ዐውደ ምሕረት
3.67K subscribers
932 photos
24 videos
271 files
195 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#24ቱ_ካህናተ_ሰማይ_25 ሆኑ !
_______

አስቀድመው ቅዱሳን ሐዋርያት 12 ብቻ ነበሩ ከመካከላቸውም ይሁዳ ገንዘብ ወዶ ዘመድ ለምዶ አገልግሎቱን ትቶ ሄደ ሐዋርያትም ወንጌል በዓለም ሳይሰበክ ቢቀር አገልግሎታችን ተስተጎግሎ መቅረቱ አይደለ ብለው እግዚአብሔር ባወቀ ይሁዳ በተዋት አገልግሎት ፈንታ ሌላ ሰው እንዲሿምላቸው በርናባስንና ማትያስን አቀረቡ መንፈስ ቅዱስም ማቲያስን መርጦ ሰጣቸው:: የሚገርመው ነገር የእግዚአብሔር ድንቅ ስጦታ ነው በአንዱ ይሁዳ ፈንታ ሁለት ምትኮችን ሰጣቸው አንዱ ማቲያስ ሲሆን ሌላው እራሱ በቃሉ ሐዲስ ሐዋርያ ብሎ የሾመው ተክለ ሃይማኖት ነው ቅዱስ ጳውሎስን ከአሳዳጅነት ቅዱስ ጴጥሮስን ከዓሳ አጥማጅነት እደጠራቸው ሐዋርያትን በጠራበት አጠራሩ አባታችን ተክለ ሃይማኖትን እንሰሳ ከሚያድኑበት ("ድ")ጠብቆ ይነበብ) ጫካ ጠርቶ በወንጌል መረብነት ሰው የሚድኑ ("ድ")ላልቶ ይነበብ አዳኝ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጉ ሾማቸው የሐዋርያት ቁጥረም 12 ቢሆንም በሐዲሱ ኢትዮጵያዊ ሐዋርያ አማካኝነት ያለ ወትሮ 13 ሆነ ምነው መጻሕፍት 12ቱ ሐዋርያት አይደል የሚለው ቢሉ መጻሕፍት በቀረበው የመጥራትም ፀባይ አላቸው 12ቱን ሐዋርያት አስሩም አያለ እንደጠራቸው ማለት ነው ስለዚህ 12ሐዋርያት ስላለ 13ተኛ አይጨመርም አያሰኝም

#አባታችን ተክለ ሃይማኖት ቁጥራቸው ከሐዋርያት ወገን ብቻ ሳይሁን ከስማዕታትም ጋር ጭምር ነው ምነው ሰማዕታት ስለ ክርስቶስ ሲሉ ሥጋቸውን የቆረሱ ደማቸውን ለምስክርነት ያፈሰሱ እንደነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ያሉ ሰዎች አይደሉም እንዴ ቢሉ አባታችን ተክለ ሃይማኖት መከራን አብዝቶ በመቀሎል ከሰማዕቱ በምን ተለዮ?በዳሞቱ ንጉስ እጃቸው በሰይፍ ተቆረጠች እግዚአብሔር እንደ ቀድሞ ጤነኛ አደረገላቸውጉልያድን በሚያካክሉ በሞተሎሚ በወታደሮች በሽምግልና አቅማቸው ደም በአፍና በአፍንጫቸው እስኪተፉ ተደብድበዋል በንብ ቀፎ ተደርገው ወደ ገደል ተጥለዋል ከዚህ ሁሉ ስቃይና ደም መፍሰስ በኃላ እራሱ አልበቃ ብሏቸው ወደ አደባባይ ወጥቼ ስለ ስምህ መስክሬ እንደሰማዕታት ደሜን አፍስሼ ልሞት እፈልጋለው አሉ:: እግዚአብሔር ግን ከዚህ በላይ ሰማዕትነት አንደሌለ ሲነግረን እኔ ከአንተ ሰውነት በእመምህ ምክንያት የሚወጣውን ፈሳሽ እኔ እንደ ሰማዕታት ደም አቆጥርልሃለው ብሎ ዕረፍታቸውን በሰማዕታት ዕረፍት ቆጠረው ::
#አንዳንድ ሞኝ ሰዎች ይህን በማንበብ እንዴት የተክለ ሃይማኖት በእመም ከሰውነታቸው የወጣ ፈሳሽ(ተቅማጥ)እንዴት ከሰማዕታት ደም ጋር እኩል ይሆናል? ሲሉ ይሰማሉ ጌታችን መዳኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌሉ" ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል"ሲል ተደምጧል #ማቴ 25 ÷40 ታዲያ ለሰው ማድረግ ለእርሱ እንደማድረግ ተደርጎ ከተቆጠረ ወይም የአባታችን የሰውነት ( ፈሳሽ ተቅማጥ) እንዴት አንደ ሰማዕታት ደም መቆጠሩ ስህተት አይደለም እንደውም ይህ ነገር ስህተት ነው ከማለት ይልቅ የጌታችን ምሳሌ ስህተት ይመስላል ሰው ሲራብ ማብላት ሰው ሲጠማ ማጠጣት ሰው ሲታሰር ሄዶ መጠነቅ የማይራበው እግዚአብሔር ተርቦ እንደ ማብላት የማይጠማውን እግዚአብሔርን ተጠምቶ እንደ ማጠጣት የመይታሰረው እግዚአብሔርን ታስሮ እንደተጠየቀ አድርጉ መቁጠር አንዴት ይቻላል? ሌላውና ወሳኙ ነጥብ በህመም ከሰውነት የሚወጣ ፈሳሽ(ተቅማጥ) እና ደም ከሚያስከትሉት ችግር አንጻር ምንም ልዮነት የላቸውም በሳይንሱም ዓለም አገልግሎቱን ያልጨረሰ ፈሳሽ ከሰውነት ከወጣ በቶላ በሌላ ፈሳሽ ምግቦች እንዲተካ ይደረጋል ለምሳሌ" ሀተት "የተሰኘውን የጠቅማጥ በሽታ ብንወስድ ለሁለት ሳምንት እና ከዛ በላይ ለሆኑ ቀኞች ተተኪ ፈሳሽ ምግብ ሳንወስድ ዝም ብንለው ወደ ሞት ያደርሰናል ይህ ማለት ደም ሥር ተቆርጦ ብዙ ደም ከፈሰሰ በኃላ ምንም ተተኪ ፈሳሽ ሳይወስዱ እንደመቀመጥ እና እነደሚያስከትለው ችግር ሊቆጠር ይችላል:: ስለዚህ ሰማዕታት ደማቸውን አፈሰሱ ሲባል ለመኖር የሚያስችላቸውን ወሳኝ ነገር(ደም)ከሰውነታቸው ወጣ ማለት ነው አባታችን ተክለ ሃይማኖትም ልክ እንደ ደም ጥቅምነቱን ሳይሰጥ ከሰውነታቸው በመውጣቱ ደሙ ሳይፈስ ቀርቶ ቢሆን ኖሮ ሰማዕታት የክብርን አክሊል ወደ ሚቀዳጅባት ሞት እንደማይቀርቡ ሁሉ አባታችንም ለሞት ባልቀረቡ ነበር::

አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ቁጥራቸው ከሐዋርያት ወይም ከሰማዕታት ወገን ናቸው ተብሎ ብቻ አይታለፍም ከካህናተ ሰማይ ከሡራፌል ጋርም ይመደባሉ ለወትሮ ካህናተ ሰማይ ሡራፌል ቁጥራቸው 24ብቻ ነበሩ ኢትዮጵያዊው አባት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የኢትዮጵያ ሲሳይ ሐዲስ ሐዋርያ ሰማእት ወነብይ ወካህን በተወለዱ እና ባደጉ ጊዜ ግን 25ለመሆን ተገደዋል ::ኃዳር 24ቀን 24ቱ ካህናተ ሰማይ ሡራፌል እንደለመዱት ሥሉስ ቅዱስ ብለው መንበሩን አያጠኑ ሳለ ድንገት ቅዱስ ሚካኤል ከሰዎች ወገን የሆነ ሰው ሲሆን እንደ መላእክት ስድስት የፀጋ ክንፎች የተሰጡት ብርሃን ዘኢትዮጵያ የሆነውን አባታችን ተክለ ሃይማኖትን ይዞ አመጣው የወርቅ ማዕጥንትም ተሰጠው ከዙፋኑም ወዳጄ ተክለ ሃይማኖት ቁጥርህ ከንግዲህ ወዲህ ከ24ቱ ሰማያተ ካህናት ጋር ይሁን አለው:: 25ተኛ ካህንም ሆኖ የሥላሴን መንበር ሥሉስ ቅዱስ እያለ በወርቅ ማዕጥንት አጠነ: : ራዕ ዮሐ 4÷4 ገድለተክለ ሃይማኖት
*ይቆየን*****
#የአባታችን እረድኤትና ምልጃው አይለየን ለዘላለሙ አሜን!!!
#በድጋሚ የተለጠፈ
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ኅዳር 23ቀን 2012 ዓ,ም
Audio
Audio
ለማራዶና ሙት ዓመት የተጻፈ
#የእግዜር እጅ /The hand of God/

እግር ኳስ ከዓለማችን ስፖርቶች ሁሉ እጅግ ተወዳጅ የሆነ ስፖርት ነው። የስፖርት ዓይነቶች ብዙና አያሌ ቢሆኑም እንደ እግር ኳስ ስፖርት ግን የገነነ የለም ።

#የስፖርት ዜና እንይ ስንል እንኳ የእግር ኳስ ዘገባዎችን እንከታተል ማለታችን እንደሆነ ተደርጎ ብቻ ይታሰባል ። ይህም እግር ኳስ ሌሎች ስፖርቶች እንዳልተፈጠሩ አድርጎ በማስረሳት በብዝዎቻችን ልቡናና አእምሮ ላይ እንደነገሰ ያመላክታል።

እግር ኳስ ተወዳጅ ከመሆኑ አልፎ ተወዳጂና ታዋቂ ያደረጋቸው ሰዎችም አያሌ ናቸው። ከነዚህ ሰዎች መካከል አርጄንቲናዊው ማራዶና አንዱ ነው።

#እንደ_ግሪጎሪያን የዘመን ቀመር ጥቅምት 30 ቀን 1960 ዓ.ም ከዛሬ 60ዓመት በፊት ላኑስ ፣ ቦነስ አይረስ ፣ አርጀንቲና ከተማ ውስጥ የተወለደው ማራዶና ወይም በሙሉ ስሙ (Diego Armando Maradona) /ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና/ ዓለም የምታውቀው በእግር ኳስ ነው።

ይልቁኑ የእግዚአብሔር እጅ /Hand of God/ በመባል በምትታወቀው ግቡ በስፖርቱ ወዳጆች ልብ ውስጥ አይረሴ አድርጋ አትማዋለች ።

#ዲያጎ አርማዶ ማራዶና በ1986 በሜክሲኮ የተካሄደውን ውድድርን በበላይነት መቆጣጠር ችሎ ነበር፡፡ እንግሊዝን በተሸነፈበት የ1-1 የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ በዓለም ዋንጫው ውስጥ በጣም የማይረሱ ሁለት ግቦችን አስቆጠረ።

ከነዚህም አንዷ በጭንቅላቱ መግጨት እንደማይሆንለት ሲረዳ እስከሚችለው ከዘለለ በኋላ በቴክኒክ እጁን በመጠቀም ኳሷን ወደ ግብነት ቀየራት ዳኛው በጭንቅላቱን ገጭቶ እንዳገባው አስበው አጸደቁለት። በኃላ ግን በጭንቅላት ሳይሆን በእጅ እንደተቆጠረች የዓለም ሕዝብ ዐወቀ ግቧም “የእግዚአብሔር እጅ ግብ” በመባል የምትታወስ ግብ ሆነችለች፡፡ ዛሬ ድረስ ማራዶና ሲነሳ ይህች ግብ አብራው ትነሳለች።

#በሁላችንም የሕይወት እግር ኳስ ውስጥ አናስተውላትም እንጂ የእግዚአብሔር እጅ አለች ከጅምሩ አጥንት ሰክቶ ጅማት ወጥሮ ደም አሰራጭቶ ያበጃጀን ይህው የእግዚአብሔር እጅ ነው በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ የእግዚአብሔር እጅ የሌለችበት ጊዜና ቦታ የለም "ወደ ሰማይ ብወጣ፥ አንተ በዚያ ነህ፤ ወደ ሲኦልም ብወርድ፥ በዚያ አለህ። እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ፥ እስከ ባሕር መጨረሻም ብበርር፥ በዚያ #እጅህ_ትመራኛለች_ቀኝህም_ትይዘኛለች " እንዲል ነቢዩ መዝ138(139)÷8-10

እነ_ቫር እና ጎል ላይን ቴክኖሎጂ ሳይመጡ በፊት እግር ኳስ ከነ ወዙ መቆየት ችሎ ነበር አሁን አሁን ግን ጨዋታ ሁሉ ቆሞ በቴክኖሎጂ እገዛ ፍርድ የሚቀለበስበት ሁኔታ ተፈጥሯል ይህም የተወዳጁን የእግር ኳስ እስፖርት አዝናኝ ኩነቶች በእጅጉ አደብዝዘውታል ።

#በእግር ኳስ ጨዋታ ውስጥ ከበረኛና የእጅ ከሚወረውር ተጫዋች በቀር ኳስን ሆን ብሎ በእጅ መንካት አይፈቀድም ወይም እጅን ወደ ኳስ ማምጣትና መንኳት ክልክል ነው። ካልሆነ ግን "ማኖ" ብሎም የቅጣት ምቶችን ያስከትላል ከፍ ሲልም በቢጫና በቀይ ካርዶች ከጨዋታው ሊያስወጣ ይችላል። ታዲያ ይህች የማራዶና ግብ እንዴት ከግብ ተቆጠረች? ብለክ ታስብ ይሆናል መልሱ ቀላል ነው "የእግዚአብሔር እጅ" ስለሆነች ነው። የእግዚአብሔር እጅ ማኖ የላትም

ምድራዊ ሕግ በእጅህ እዳትነካ ቢያስጠነቅቅህም የእግዚአብሔር እጅ ካንተ ጋር ካለች እግር ኳሱን ቅርጫት ኳስ ብታደርገው እንኳ ዓላማህ ግብን ይመታል ። ባርም ጎል ላይን ቴክኖሎጂም አይቃወሙህም።

#ይህ_ሲባል ግን ወዳጄ የእግዚአብሔር እጅ አጭበርባሪውንና አታላዮን ትወዳለች ከእርሱ ጋርም ታብራለች ማለት አይደለም። የቤቱ ሁለተኛ ልጅ ብትሆንና ብኩርናን አጥብቀህ ብትሻት መሻትህን አውቆ እንደ ያዕቆብ ፊተኛ ያለው ቀዳማዊ ፣ተከታይ የሆነ መሪ ፣ታላቅ ያለው በኩር ያደርግሃል ማለቴ ነው። እንደ ዔሳው ካቃለልካት፣ በኩርናህን ካልጠበካት ፣ በምስር ወጥም ከሸጥካት ግን የመጀመሪያው መጨረሻ አንተ ትሆናለህ በእግር ብታገባው እንኳን ግብ የተሻረ ይሆናል ፊተኞች ዋለኞች ዋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ የሚለው ቃል የሚከወነው በሰው መሻትና በእግዚአብሔር እጅ እንደሆነ ዕወቅ። #ዘፍ25÷34

#የእግዚአብሔር እጅ ተንጠራርተው ከግባቸው ላልደረሱ ብቻ ትቀጠላለች እንጂ ባሉበት ቆመው ያለ ጥረት ተአምር ለሚጠብቁት አትቀጠልም ሞክረህ ባቃተ ጊዜ ብቻ እርዳታ ጠይቅ አቤቱ ከአርያም ክድህን ስደድልኝ በለው።

በባለጋራዬ በሥጋ ፍቃድ፣በሰይጣን ፈተና ፣ በዓለም መውጊ ተውግቼ መሸነፍ አልፈልግም አድነኝ ብለ ጥራው እነሆ፥ የእግዚአብሔር እጅ ፈጥና ታድንለች በጠላቶችህ ላይም ድልን ታቀዳጅሃለች። “ #እነሆ_የእግዚአብሔር_እጅ ከማዳን አላጠረችም ፤ ጆሮውም ከመስማት አልደነቈረችም "
#ኢሳ 59፥1

#እኔም_እንደ_ፔሌ አንድ ቀን በሰማይ ኳስ እንገፋለን ባልለውም ይህን የዓለማችን የእግር ኳስ ፈርጥ ግን ነብስህን ይማራት ሳልል ማለፍ አልፈልግም 🙏!

#Thank_you Armando

ኃ/ማርያም
አ.አ ኢትዮጵያ
ጥር 3/2013 ዓ.ም
Forwarded from Biniam kalayu
Audio
Forwarded from Biniam kalayu
Audio
#አብሳሪው_መላእክ_ቅዱስ_ገብርኤል ሆይ እውነተኛ የሰላም ብሥራት ለኢትዮጵያም አብስራት !
" #ደስታ_ተክለ_ሃይማኖት_ተወለደ"

#የሚገቡት
እንኳን ማርያም ማረችሽ ፣
አሜን!
እንኳን ማርያም ሁለት አረገችሽ
አሜን!
#የሚወጡት
ማርያም ጭንሽን ታሙቀው
አሜን!
ማርያም በሽልም ታውጣሽ.......ይሏታል
የእመጫቷ መልስ አሜን !አሜን! የሚል ብቻ ነው። ይህ የእግዚእኃረያ ቤት ነው። ባሏ ፀጋ ዘአብ ደስታውን መቋቋም አቅቶታል ቤቷ በወዳጆቻቸው እና በጠያቂዎቻቸው እንዲሁም ባለ መውለዳቸው እንደ ኃጢያተኛ ቆጥሮ ይጠቋቆሙባቸው በነበሩ ሰዎች ተጨናንቃለች መካን ሚስቱ ወንድ ልጅን ወልዳለችና ። ለሁሉም እንደ ማዕረጋቸው ምሳ አደረጉላቸው ማጋረጃ ገልጠው እናቲቱንና ልጇን ቅቤ እስኪቀቡ የቸኮሉ ሳይኖሩ አይቀሩም ሌላው ግን ስለ አወላለዷ ለመረዳት ሰሀናቸውን ይዘው የወላዲቱ አልጋ አጠገብ ጠጋ ብለው የተቀመጡም አልጠፋም ።

#እርሷም_የእግዚአብሔርን ቸርነት የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እየመሰከረች ከሞተለሚ ምርኮ እንዴት ባለ ተአምር እደዳነች እያወራች ከባሏ ከፀጋ ዘአብም ጋርም ወንድ ልጅ ስለ መውለዷ አስቀድመው ዕራይን እንዳዮ እየነገረቻቸው ቀኑን በደስታ አሳለፈች ደስታ የሆነ ልጅ ወልዳለችና ።

*ስሙንስ ማን አላችሁት ?
ፍስሐ ጽዮን ( የጽዮን ደስታዋ) ብለነዋል ። ነገር ግን መላእኩ እንደነገረን ስሙ ሌላ ነው ከእናንተም የተሰወረ በልበ ሥላሴ የተጻፈ አዲስ ስም ይወጣለታል ብሎናል። "ተክለ ሃይማኖት"! ሕጻናት እንደሚያለቅሱም አያለቅስም ነበር "ቅኖች ሰዎች ሁል ጊዜ ደስ ይላቸዋል" እንደሚል

"ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን ለእራስህ አዘጋጀህ " አንደተባለም ሕጻኑ ፍስሐ ጽዮን በተወለደ ገና በሦስተኛው ቀን ከእናቱ እቅፍ ወርዶ "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ ሥላሴን በአንድነት በሦስትነት አመስግነ:: መዝ 9÷2

#ልጆች_የእግዚአብሔር ስጦታዎች ናቸው የእግዚአብሔር ስጦታ ሁሉ ደግሞ ደስ ያሰኛል ። ይልቁኑ እግዚአብሔር በእነርሱ አድሮ ድንቅ ሥራውን ይሰራባቸው ዘንድ ያዘጋጃቸው የቅዱሳን ሰዎች ልደታቸው ብቻ ሳይሆን እነርሱ እራሳቸው ደስታ ናቸው :: " በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል ተድላና ደስታም ይሆንልሃል" ዮሐ1፥14 ተብሎ እንደተጻፈ እውነት ነው በመወለዱ ብዙዎች ደስ ብሎናል በሉቃስ ወንጌል ላይ መላእኩ ቅዱስ ገብርኤል በመጥምቀ መለኮት በቅዱስ ዮሐንስ መወለድ ብዙዎች ደስ እንደሚሰኙ አስረግጦ ነግሮናል።

እነሆ ዛሬ ደግሞ እንደ ዮሐንስ በድንግልና የኖረ እንደ መጥምቁ ካህን ያውም ሰማያዊ የሆነ እንደ አዋጅ ነጋሪው በምድረ ኢትየጵያን ሁሉ እየዞረ ወንጌልን የሰበከ ለእናትና ለአባቱ እንዲሁም ለብዝዎቻችን የደስታ ምንጭ የሆነ የጽዮን ደስታዋ የተባለ ፍስሐ ጽዮን ተወለደ እነሆ እኛም እንደ ተስፋው ቃል ዳግማዊው ዮሐንስ ተወልዶልናልና ደስ አለን::
#መፍቀሬ ጥበብ ቅዱስ ሰለሞን" ጻድቃን በበዙ ቁጥር ሕዝብ ደስ ይለዋል" እንዳለ አባታችን ተክለ ሃይማኖት በተወለዱ ሰዓት ክርስቲያኖች ደስ ብሏቸዋል ምክንያቱም ጻድቁ ሕሙማነ ነፍስን በትምህርታቸው ሕሙማነ ሥጋን በተአምራታቸው እያዳኑና እየፈወሱ ለሕዝብ ደስታ ምንጭ ሆነዋል ያን ጊዜ ብቻም ሳይሆን ዛሬም በአፀደ ነፍስ ሳሉ ለኛ ለክርስቲያኖች የደስታችን ምንጭ ናቸው " የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለችና " ስለኛ የጽድቅ ሕይወት የሰላም እጦት የሃይማኖት ጉለት የምግባር ዝቅጠት ዕለት ዕለት ወደ ፈጣሪ እየጸለዮ ያማልዱናልና ነው #ያዕቆ 5÷16

በጻድቃን መወለድ ሕዝብ ደስ የሚለው በተወለዱበት ዘመን እና ወር ብቻ አይደለም አንዴ ጻድቃን ከተወለዱ በኃላ ሕዝብ ለዘለአለሙ ደስ ይለዋል ጻድቃን በአፀደ ሥጋም በአፀደ ነፍስም በምልጃቸው ደስ ያሰኛሉና ..... .. ልክ እንደዛሬው......

" #እኔ ግን ለዘለዓለሙ ደስ ይለኛል
ለያዕቆብ( #ለተክለ_ሃይማኖት )
አምላክም ዝማሬን አቀርባለው" #መዝ76÷9
...........ይቆየን........

የጻድቁ አባታችን የተክለ ሃይማኖት እረድኤትና በረከት በሀገራችን ኢትዮጵያ ጸንታ ትኑር
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ታኅሳስ 24/2014 ዓ.ም
#አዲስ_መልአክ_ተክለ_ኤል
________
ተፈጥሮ ከመላእክት ወገን ያልሆነ ሰው ሆኖ ሳለ ነገር ግን በሃይማኖቱ ጽናት በምግባሩ ቅንሐት እና በተጋድሎዎ ብዛት ምድራዊ ሲሆን ሰማያዊ አዳማዊ ሲሆን መላእካዊ ለመሆን የበቃ ሐዲስ መላእክ ነው :: ተክለ ኤል

ቅዱሳን መላእክት በዘር የተገኙ አይደሉም ተክለ ኤል ( #ተክለ_ሃይማኖት ) ግን ከሕግ ዘር የተገኘ ሰው የሆነ አዲስ መላእክ ነው ::

#ተክል › ማለት ፍሬያማ ዕንጨት፣ ዛፍ፣ ቅመም፣ ቅጠላ ቅጠል፣፣ የሚሸተት፣ቢበሉት ጥጋብ ፣ቢያርፉበት ጥላ የሚሆን ገነታዊ ዕፅ፣ እንዲሁም ሕግ ሥርዓት ማለት ነው /ማቴ.፲፭፥፲፫/፡፡

" #ኤል " ማለት ደግሞ እግዚአብሔር ማለት ነው :: ስመ መላእክት ስመ እግዚአብሔርን ያዘለ በመሆኑ የሁሉም ቅዱሳን መላእክ ስም "ኤል" የሚል መቀጽል አለው #ለምሳሌ :-ሚካ-ኤል ፣ ገብር-ኤል ፣ ዑራ -ኤል፣ ወዘተ .... ስለዚህ ተክለ ኤል ስንልም #የእግዚአብሔር _ተክል ማለታችን ነው :: ታላቁ ሊቅ ቅዱስ #ባስልዮስ ዘ ቄሳሪያ እኔስ #እግዚአብሔር ባልኩ ጊዜ #አብ_ወልድ_መንፈስ_ቅዱስ ማለቴ ነው ብሎ እንደተናገረ እኛም እግዚአብሔር ስንል አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለታችንነውና #ተክለ_ኤል ስንለውም የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተክል ማለታችን ጭምር ነው::

#ቦታው በሸዋ ክፍለ ሀገር ዛሬ ኢቲሳ በመባል በሚታወቀው ከከሰም ጅረት አካባቢ ባለ ቦታ በጥንቱ ፈጠጋር ቡልጋ በደብረ ጽላልሽ አውራጃ ዞረሬ በተባለው ሥፍራ ነው ። በዚሁ ሥፍራ (ዘርዐ ዮሐንስ) ፀጋ ዘአብ የሚባል የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህን የነበረ ጻድቅ ሰው ነበር "ጸጋ ዘአብ " ማለት የአብ ሥጦታ ማለት ነው ካህኑ ጸጋ ዘአብ በሃገሩ ደጋግ ከሆኑ ሰዎች ወገን ሣራ የምትባል ሴት አገባ ።

ሁለቱም ፈሪያ እግዚአብሔር ያደረባቸው በጎ ሥራን የሚሠሩ ሰዎች ነበሩ የፀጋ ዘአብ ሚስት ሣራ ሃይማኖት ከምግባር መልክና ደም ግባት ከሙያ ጋር አሟልቷ የሰጣት ሴት ነበረች ። አማቷ የፀጋ ዘአብ አባት " ወረደ ምሕረት " የሥራዋን ደግነት አይተው " እግዚኀረያ " ብለው ስም አወጡላት ጌታ የመረጣት ማለታቸው ነው።

#በሊቀ_መላእክት_በቅዱስ_ሚካኤል አብሳሪነት ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ተወለዱ ወላጆቻቸውም ፍስሐ ፂዮን ።(የጽዮን ደስታዋ)ብለው ሰየሟቸው፡፡ ጻድቁ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹ አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› ማለትም ‹‹አንዱ አብ ቅዱስ ነው አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው›› በማለት የፈጠራቸውን አምላክ አመስግነዋል። ይህን ጊዜ እናታቸው እግዚ ኀረያም በመገረም ሆና " ይህ ሥራ የአባት ነው ላንተ የሚገባህ ጡት መጥባት ነው" ብላ ጡቷን አጎረሰችሁ ፡፡

#ቅዱሳን_መላእክት ቀን ከሌት #ቅዱስ_ቅዱስ_ቅዱስ እያሉ ያመሰግናሉ ኢሳ 6፥÷6 ይህም የህጻኑ ሁኔታ መላእካዊ ግብሩን ገና በህጻንነት የገለጠ ሁኔታ ነበር። ካህኑ ፀጋ ዘአብ የወቅቱን የቤተ ክርሰቲያን አገልግሎታቸውን ጨርሰው ወደ ቤታቸው ሲገቡ ሚስታቸው እግዚ ኀረያ በመገረም ሆና የሦስት ቀን ልጃቸው ፍስሐ ፂዮን እንዴት ባለ ምሥጋና ፈጣሪያቸውን እንዳመሰገነ ነገረቻቸው ጸጋ ዘአብም ህጻኑን ተቀብለው ታቅፈው እየሳሙ ልጄ ሺህ ዘመን ኑርልኝ እንዲ እያልክ በቤተ መቅደስ ስትቀድስ አይህ ዘንድ እመኛለው አሉ።
‹‹ #ተክለ_ሃይማኖት ›› ብሎ #የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ፍስሐ ፂዮን የሚለውን ስሙን በፈጣሪው ትዛዝ መሠረት ጠራቸው፡፡ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው ዲቊናን፤ በ22 ዓመታቸው ደግሞ ቅስናን ከግብፃዊው ጳጳስ ከአባ ጌርሎስ ወይም (አባ ቄርሎስ) ዘንድ ተቀብለዋል፡፡

ሐዋርያዊ ተግባርንም በከተታ እና በፈጠጋር (በጽላልሽና በአካባቢዋ፣በዳሞት በምድረ ወላይታና አካባቢው ፣በአምሓራና በሸዋ በሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ፣ በኣድያማተ ትግራይ፣በገዳመ ዋሊ (ዋልድባ) ፣በገነተ ማርያም ላስታ በደብረ ዘመዶ ማርያም ገዳም በዚያው በላስታ፣ በኤርትራ ገዳማት ፣በደብረ ዳሞ አቡነ አረጋዊ ገዳም ወዘተ በአገሪቱ ወንጌል ባልተዳረሰበት ቦታ ሁሉ እየተዘዋወሩ ኢትዮጵያ አንዲት የሐዋርያት ወንጌል ሰፍተዋታል ።
#ጻድቁ_አባታችን ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣ እንደ ገበሬ ታጥቀው፣ ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በብሕትውና በመኖራቸው፤ እርሳቸው በአሚነ ሥላሴ ጸንተው ሌሎችንም እንዲጸኑና እንዲያምኑ በማድረጋቸው፤ እንደዚሁም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ በመስበክ በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ሰባኬ ወንጌል በመኾናቸው ‹‹ #ተክለ_ሃይማኖት ›› ተብለው ይጠራሉ::

#በየ_ደረሱበትም ከሥራው ጽናት ከተአምራቱ ብዛት የተነሳ አንተ ሰውነህን ወይስ መላእክ ነህ ንገረን ይሉት ነበር በዚህም በደብረ ዳሞት አቡነ አረጋዊ ገዳም 10 ዓመት ከቆዮ በኃላ ተሰናብቷቸው ሊሄድ ተነሳ ሁሉም ከፍቅሩ ጽናት የተነሳ አለቀሱለት አበምኔቱም ይህን ሰው ኃጢያቴ አባሮታልና ወየውልኝ ብሎ መነኮሳቱን ሰብስቦ ሊሸኙት ተነሱ ከገዳሞም ያለ እረጅም ገመድ (ጠፈር) መውረድም ሆነ መውጣት አይቻልም ነበርና የመውረጃውን ገመድ (ጠፍር) ይዞ ይወርድ ዘንድ ጀመረ ጥንተ ጠላት ዲያቢሎስ ገመዱን ከካስማው ላይ ቆረጠው አባታችንም ይህን አስደንጋጭ ክስሀት ተከትሎ የተሰጣቸው የፀጋ ክንፍ በገዐድ ተገለጠ አበ ምኔቱና መነኮሳቱም ከገዳሙ አፈፍ ሆነው የሚሆነውን ያዮ ነበር ጻድቁም እንደ ሰማያዊ መላእክ በክንፉቸው በረው በደህና ከመሬት ደረሱ መነኮሳቱም መንክር እግዚአብሔር በላዕለ ቅዱሳኒሁ ብለው አደነቁ::
ከዚህም ባለፈ ህዳር 24ቀን መላእኩ ከምድራዊ ቦታቸው ነጥቆ ወስዶ ከሱራፌል ጋር ቀላቀላቸው በልጅነት አንደበታቸው አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ብለው ያመሠገኑት አግአስተ ዓለም ቅድስት ሥላሴን ዛሬ ደግሞ በዙፋኑ ላይ እናዳለ እያዮት በከንፈሮቻቸው ሰለሱት ቀደሱት በወርቅ ማዕጥንትም ዙፋኑን አጠኑ ።ወደ ቀደመም ኑሯቸው መላኩ መለሳቸውና ተጋድሏቸውን ቀጠሉ።

#በገዳመ አስቄጥስ ግብጽ እና ከኢየሩሳሌም።ጉብኝት በኃላ እየዞሩ ወንጌልን ለማስተማር ባይቻላቸው ስለዚህ በአንድ ቦታ መቆምን መረጡ ከፊት ከኃላ ከግራ ከቀኝ የሚያነቃ የሶር ሶማያ ስለው በመትከል በደብረ አስቦ በደብረ አስቦ ዋሻ ከዘረጉ ሳያጥፉ ከቆሙ ሳይቀመጡ ለ22 ዓመታት በጸሎት ጸኑ ጥር 4 ቀን 12 88ዓ.ም በ92 ዓመት ሲሆናቸው አንዲቱ የእግራቸው አገዳ ከመቆም ብዛት ተሰብራ ወደቀች ጸሎታቸውንም ሳያቆርጡ በአንድ እግራቸው 7 ዓመት አክለው በጸሎት ተጎ በድምሩም 29 ዓመት በጸሎት ተጋደሉ :: ከፈጣሪ ዘንድም ብዙ ጸጋና ቃል ኪዳን ከተቀበሉ በኃላ በ99ዓመት ከ10ወር ከ10ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በክብር አርፈዋል:: እንደ ሰው በምድር ተወልደው እንደ መላክት የኖሩ አዲስ መላክ ያልናቸውም ለዚሁ ነው።

የጻድቁ አባት የአቡነ #ተክለ_ሃይማኖት እረድኤት በረከታቸው በአማላጅነታቸው የምትገኝ ጸጋ ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትኑር .....አሜን!
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥቅምት 2013ዓ.ም