣን ባለመበላለጥ እንጂ ሥጋዊ አባት ልጁን እንደሚበልጥ ያለ አይደለም፡፡ ይልቁኑ በስልጣን የሚተካከለውን አንድ የሚሆነውን በጊዜም የማይበልጠውን አንድያ ልጁን ከፍጥረት ሁሉ በኩር የሆነውን አንድያ ልጁን ወለደው እንጂ፡፡ ዮሐ 10፡30 መዝ 2፡7
አንድም ክርስቶስ በኩረ ማርያም ነው፡፡ የእመቤታችን የመጀመሪያና ብቸኛ ልጅ በመሆኑ በኩረ ማርያም ተብሏል፡፡ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለ ተፈትሖ ማሕጸን በድንግልና በመሆኑ ከሌሎች የሰው ልጆች በኩራት ሁሉ የተለየ ነው፡፡ ማቴ 1፡18 ኢሣ 7፡14
ሌላው ከላይ በርዕሳችን እንዳነሳነው ክርስቶስ በኩረ ትንሳኤ እንዲሁም በኩረ ሙታን ይባላል፡፡ የሰው ልጅ ሁሉ ይሞታል፡፡ ለሞት ያልተገዛ ወደፊትም የማይገዛም ማንም የለም፡፡ ክርስቶስም ቢሆን ሞትን ቀምሷል፡፡ ነገር ግን የኛ የሰው ልጆች እና የጌታችን ሞት ልዩ እንደሆነ ማወቅ ይገባል፡፡ ይህም ስለምንድን ነው ቢሉ ሁለት ምክንያቶችን ማንሳት ይገባል፡፡
፩. ሞት ሁሉን እንዲገዛ ስልጣን የሰጠው ራሱ እግዚአብሔር በመሆኑ፡፡ ይህ ማለት ሞት ሁሉንም ቢገዛም ክርስቶስ ግን በሞት አልተገዛም፡፡ ይህንንም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሲናገር ‹‹ሁሉ በክርስቶስ ሕያው ይሆናሉ፡፡ … የኋለኛው ጠላት የሚሻረው ሞት ነው፡፡ ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቷልና፡፡ ነገር ግን ሁሉ ተገዝቷል ሲል ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው፡፡ ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል፡፡›› 1ኛ ቆሮ 14፡22-28 በቃሉ መሰረት ሞት ሁሉን እንደገዛ ነገር ግን ሁሉን ካስገዛለት በቀር ብሎ ክርስቶስ በሞት እንዳልተገዛ ይነግረናል፡፡ ነገር ግን ክርስቶስም ሞትን መቅመሱንም ቀጥሎ ባለው ቃል አስረድቷ፡፡ ‹‹በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል፡፡›› በማለት፡፡
፪. ሁለተኛው ምክኒያት ክርስቶስ ሞትን የቀመሰው ራሱ እግዚአብሔር በወደደ ጊዜ በፈቃዱ በመሆኑ ነው፡፡ ለእኛ ለሰው ልጆች ሞት በፈቃዳችን ወይም በእቅዳችን አይደለም፡፡ የጌታችን ሞት ግን ባሰባት እና ባቀዳት ጊዜ ነው የተፈጸመችው፡፡ ‹‹ጊዜዬ ገና አልደረሰም፡፡›› ዮሐ 2፡2 እንዲሁም ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በትንቢት ‹‹እኔ ተኛሁ አንቀላፋሁም፡፡›› ብሎ የጌታችን ሞት በራሱ በፈቃዱ መሆኑን ገልጦልናል፡፡ መዝ 3፡5 በኋላ ጊዜው ሲደርስም ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ሲለይ ‹‹አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለው፡፡›› ብሎ በፈቃዱ ነፍሱን ከሥጋው ለየ፡፡ ሉቃ 23፡46 እኛ የሰው ልጆች ግን መሞታችንን አናውቅም፡፡ ለዚህ ነው ‹‹ቀኒቱን እና ሰዓቱን አታውቁምና እግዲህ ንቁ፡፡›› ብሎ ጌታችን በወንጌል የተናገረው፡፡ ማቴ 25፡12 ሉቃ 12፡20 ጌታችን ግን ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው የሚለየው በፈቃዱና በስልጣኑ እንደሆነ ሲናገር ‹‹ነፍሴን ላኖራትም ላነሳትም ስልጣን አለኝ፡፡›› ሲል አስቀድሞ ተናግሯ፡፡ ዮሐ 10፡18 ሌላው ማስተዋል የሚገባን ክርስቶስ ሞተ ሲባል እንደኛ በድን ሆነ ማለት አይደለም፡፡ እንዴት ቢሉ ወደ መቃብር የወረደው ሥጋ መለኮት የተዋሐደው ነፍስ የተለየው በመሆኑ ነው፡፡ ‹‹እኔ ተኝቻለው ልቤ ግን ነቅቷል፡፡›› ብሎ ጠቢቡ ሰለሞን በትንቢት ሲናገር እንዲሁም ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹በሥጋው ሞተ በመንፈሱ ግን ሕያው ሆነ፡፡›› ብሎ አስረግጦናል፡፡ መኃ 5፡2 እና 1ኛ ጴጥ 3፡19
በመሆኑም ከላይ ባነሳናቸው ሁለት ምክንያቶች ክርስቶስ በኩረ ሙታን እንደሚባል አይተናል፡፡ በቀጣዩ ጽሑፋችን ደግሞ ክርስቶስ በኩረ ትንሳኤ የተባለበትን ምክንያት እንመለከታለን፡፡ የእግዚአብሔር ቸርነት የእመቤታችን አማላጅነት የቅዱሳኑ ተራዳኢነት አይለየን፡፡

ይቆየን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር፡፡

በወንድማችን #አቤኔዘር የተዘጋጀ

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
Forwarded from ዐውደ ምሕረት
#በኩረ #ሙታን #ወትንሳኤ

👉👉ክፍል አንድ👈👈👈

ክርስቶስ ተንስዓ ሙታን
በአቢይ ኃይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አግአዞ ለዓዳም
ሰላም
እምይዜሰ
ኮነ
ፍስሐ ወሰላም

የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የአስራት ልጆች የቅዱሳን ወዳጆች እንደምን ቆያችሁ? አሜን የትንሳኤያችን በኩር አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከባሕሪይ አባቱ ከእግዚአብሔር አብ ከባሕሪይ ሕይወቱ ከእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጋር ዛሬም ዘውትርም እስከ ዘለዓለም ድረስ በፍጥረቱ አንደበት የከበረ የተመሰገነ ይሁን፡፡ እንኳን ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን፡፡

በኩር ማለት የመጀመሪያ ቀዳሚ አለቃ ሹም ማለት ነው፡፡ በኩረ ሙታን ወትንሳኤ ማለት ደግሞ የሙታን እና የትንሳኤ ሁሉ መጀመሪያ ቀዳሚ ማለት ነው፡፡ ይህም የአምላካችን የመድኃታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሞቱ እና ትንሳኤው በኩር እየተባለ ይጠራል፡፡ ይህ ሞት እና ትንሳኤ በኩር ለምን ተባለ የሚለውን ከማየታችን በፊት ራሱ ክርስቶስ በኩር ተብሎ እንደሚጠራ ማወቅ ይኖርብናል፡፡

ክርስቶስ በኩር የተባለው ቀዳሚ የሌለው ቀዳማዊ ማንም ያልሾመው አምላክ ማንም ሊሽረው የማይችል አለቃ እርሱ በመሆኑ በኩር ተብሏል፡፡ ኢሣ 9፡6 አንድም በኩር የእናቱን ማሕጸን የከፈተ የመጀሪያ ልጅ ማለት ነው፡፡ ጌታችንም የአብ ተቀዳሚም ተከታይ የሌለው አንድያ የባሕሪይ ልጁ በመሆኑ በኩር ተብሏል፡፡ አግዚአብሔር አብ ጌታችንን ሲወልደው በጊዜ ባለመቀዳደም በስልጣን ባለመበላለጥ እንጂ ሥጋዊ አባት ልጁን እንደሚበልጥ ያለ አይደለም፡፡ ይልቁኑ በስልጣን የሚተካከለውን አንድ የሚሆነውን በጊዜም የማይበልጠውን አንድያ ልጁን ከፍጥረት ሁሉ በኩር የሆነውን አንድያ ልጁን ወለደው እንጂ፡፡ ዮሐ 10፡30 መዝ 2፡7
አንድም ክርስቶስ በኩረ ማርያም ነው፡፡ የእመቤታችን የመጀመሪያና ብቸኛ ልጅ በመሆኑ በኩረ ማርያም ተብሏል፡፡ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለ ተፈትሖ ማሕጸን በድንግልና በመሆኑ ከሌሎች የሰው ልጆች በኩራት ሁሉ የተለየ ነው፡፡ ማቴ 1፡18 ኢሣ 7፡14
ሌላው ከላይ በርዕሳችን እንዳነሳነው ክርስቶስ በኩረ ትንሳኤ እንዲሁም በኩረ ሙታን ይባላል፡፡ የሰው ልጅ ሁሉ ይሞታል፡፡ ለሞት ያልተገዛ ወደፊትም የማይገዛም ማንም የለም፡፡ ክርስቶስም ቢሆን ሞትን ቀምሷል፡፡ ነገር ግን የኛ የሰው ልጆች እና የጌታችን ሞት ልዩ እንደሆነ ማወቅ ይገባል፡፡ ይህም ስለምንድን ነው ቢሉ ሁለት ምክንያቶችን ማንሳት ይገባል፡፡
፩. ሞት ሁሉን እንዲገዛ ስልጣን የሰጠው ራሱ እግዚአብሔር በመሆኑ፡፡ ይህ ማለት ሞት ሁሉንም ቢገዛም ክርስቶስ ግን በሞት አልተገዛም፡፡ ይህንንም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሲናገር ‹‹ሁሉ በክርስቶስ ሕያው ይሆናሉ፡፡ … የኋለኛው ጠላት የሚሻረው ሞት ነው፡፡ ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቷልና፡፡ ነገር ግን ሁሉ ተገዝቷል ሲል ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው፡፡ ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል፡፡›› 1ኛ ቆሮ 14፡22-28 በቃሉ መሰረት ሞት ሁሉን እንደገዛ ነገር ግን ሁሉን ካስገዛለት በቀር ብሎ ክርስቶስ በሞት እንዳልተገዛ ይነግረናል፡፡ ነገር ግን ክርስቶስም ሞትን መቅመሱንም ቀጥሎ ባለው ቃል አስረድቷ፡፡ ‹‹በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል፡፡›› በማለት፡፡
፪. ሁለተኛው ምክኒያት ክርስቶስ ሞትን የቀመሰው ራሱ እግዚአብሔር በወደደ ጊዜ በፈቃዱ በመሆኑ ነው፡፡ ለእኛ ለሰው ልጆች ሞት በፈቃዳችን ወይም በእቅዳችን አይደለም፡፡ የጌታችን ሞት ግን ባሰባት እና ባቀዳት ጊዜ ነው የተፈጸመችው፡፡ ‹‹ጊዜዬ ገና አልደረሰም፡፡›› ዮሐ 2፡2 እንዲሁም ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በትንቢት ‹‹እኔ ተኛሁ አንቀላፋሁም፡፡›› ብሎ የጌታችን ሞት በራሱ በፈቃዱ መሆኑን ገልጦልናል፡፡ መዝ 3፡5 በኋላ ጊዜው ሲደርስም ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ሲለይ ‹‹አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለው፡፡›› ብሎ በፈቃዱ ነፍሱን ከሥጋው ለየ፡፡ ሉቃ 23፡46 እኛ የሰው ልጆች ግን መሞታችንን አናውቅም፡፡ ለዚህ ነው ‹‹ቀኒቱን እና ሰዓቱን አታውቁምና እግዲህ ንቁ፡፡›› ብሎ ጌታችን በወንጌል የተናገረው፡፡ ማቴ 25፡12 ሉቃ 12፡20 ጌታችን ግን ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው የሚለየው በፈቃዱና በስልጣኑ እንደሆነ ሲናገር ‹‹ነፍሴን ላኖራትም ላነሳትም ስልጣን አለኝ፡፡›› ሲል አስቀድሞ ተናግሯ፡፡ ዮሐ 10፡18 ሌላው ማስተዋል የሚገባን ክርስቶስ ሞተ ሲባል እንደኛ በድን ሆነ ማለት አይደለም፡፡ እንዴት ቢሉ ወደ መቃብር የወረደው ሥጋ መለኮት የተዋሐደው ነፍስ የተለየው በመሆኑ ነው፡፡ ‹‹እኔ ተኝቻለው ልቤ ግን ነቅቷል፡፡›› ብሎ ጠቢቡ ሰለሞን በትንቢት ሲናገር እንዲሁም ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹በሥጋው ሞተ በመንፈሱ ግን ሕያው ሆነ፡፡›› ብሎ አስረግጦናል፡፡ መኃ 5፡2 እና 1ኛ ጴጥ 3፡19
በመሆኑም ከላይ ባነሳናቸው ሁለት ምክንያቶች ክርስቶስ በኩረ ሙታን እንደሚባል አይተናል፡፡ በቀጣዩ ጽሑፋችን ደግሞ ክርስቶስ በኩረ ትንሳኤ የተባለበትን ምክንያት እንመለከታለን፡፡ የእግዚአብሔር ቸርነት የእመቤታችን አማላጅነት የቅዱሳኑ ተራዳኢነት አይለየን፡፡

ይቆየን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር፡፡

በወንድማችን #አቤኔዘር የተዘጋጀ

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#በኩረ #ሙታን #ወትንሳኤ

👉👉ክፍል አንድ👈👈👈

ክርስቶስ ተንስዓ ሙታን
በአቢይ ኃይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አግአዞ ለዓዳም
ሰላም
እምይዜሰ
ኮነ
ፍስሐ ወሰላም

የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የአስራት ልጆች የቅዱሳን ወዳጆች እንደምን ቆያችሁ? አሜን የትንሳኤያችን በኩር አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከባሕሪይ አባቱ ከእግዚአብሔር አብ ከባሕሪይ ሕይወቱ ከእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጋር ዛሬም ዘውትርም እስከ ዘለዓለም ድረስ በፍጥረቱ አንደበት የከበረ የተመሰገነ ይሁን፡፡ እንኳን ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን፡፡

በኩር ማለት የመጀመሪያ ቀዳሚ አለቃ ሹም ማለት ነው፡፡ በኩረ ሙታን ወትንሳኤ ማለት ደግሞ የሙታን እና የትንሳኤ ሁሉ መጀመሪያ ቀዳሚ ማለት ነው፡፡ ይህም የአምላካችን የመድኃታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሞቱ እና ትንሳኤው በኩር እየተባለ ይጠራል፡፡ ይህ ሞት እና ትንሳኤ በኩር ለምን ተባለ የሚለውን ከማየታችን በፊት ራሱ ክርስቶስ በኩር ተብሎ እንደሚጠራ ማወቅ ይኖርብናል፡፡

ክርስቶስ በኩር የተባለው ቀዳሚ የሌለው ቀዳማዊ ማንም ያልሾመው አምላክ ማንም ሊሽረው የማይችል አለቃ እርሱ በመሆኑ በኩር ተብሏል፡፡ ኢሣ 9፡6 አንድም በኩር የእናቱን ማሕጸን የከፈተ የመጀሪያ ልጅ ማለት ነው፡፡ ጌታችንም የአብ ተቀዳሚም ተከታይ የሌለው አንድያ የባሕሪይ ልጁ በመሆኑ በኩር ተብሏል፡፡ አግዚአብሔር አብ ጌታችንን ሲወልደው በጊዜ ባለመቀዳደም በስልጣን ባለመበላለጥ እንጂ ሥጋዊ አባት ልጁን እንደሚበልጥ ያለ አይደለም፡፡ ይልቁኑ በስልጣን የሚተካከለውን አንድ የሚሆነውን በጊዜም የማይበልጠውን አንድያ ልጁን ከፍጥረት ሁሉ በኩር የሆነውን አንድያ ልጁን ወለደው እንጂ፡፡ ዮሐ 10፡30 መዝ 2፡7
አንድም ክርስቶስ በኩረ ማርያም ነው፡፡ የእመቤታችን የመጀመሪያና ብቸኛ ልጅ በመሆኑ በኩረ ማርያም ተብሏል፡፡ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለ ተፈትሖ ማሕጸን በድንግልና በመሆኑ ከሌሎች የሰው ልጆች በኩራት ሁሉ የተለየ ነው፡፡ ማቴ 1፡18 ኢሣ 7፡14
ሌላው ከላይ በርዕሳችን እንዳነሳነው ክርስቶስ በኩረ ትንሳኤ እንዲሁም በኩረ ሙታን ይባላል፡፡ የሰው ልጅ ሁሉ ይሞታል፡፡ ለሞት ያልተገዛ ወደፊትም የማይገዛም ማንም የለም፡፡ ክርስቶስም ቢሆን ሞትን ቀምሷል፡፡ ነገር ግን የኛ የሰው ልጆች እና የጌታችን ሞት ልዩ እንደሆነ ማወቅ ይገባል፡፡ ይህም ስለምንድን ነው ቢሉ ሁለት ምክንያቶችን ማንሳት ይገባል፡፡
፩. ሞት ሁሉን እንዲገዛ ስልጣን የሰጠው ራሱ እግዚአብሔር በመሆኑ፡፡ ይህ ማለት ሞት ሁሉንም ቢገዛም ክርስቶስ ግን በሞት አልተገዛም፡፡ ይህንንም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሲናገር ‹‹ሁሉ በክርስቶስ ሕያው ይሆናሉ፡፡ … የኋለኛው ጠላት የሚሻረው ሞት ነው፡፡ ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቷልና፡፡ ነገር ግን ሁሉ ተገዝቷል ሲል ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው፡፡ ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል፡፡›› 1ኛ ቆሮ 14፡22-28 በቃሉ መሰረት ሞት ሁሉን እንደገዛ ነገር ግን ሁሉን ካስገዛለት በቀር ብሎ ክርስቶስ በሞት እንዳልተገዛ ይነግረናል፡፡ ነገር ግን ክርስቶስም ሞትን መቅመሱንም ቀጥሎ ባለው ቃል አስረድቷ፡፡ ‹‹በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል፡፡›› በማለት፡፡
፪. ሁለተኛው ምክኒያት ክርስቶስ ሞትን የቀመሰው ራሱ እግዚአብሔር በወደደ ጊዜ በፈቃዱ በመሆኑ ነው፡፡ ለእኛ ለሰው ልጆች ሞት በፈቃዳችን ወይም በእቅዳችን አይደለም፡፡ የጌታችን ሞት ግን ባሰባት እና ባቀዳት ጊዜ ነው የተፈጸመችው፡፡ ‹‹ጊዜዬ ገና አልደረሰም፡፡›› ዮሐ 2፡2 እንዲሁም ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በትንቢት ‹‹እኔ ተኛሁ አንቀላፋሁም፡፡›› ብሎ የጌታችን ሞት በራሱ በፈቃዱ መሆኑን ገልጦልናል፡፡ መዝ 3፡5 በኋላ ጊዜው ሲደርስም ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ሲለይ ‹‹አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለው፡፡›› ብሎ በፈቃዱ ነፍሱን ከሥጋው ለየ፡፡ ሉቃ 23፡46 እኛ የሰው ልጆች ግን መሞታችንን አናውቅም፡፡ ለዚህ ነው ‹‹ቀኒቱን እና ሰዓቱን አታውቁምና እግዲህ ንቁ፡፡›› ብሎ ጌታችን በወንጌል የተናገረው፡፡ ማቴ 25፡12 ሉቃ 12፡20 ጌታችን ግን ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው የሚለየው በፈቃዱና በስልጣኑ እንደሆነ ሲናገር ‹‹ነፍሴን ላኖራትም ላነሳትም ስልጣን አለኝ፡፡›› ሲል አስቀድሞ ተናግሯ፡፡ ዮሐ 10፡18 ሌላው ማስተዋል የሚገባን ክርስቶስ ሞተ ሲባል እንደኛ በድን ሆነ ማለት አይደለም፡፡ እንዴት ቢሉ ወደ መቃብር የወረደው ሥጋ መለኮት የተዋሐደው ነፍስ የተለየው በመሆኑ ነው፡፡ ‹‹እኔ ተኝቻለው ልቤ ግን ነቅቷል፡፡›› ብሎ ጠቢቡ ሰለሞን በትንቢት ሲናገር እንዲሁም ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹በሥጋው ሞተ በመንፈሱ ግን ሕያው ሆነ፡፡›› ብሎ አስረግጦናል፡፡ መኃ 5፡2 እና 1ኛ ጴጥ 3፡19
በመሆኑም ከላይ ባነሳናቸው ሁለት ምክንያቶች ክርስቶስ በኩረ ሙታን እንደሚባል አይተናል፡፡ በቀጣዩ ጽሑፋችን ደግሞ ክርስቶስ በኩረ ትንሳኤ የተባለበትን ምክንያት እንመለከታለን፡፡ የእግዚአብሔር ቸርነት የእመቤታችን አማላጅነት የቅዱሳኑ ተራዳኢነት አይለየን፡፡

ይቆየን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር፡፡

በወንድማችን #አቤኔዘር የተዘጋጀ

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit