#የፍቅር_ሕብረት
እንኳን ሊፋቀሩ በእህልና ውኃ
የሚገለማመጡ ሲልፉ በጉዳና
ጠላቶች ነበሩ ሳምርና ይሁዳ
#ዛሬ ግን በአንድነት ይህው ተባበሩ
በአንድ አካል በአንድ አምሳል በፍቅር ከበሩ
ዲያቆኑ በጥበብ በአራራይ ዜማ
አራርቶ ቢነግራት ውኃ እንደተጠማ
ሳምር ተሸነፈች በድምጹ ተደማ
ትቀዳለት ጀመር ገንቦዋን አዝማ
ከክርስቶስ ቀድሞ ውኃ ካሰጠማ
በል ንገረኝማ
ማነው ያስተማረ እንዲህ ያለ ዜማ?
#ደሞ ወንድም ጋሼ
የአይሁድ መምህራቸው አንተ ሆነ ሳለህ
እንዴት ከሳምር ሴት ውኃ ትጠጣለህ ? ብለው ቢጠይቁህ
ክርስቶ ተጠመቶ ውኃ አጠጪኝ ያለው
ሄኖክ ሰብኮ ደክሞ እንዲጎነጭ ነው
ብለህ መልሳቸው
ፍቅር ድንበር አልባ ነው እኮ በላቸው
#ተክለ ኤል ኃ /ማርያም
ሰኔ 04/2014 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጵያ
እንኳን ሊፋቀሩ በእህልና ውኃ
የሚገለማመጡ ሲልፉ በጉዳና
ጠላቶች ነበሩ ሳምርና ይሁዳ
#ዛሬ ግን በአንድነት ይህው ተባበሩ
በአንድ አካል በአንድ አምሳል በፍቅር ከበሩ
ዲያቆኑ በጥበብ በአራራይ ዜማ
አራርቶ ቢነግራት ውኃ እንደተጠማ
ሳምር ተሸነፈች በድምጹ ተደማ
ትቀዳለት ጀመር ገንቦዋን አዝማ
ከክርስቶስ ቀድሞ ውኃ ካሰጠማ
በል ንገረኝማ
ማነው ያስተማረ እንዲህ ያለ ዜማ?
#ደሞ ወንድም ጋሼ
የአይሁድ መምህራቸው አንተ ሆነ ሳለህ
እንዴት ከሳምር ሴት ውኃ ትጠጣለህ ? ብለው ቢጠይቁህ
ክርስቶ ተጠመቶ ውኃ አጠጪኝ ያለው
ሄኖክ ሰብኮ ደክሞ እንዲጎነጭ ነው
ብለህ መልሳቸው
ፍቅር ድንበር አልባ ነው እኮ በላቸው
#ተክለ ኤል ኃ /ማርያም
ሰኔ 04/2014 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጵያ
ዐውደ ምሕረት
Photo
#መንፈስ_ቅዱስ ወረደ ላይለ ሐዋርያት
ተመሲሎ(5) በነደ እሳት
#መንፈስ_ቅዱስ ወረደ በሐዋርያት ላይ
ተመስሎ (5) በሚነድ እሳት
"ይህ ቀን #የቤተ_ክርስቲያን_የልደት ቀን ነው"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
ቤተ ክርስቲያ ሆይ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅጸነ ሐዋርያት እንኳን በዛሬዋ ዕለት ተወለድሽልን👏
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሰኔ05/2014 ዓ.ምአ
አ.አ ኢትዮጵያ
ተመሲሎ(5) በነደ እሳት
#መንፈስ_ቅዱስ ወረደ በሐዋርያት ላይ
ተመስሎ (5) በሚነድ እሳት
"ይህ ቀን #የቤተ_ክርስቲያን_የልደት ቀን ነው"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
ቤተ ክርስቲያ ሆይ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅጸነ ሐዋርያት እንኳን በዛሬዋ ዕለት ተወለድሽልን👏
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሰኔ05/2014 ዓ.ምአ
አ.አ ኢትዮጵያ
ገቢው ሙሉ በሙሉ ለአ.አ ደብረ አሚን #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ማሳደሻነት የሚውል!
20220615_112539.aac
24.8 MB
#በመምህር ኢዮብ ክንፈ ሊደመጥ የሚገባው ጥዑም ወቅታዊ ትምህርት እነሆ
ይድረስ ለብዙ አፎምያዎች
ይድረስ ለብዙ ባሕራኖች
የአፎምያ ጥያቄ የባሕራን መልስ
#ቅዱስ_ሚካኤል
_________
እርግብ የምታገባው አንድ ብቻ ነው። ቢሞት እንኳን ሌላ መጥቶ እንዳይተናኮላት ምላሷን ትሰነጥቃለች። ድንገት ቢመጣባት በደንብ መጮህ እንድትችል እና ሌሎች መጥተው ደርሰውላት እንዲያባርሩላት ነው። ቅድስት አፎምያም እንደ እርግ የምትኖር ደገኛ ሴት ነበረች።
የኬልቅያ መስፍን የነበረው የምትወደው ባሏ አስተራኒቆስ በሞት ከተለያት በኋላ በዕውቅ አስሎ የሰጣትን የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ይዛ በጾም በጸሎት ተስና ስትኖር ጸላዬ ሰናያት የመልካም ነገሮች ሁሉ ጠላት የሆነ ሰይጣን ዲያቢሎስ ደግ መነኩሴ መስሎ መቶ ጾም ጸሎት እንድትተው ሌላ ባል አግብታ ተድላ ደስታ እንድታደርግ መከራት እርሷ ግን አባ አለባበሶት ደግ ነበር ንግግሮት ግን የከፋ ነው። ጾም ፣ጸሎት ና ምጽዋት ደገኛ ሥርዓት አይደሉምን? ስለምንስ ዳግመኛ እንዳገባ ይመክሩኛል በሉ ከኔ ወግዱልኝ ብላ አሳፍረችው። ይህን ግዜ የደበቀውን ሰይጣናዊ ግብር ገልጦ ቆቡን ጥሎ ከቁራ ሰባት ጅ ጠቆረ ሰኔ አሥራሁለት ቀን ተመልሼ እመጣለሁ አጠፋሻለሁም ብሎ ዝቶባት እንደ ጢስ ተኞ እንደ ትብያ ተኖ ጠፍቶ ሄደ ።
ሰይጣን ዲያቢሎስ እንዳለሁም ግብሩን ለውጦ በሰኔ አሥራ ሁለት ቀንም የመላእከት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን መስሎ ባማረና በተዋበ ልብስ ወደ ቤቷ መጥቶ ተገለጠላት “ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና።” ተብሎ እንደተጻፈ 2ኛ ቆሮ 11፥14
ቤቴን በብርሃንህ የሞላህ አንተ ማነህ ? አለችሁ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነኝ ይህ ከብርሃኔ ተረጂ አላት ቆየኝ መጣው ብላ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጂ የነበረው ባሏ አስተራኒቆስ አስሎ ነሰጣትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕለ አድህኖ ይዛ መጣች ። እያመሳሰለችሽ ንጉሥ ለጭፍሮቹ መታወቂያ ማኅተቡን አትሞ አስይዞ ይልካቸዋል የእግዚአብሔር መላእክ ቅዱስ ሚካኤል ከሆንክ ማዕተመ መስቀልህ የንጉሥህ መታወቂያ በትረ መስቀልህ የታለ ?አለችሁ። እርሱም ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና እኛ በእግዚአብሔር ፊት የምንቆም መላእክት መስቀል መያዝ ለምናችን ጨርሶ አያስፈልገንም አላት ይህን ጊዜ አንተማ መላእኩ ቅዱስ ሚካኤል አይደለህም አላምንህም አለችሁ ያን ጊዜ እንዳ ወቀችበት ሲረዳ ግብሩ ቀይሮ በብርሃን የመላው ቤቷን በጽልመት መላው ቀንዱ በቀለ ፣ጥፍሩ እረዘረዘ፣ ዐይኑ ፈጠጠ ፣ጥርሱ ገጠጠ አንቺንስ ካላጠፋሁ ሠላሜን አላገኝም ብሎ ተወርውሮም አንቆ ያዛት ቅድስት እናት አፎምያም እውነተኛው ታላቁ መላእክ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እርዳኝ ብላ በጣር ውስጥ ሆና ተጣራች እውነተኛው የእግዚአብሔር መላእክም ከዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጣና ዲያቢሎስን ረግጦ ያስጨንቀው ገባ ሰይጣንም ሚካኤል ሆይ ጊዜዬ ሳይደርስ እንዳታጠፋኝ በፈጣሪህ እለምንሃለው እያለ ጮኸ ቅዱስ ሚካኤልም ለቀቀው በኖ ተኖ ጠፋ ቅድስት እናት አፎምያንንም ያረጋጋት ጀመር ። “ #የእግዚአብሔር_መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” እዳለ መጻሕፍ #መዝ (33) 34፥7
*አንባቢ ሆይ አንተስ በክርስቶስ ክርስቲያን ነኝ ትላለህንን እንግዲያውስ መስቀልህ የታል?
*አንባቢት ሆይ የንጉሥሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ትያለሽን? መልካም ትያለሽ ግን የንጉሡ ደመ ማዕተብ በትረ መስቀልሽ ከወዴት አለ? የአፎምያ ጥያቄ ይህ ነበር መስቀልህ የታለህ? ለአፎምያ ትክለኛ ጥያቄ መልስ የሆናት እውነተኛው ቅዱስ ሚካዬል በትረ መስቀሉን ጨብጦ ይዞ በመታየት ነው።ወዳጄ የድልህ ዐርማ የሆነውም " ሁልጊዜ በልብህ አኑረው፥ በአንገትህም እሰረው። ስትሄድም ይመራሃል፤ ስትተኛ ይጠብቅሃል፤ ስትነሣ ያነጋግርሃል። " #ምሳ 6÷21-22 የደሃ አደጊቱ ልጅ ባሕራንም የሞት ደብዳቤውን ተቀብሎ የደስታ የፍስሐ የሰርግ ደብዳቤ አድርጎ የመለሰለት የደስታ ሁሉ መልስ ቅዱስ ሚካኤል በዚህች ዕለት በነገዱ ሁሉ ላይ የተሾመበት የሹመቱ በዓል ነው!
መንፈስ ቅዱስ ያወቀውን ሰይጣን የሸመቀው ከጠላት የተንኮል እንቆቅልሽ ሁሉ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የደስታ መልስ ይሁንልን!
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
ሰኔ ፲፪ ቀን /፳፻፲፫ ዓ.ም
ይድረስ ለብዙ ባሕራኖች
የአፎምያ ጥያቄ የባሕራን መልስ
#ቅዱስ_ሚካኤል
_________
እርግብ የምታገባው አንድ ብቻ ነው። ቢሞት እንኳን ሌላ መጥቶ እንዳይተናኮላት ምላሷን ትሰነጥቃለች። ድንገት ቢመጣባት በደንብ መጮህ እንድትችል እና ሌሎች መጥተው ደርሰውላት እንዲያባርሩላት ነው። ቅድስት አፎምያም እንደ እርግ የምትኖር ደገኛ ሴት ነበረች።
የኬልቅያ መስፍን የነበረው የምትወደው ባሏ አስተራኒቆስ በሞት ከተለያት በኋላ በዕውቅ አስሎ የሰጣትን የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ይዛ በጾም በጸሎት ተስና ስትኖር ጸላዬ ሰናያት የመልካም ነገሮች ሁሉ ጠላት የሆነ ሰይጣን ዲያቢሎስ ደግ መነኩሴ መስሎ መቶ ጾም ጸሎት እንድትተው ሌላ ባል አግብታ ተድላ ደስታ እንድታደርግ መከራት እርሷ ግን አባ አለባበሶት ደግ ነበር ንግግሮት ግን የከፋ ነው። ጾም ፣ጸሎት ና ምጽዋት ደገኛ ሥርዓት አይደሉምን? ስለምንስ ዳግመኛ እንዳገባ ይመክሩኛል በሉ ከኔ ወግዱልኝ ብላ አሳፍረችው። ይህን ግዜ የደበቀውን ሰይጣናዊ ግብር ገልጦ ቆቡን ጥሎ ከቁራ ሰባት ጅ ጠቆረ ሰኔ አሥራሁለት ቀን ተመልሼ እመጣለሁ አጠፋሻለሁም ብሎ ዝቶባት እንደ ጢስ ተኞ እንደ ትብያ ተኖ ጠፍቶ ሄደ ።
ሰይጣን ዲያቢሎስ እንዳለሁም ግብሩን ለውጦ በሰኔ አሥራ ሁለት ቀንም የመላእከት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን መስሎ ባማረና በተዋበ ልብስ ወደ ቤቷ መጥቶ ተገለጠላት “ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና።” ተብሎ እንደተጻፈ 2ኛ ቆሮ 11፥14
ቤቴን በብርሃንህ የሞላህ አንተ ማነህ ? አለችሁ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነኝ ይህ ከብርሃኔ ተረጂ አላት ቆየኝ መጣው ብላ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጂ የነበረው ባሏ አስተራኒቆስ አስሎ ነሰጣትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕለ አድህኖ ይዛ መጣች ። እያመሳሰለችሽ ንጉሥ ለጭፍሮቹ መታወቂያ ማኅተቡን አትሞ አስይዞ ይልካቸዋል የእግዚአብሔር መላእክ ቅዱስ ሚካኤል ከሆንክ ማዕተመ መስቀልህ የንጉሥህ መታወቂያ በትረ መስቀልህ የታለ ?አለችሁ። እርሱም ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና እኛ በእግዚአብሔር ፊት የምንቆም መላእክት መስቀል መያዝ ለምናችን ጨርሶ አያስፈልገንም አላት ይህን ጊዜ አንተማ መላእኩ ቅዱስ ሚካኤል አይደለህም አላምንህም አለችሁ ያን ጊዜ እንዳ ወቀችበት ሲረዳ ግብሩ ቀይሮ በብርሃን የመላው ቤቷን በጽልመት መላው ቀንዱ በቀለ ፣ጥፍሩ እረዘረዘ፣ ዐይኑ ፈጠጠ ፣ጥርሱ ገጠጠ አንቺንስ ካላጠፋሁ ሠላሜን አላገኝም ብሎ ተወርውሮም አንቆ ያዛት ቅድስት እናት አፎምያም እውነተኛው ታላቁ መላእክ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እርዳኝ ብላ በጣር ውስጥ ሆና ተጣራች እውነተኛው የእግዚአብሔር መላእክም ከዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጣና ዲያቢሎስን ረግጦ ያስጨንቀው ገባ ሰይጣንም ሚካኤል ሆይ ጊዜዬ ሳይደርስ እንዳታጠፋኝ በፈጣሪህ እለምንሃለው እያለ ጮኸ ቅዱስ ሚካኤልም ለቀቀው በኖ ተኖ ጠፋ ቅድስት እናት አፎምያንንም ያረጋጋት ጀመር ። “ #የእግዚአብሔር_መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” እዳለ መጻሕፍ #መዝ (33) 34፥7
*አንባቢ ሆይ አንተስ በክርስቶስ ክርስቲያን ነኝ ትላለህንን እንግዲያውስ መስቀልህ የታል?
*አንባቢት ሆይ የንጉሥሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ትያለሽን? መልካም ትያለሽ ግን የንጉሡ ደመ ማዕተብ በትረ መስቀልሽ ከወዴት አለ? የአፎምያ ጥያቄ ይህ ነበር መስቀልህ የታለህ? ለአፎምያ ትክለኛ ጥያቄ መልስ የሆናት እውነተኛው ቅዱስ ሚካዬል በትረ መስቀሉን ጨብጦ ይዞ በመታየት ነው።ወዳጄ የድልህ ዐርማ የሆነውም " ሁልጊዜ በልብህ አኑረው፥ በአንገትህም እሰረው። ስትሄድም ይመራሃል፤ ስትተኛ ይጠብቅሃል፤ ስትነሣ ያነጋግርሃል። " #ምሳ 6÷21-22 የደሃ አደጊቱ ልጅ ባሕራንም የሞት ደብዳቤውን ተቀብሎ የደስታ የፍስሐ የሰርግ ደብዳቤ አድርጎ የመለሰለት የደስታ ሁሉ መልስ ቅዱስ ሚካኤል በዚህች ዕለት በነገዱ ሁሉ ላይ የተሾመበት የሹመቱ በዓል ነው!
መንፈስ ቅዱስ ያወቀውን ሰይጣን የሸመቀው ከጠላት የተንኮል እንቆቅልሽ ሁሉ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የደስታ መልስ ይሁንልን!
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
ሰኔ ፲፪ ቀን /፳፻፲፫ ዓ.ም