ስለጠየቁ እናመሰግናለን በተለይ ደግሞ ወቅቱንና ጊዜውን ያገናዘበ ዘመኑን የዋጀ ጥያቄ በመሆኑ ይበል የሚያሰኝ ነው ::በርቱልን:: የቤተ ክርስቲያን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር የሕይወትን ቃል ያሰማልን::
ምላሽ :- ወደ አተታውና ወደ መደመደሚያው ከመሄዳችን በፊት አጠር ያለና ቀጥተኛ ምላሽ እንስጥ :: ቤተ ክርስቲያን በልጆቿ ላይ እየደረሰባቸው ያለውን ግድያ እንዴት ታየዋለች ? ለሚለው ጥያቄ ቤተ ክርስቲያን የልጆቿን ሞት እንደ ሰማዕታት ሞት ታየዋለች:: የሚል ግልጽ መልስ እንሰጣለን :: ሰማዕታት ደግሞ ለቤተ ክርስቲያን የሐዘኟ ምንጮች ፣የጠባሳዋ ማስታወሻዎች ፣ የቁስሏ ጥዝጣዜዎ ሳይሆኑ ጌጦቿ ናቸው ::ጌጥን ደግሞ ሁል ጊዜ ስለ እርሱ እያወሱ ያጌጡበታል ይዋውበታል እንጂ አፍረው አይሸሽጉትም ቤተ ክርስቲያንም በጌጦቿ አታፍርባቸውም ከዛ ይልቅ ቤተ ክርስቲያ አንጻ ፣ታቦት ቀርጻ፣ ገድል ጽፋ ፣ቀን ቆጥራ ዘላለም ስታዘክራቸው ትኖራለች::
ሰማዕትነት የራሱ የሆነ ሃይማኖታዊ ፋይዳና ረብ ያለው የቅድስና ማግኛ አንዱ መንገድ ነው :: ቢሆንም ግን ሁሉም ክርስቲያን አንገቱን ለሰይፍ ሰቶ ሃይማኖቱን ያለ ተከታይ ቤተ ክርስቲያንን ያለ ቀዳሽ ሀገርን ያለ ወራሽ ባዶ አርጎ ያስቀራት ማለት አይደለም :: ክርስትና ቀኝ ጉንጭህን ለሚመታህ ግራህን ደግሞ አዙረህ ስጠው የምትል የፍቅር ሕግ ብትሆንም ቅሉ ዝም ብለህ ስትጠፈጠፍ ሁለ ግባ ማለት ግን አይደለም የእግዚአብሔር መቅደስ የሆነ ሰውነታችን ማንም እንዲጠፈጥፈው አይደለም በአምሳሉ አክብሮ የፈጠረን :: እንዲያውም አንድ አባት አንድ ወጠጤ መቶ በጥፊ ፊታቸውን ይመታቸዋል እርሳቸውም እንደ ወንጌሉ ብለው ሌላው ጉንጫቸውን አዙረው ይሰጡታል ያም ደፋር ወጠጤ ያለ እርህራሄ ደግሞ በዚህ በኩልም ይመታቸዋል ጥፊው በጣም ያመማቸው አባም መልሰው የሁለት ጥፊ እጥፍ በሚሆን ቦክስ መተው መሬት ላይ ይዘርሩታል ወጠጤውም እንዴ አባ ወንጌል ተላለፉ እኮ ቢላቸው ውይ ልጄ አዙረ ስጠው እንጂ ደጋግመህ ስጠው አላለም አሉት ይባላል። ሰማዕትነት የራሱ ወግና ሥርዓት ያለው እንጂ ዝም ብሎ ሄዶ ከእሳት መማገድ፣ በሰይፍ ማለቅ በጥይት መደብደብ ማለት አይደለም ስለዚህ ክርስቲያኖት በወንድሞቻችን እየደረሰ ያለሁን መከራ እያየን እየተሳቀቅን ሃይማኖት መለወጥ ወደ ኃላ ማፈግፈግ ወይም እንደ ሰማዕታት ብለን ደግሞ ተገዝግዘን ማለቅ ብቻ የለብንም ክርስቲያን አንድ የሀሳብ ጽንፍ ይዞ የሚቆም ጽንፈኛ አይደለም ነገሮችን በማገናዘብ በሚዛናዊነት ይቆማል እንጂ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ያስተማረን “እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ።” ብሎ ነው ማቴዎስ 10፥16 ::
በተአምረ ኢየሱስ ላይ ተጽፍ እንደምናነበው ህጻኑ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ህጻናት ጠባይ ሲጫወት ሲታዘዝ ሲወድቅ ሲነሳ እናያለን በዚሁ የህጻናት ጠባይም ትምህርት ቤት ገብቶ ሳለ የመምህሩን የመጻፊያ ቀለም ሳያውቅ ጥቁሩን ከነጩ ይደባልቀዋል መምህሩም ቁጡ ነበርና የምጽፍበትን ቀለም ደፋህ ይልቁኑ ጥቁሩን ከነጩ ደባለክብኝ ብሎ ህጻኑን ኢየሱስ ክርስቶስን በጥፊ መታው ይህን ጊዜ ግን ግራ ጉንጭህን ለሚመታህ ቀኝህን ደግሞ አዙረ ስጠው ብሎ የሚያስተምር አምላክ ሆኖ ሳለ አዙሮ ግይ ጉንጩን ሲሰጠው አንመለከትም ከዛ ይልቅ መምህሩን ጠየቀው :: እንዲ ሲል መምህር ያጠፋሁብህ እንደሆነ አስተካክል ትለኛለ እንጂ ለምን ትመታኛለህ ??? አለው ። የተደባለቀውንም ጥቁርና ነጭ ቀለምም በተአምራት ለየ ብቻ ለይቶ ሰጠው:: እንደ ሰውነቱ አጠፋ እንደ አምላክነቱ ጥቁሩን ከነጭ ለይቶ ሰጠው :: ታዲያ ከዚህ የምንማረው ቀኝ ጉንጭህን ለሚመታ ግራህን ደግሞ አዙረ ስጠው የሚለውን ይዞ ሲጠፋጠፉሁ መዋል ፍጽም አግባብ አይደለም ሰማዕታትም አያሰኝም ከዛ ይልቅ ለምን ትመታኛለህ ማለቱና እራስን ማስከበሩ የተገባ ነው ። ዛሬም በልዮ ልዮ ዱላ የሚመቱን ቁጡ መመህራኖች በዝተውብናል ለምን ትመቱናላችሁ ብለን ልንጠይቅ ይገባል።። “ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፥ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው።” ሮሜ 8፥36 ::
ታድያ ምን እናድርግ?
#ስለ ቀናች ሃይማኖት #መጋደል አለብን::
ክርቲያኖች በሃይማኖታችን ጸንተን መሞት ብቻ ሳይሆን መኖርም ተፈቅዶልናል “ወዳጆች ሆይ፥ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።” ይሁዳ 1÷3
ማስታወሻ :- መጋደል ሲባል ቆሞ መገደል ማለት አይደለም ባንገል እንኳ እንዳንሞት እራሳችንን መከላከል መቻል ማለት ነው :: ልክ ድብድብ ስንል የሁለት ሰዎች ሱታፌ ያለበት ኩነት እንደሆነ ሁሉ መጋደልም እንዲሁ ማለት ነው አንዱ ወገን ብቻ የሚያጠቃበት ከሆነ ድብደባ እንጂ ድብድብ አያሰኘውም ::
እኛ ክርስቲያኖች ሙስሊሙ ያርደናል ፖለቲካው ያቃጥለናል ሰይጣን ይሸምቅብናል መለያየት ያተኩሰናል ጴንጤው ያሰናክለናል ነገር ግን ይህ የክርስቲያኖች ጠባይ ነው በመቱን ቁጥር እንደ ሚስማር እንጠብቃለን በገፉሁን ቁጥር እንደ ቅቤ ከፍ እንልና የራስ አክሊል እንሆናለን የሰማዕታት ደም ዘር ነውና ሊቀንሱን ሲያርዱን 30፣60፣100 ፍሬ ሆነን በዝተን እናፈራለን ።
#በጸሎት እንትጋ
ክርስቲያኖች በሃይማኖት ነቅ የሌለባቸው ጻድቃኖች(እውነተኞች) ናቸው ። በመሆኑም በእምነት ሆነው የሚጸልዮት ጸሎት ተሰሚነት አለው ጸሎት የክርስቲያኖች ዋነኛ መሳሪያ ነው::“እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ። ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።” ያዕቆብ 5፥16
#ስለ ሀገራችን ጸልዮ
#ሰለ ሃይማኖታችን ጸልዮ
#ስለ አንድነታችን ጸልዮ
“ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው።” ማቴ26፥41
“በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፤” ኤፌሶን 6፥18
#ቀርበን እንወቃት እንማራት
የማያውቁትሀገር አይናፍቅም ነውና ይበልጥ ተቆርቋሪዎቿ ለመሆን ከፈለግን ወደ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀርበን እንማር ታሪኳን እናጥና ያሳለፈችሁን የመከራ ዘመን እንዴት እንዳለፈችሁ መርምረን ለነገ ችግሯ መፍትኤ እናብጅላት::
" የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ። መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።ስለዚህ በክፉው ቀን ለመቃወም፥ ሁሉንም ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ። እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ታጥቃችሁ፥ የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፥ በሰላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ፤ በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤ የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ #እርሱም_የእግዚአብሔር ቃል ነው።" ኤፌ 6 ÷11-17 ይቆየን
ሐምሌ 26 ቀን ዕለተ እሁድ
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ ማርያም
@YEAWEDIMERITE
ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ምላሽ :- ወደ አተታውና ወደ መደመደሚያው ከመሄዳችን በፊት አጠር ያለና ቀጥተኛ ምላሽ እንስጥ :: ቤተ ክርስቲያን በልጆቿ ላይ እየደረሰባቸው ያለውን ግድያ እንዴት ታየዋለች ? ለሚለው ጥያቄ ቤተ ክርስቲያን የልጆቿን ሞት እንደ ሰማዕታት ሞት ታየዋለች:: የሚል ግልጽ መልስ እንሰጣለን :: ሰማዕታት ደግሞ ለቤተ ክርስቲያን የሐዘኟ ምንጮች ፣የጠባሳዋ ማስታወሻዎች ፣ የቁስሏ ጥዝጣዜዎ ሳይሆኑ ጌጦቿ ናቸው ::ጌጥን ደግሞ ሁል ጊዜ ስለ እርሱ እያወሱ ያጌጡበታል ይዋውበታል እንጂ አፍረው አይሸሽጉትም ቤተ ክርስቲያንም በጌጦቿ አታፍርባቸውም ከዛ ይልቅ ቤተ ክርስቲያ አንጻ ፣ታቦት ቀርጻ፣ ገድል ጽፋ ፣ቀን ቆጥራ ዘላለም ስታዘክራቸው ትኖራለች::
ሰማዕትነት የራሱ የሆነ ሃይማኖታዊ ፋይዳና ረብ ያለው የቅድስና ማግኛ አንዱ መንገድ ነው :: ቢሆንም ግን ሁሉም ክርስቲያን አንገቱን ለሰይፍ ሰቶ ሃይማኖቱን ያለ ተከታይ ቤተ ክርስቲያንን ያለ ቀዳሽ ሀገርን ያለ ወራሽ ባዶ አርጎ ያስቀራት ማለት አይደለም :: ክርስትና ቀኝ ጉንጭህን ለሚመታህ ግራህን ደግሞ አዙረህ ስጠው የምትል የፍቅር ሕግ ብትሆንም ቅሉ ዝም ብለህ ስትጠፈጠፍ ሁለ ግባ ማለት ግን አይደለም የእግዚአብሔር መቅደስ የሆነ ሰውነታችን ማንም እንዲጠፈጥፈው አይደለም በአምሳሉ አክብሮ የፈጠረን :: እንዲያውም አንድ አባት አንድ ወጠጤ መቶ በጥፊ ፊታቸውን ይመታቸዋል እርሳቸውም እንደ ወንጌሉ ብለው ሌላው ጉንጫቸውን አዙረው ይሰጡታል ያም ደፋር ወጠጤ ያለ እርህራሄ ደግሞ በዚህ በኩልም ይመታቸዋል ጥፊው በጣም ያመማቸው አባም መልሰው የሁለት ጥፊ እጥፍ በሚሆን ቦክስ መተው መሬት ላይ ይዘርሩታል ወጠጤውም እንዴ አባ ወንጌል ተላለፉ እኮ ቢላቸው ውይ ልጄ አዙረ ስጠው እንጂ ደጋግመህ ስጠው አላለም አሉት ይባላል። ሰማዕትነት የራሱ ወግና ሥርዓት ያለው እንጂ ዝም ብሎ ሄዶ ከእሳት መማገድ፣ በሰይፍ ማለቅ በጥይት መደብደብ ማለት አይደለም ስለዚህ ክርስቲያኖት በወንድሞቻችን እየደረሰ ያለሁን መከራ እያየን እየተሳቀቅን ሃይማኖት መለወጥ ወደ ኃላ ማፈግፈግ ወይም እንደ ሰማዕታት ብለን ደግሞ ተገዝግዘን ማለቅ ብቻ የለብንም ክርስቲያን አንድ የሀሳብ ጽንፍ ይዞ የሚቆም ጽንፈኛ አይደለም ነገሮችን በማገናዘብ በሚዛናዊነት ይቆማል እንጂ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ያስተማረን “እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ።” ብሎ ነው ማቴዎስ 10፥16 ::
በተአምረ ኢየሱስ ላይ ተጽፍ እንደምናነበው ህጻኑ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ህጻናት ጠባይ ሲጫወት ሲታዘዝ ሲወድቅ ሲነሳ እናያለን በዚሁ የህጻናት ጠባይም ትምህርት ቤት ገብቶ ሳለ የመምህሩን የመጻፊያ ቀለም ሳያውቅ ጥቁሩን ከነጩ ይደባልቀዋል መምህሩም ቁጡ ነበርና የምጽፍበትን ቀለም ደፋህ ይልቁኑ ጥቁሩን ከነጩ ደባለክብኝ ብሎ ህጻኑን ኢየሱስ ክርስቶስን በጥፊ መታው ይህን ጊዜ ግን ግራ ጉንጭህን ለሚመታህ ቀኝህን ደግሞ አዙረ ስጠው ብሎ የሚያስተምር አምላክ ሆኖ ሳለ አዙሮ ግይ ጉንጩን ሲሰጠው አንመለከትም ከዛ ይልቅ መምህሩን ጠየቀው :: እንዲ ሲል መምህር ያጠፋሁብህ እንደሆነ አስተካክል ትለኛለ እንጂ ለምን ትመታኛለህ ??? አለው ። የተደባለቀውንም ጥቁርና ነጭ ቀለምም በተአምራት ለየ ብቻ ለይቶ ሰጠው:: እንደ ሰውነቱ አጠፋ እንደ አምላክነቱ ጥቁሩን ከነጭ ለይቶ ሰጠው :: ታዲያ ከዚህ የምንማረው ቀኝ ጉንጭህን ለሚመታ ግራህን ደግሞ አዙረ ስጠው የሚለውን ይዞ ሲጠፋጠፉሁ መዋል ፍጽም አግባብ አይደለም ሰማዕታትም አያሰኝም ከዛ ይልቅ ለምን ትመታኛለህ ማለቱና እራስን ማስከበሩ የተገባ ነው ። ዛሬም በልዮ ልዮ ዱላ የሚመቱን ቁጡ መመህራኖች በዝተውብናል ለምን ትመቱናላችሁ ብለን ልንጠይቅ ይገባል።። “ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፥ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው።” ሮሜ 8፥36 ::
ታድያ ምን እናድርግ?
#ስለ ቀናች ሃይማኖት #መጋደል አለብን::
ክርቲያኖች በሃይማኖታችን ጸንተን መሞት ብቻ ሳይሆን መኖርም ተፈቅዶልናል “ወዳጆች ሆይ፥ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።” ይሁዳ 1÷3
ማስታወሻ :- መጋደል ሲባል ቆሞ መገደል ማለት አይደለም ባንገል እንኳ እንዳንሞት እራሳችንን መከላከል መቻል ማለት ነው :: ልክ ድብድብ ስንል የሁለት ሰዎች ሱታፌ ያለበት ኩነት እንደሆነ ሁሉ መጋደልም እንዲሁ ማለት ነው አንዱ ወገን ብቻ የሚያጠቃበት ከሆነ ድብደባ እንጂ ድብድብ አያሰኘውም ::
እኛ ክርስቲያኖች ሙስሊሙ ያርደናል ፖለቲካው ያቃጥለናል ሰይጣን ይሸምቅብናል መለያየት ያተኩሰናል ጴንጤው ያሰናክለናል ነገር ግን ይህ የክርስቲያኖች ጠባይ ነው በመቱን ቁጥር እንደ ሚስማር እንጠብቃለን በገፉሁን ቁጥር እንደ ቅቤ ከፍ እንልና የራስ አክሊል እንሆናለን የሰማዕታት ደም ዘር ነውና ሊቀንሱን ሲያርዱን 30፣60፣100 ፍሬ ሆነን በዝተን እናፈራለን ።
#በጸሎት እንትጋ
ክርስቲያኖች በሃይማኖት ነቅ የሌለባቸው ጻድቃኖች(እውነተኞች) ናቸው ። በመሆኑም በእምነት ሆነው የሚጸልዮት ጸሎት ተሰሚነት አለው ጸሎት የክርስቲያኖች ዋነኛ መሳሪያ ነው::“እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ። ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።” ያዕቆብ 5፥16
#ስለ ሀገራችን ጸልዮ
#ሰለ ሃይማኖታችን ጸልዮ
#ስለ አንድነታችን ጸልዮ
“ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው።” ማቴ26፥41
“በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፤” ኤፌሶን 6፥18
#ቀርበን እንወቃት እንማራት
የማያውቁትሀገር አይናፍቅም ነውና ይበልጥ ተቆርቋሪዎቿ ለመሆን ከፈለግን ወደ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀርበን እንማር ታሪኳን እናጥና ያሳለፈችሁን የመከራ ዘመን እንዴት እንዳለፈችሁ መርምረን ለነገ ችግሯ መፍትኤ እናብጅላት::
" የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ። መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።ስለዚህ በክፉው ቀን ለመቃወም፥ ሁሉንም ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ። እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ታጥቃችሁ፥ የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፥ በሰላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ፤ በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤ የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ #እርሱም_የእግዚአብሔር ቃል ነው።" ኤፌ 6 ÷11-17 ይቆየን
ሐምሌ 26 ቀን ዕለተ እሁድ
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ ማርያም
@YEAWEDIMERITE
ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit