Forwarded from Mikha Denagil ምክሐ ደናግል
MD || “ስለ እናንተ ሲያማልዱ ይናፍቁአችኋል። ” || ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ Dn Henok Haile
https://youtube.com/watch?v=kcBXJ0sWoQY
https://youtube.com/watch?v=kcBXJ0sWoQY
YouTube
MD || “ስለ እናንተ ሲያማልዱ ይናፍቁአችኋል። ” || ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ Dn Henok Haile
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ቴሌግራም ቻናል
Telegram https://tttttt.me/Mikhadenagil
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ኢንስታግራም
Instagram https://www.instagram.com/mikhadenagil/?hl=en
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም የዩቱብ ቻናል
Youtube https://www.youtube.com/channel/UCIiCKAoZVHXJ2mlKGXDGyPg
የማኅበራችን…
Telegram https://tttttt.me/Mikhadenagil
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ኢንስታግራም
Instagram https://www.instagram.com/mikhadenagil/?hl=en
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም የዩቱብ ቻናል
Youtube https://www.youtube.com/channel/UCIiCKAoZVHXJ2mlKGXDGyPg
የማኅበራችን…
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
መዝሙር
የዋኅ መልአክ
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል
ታዳጊያችን ነህ ምክሩ ለልዑል
የአምላክ ኀይሉ መገለጫው ነህ
የእልፍ አእላፍ መላእክት መስፍናቸው ነህ
አዝ.........
ለሠራዊተ ሰማይ መላእክት አለቃቸው
ለፍጥረቱ ለባሕር ለየብሱ አጽንኦታቸው
የዋኅ ርኅሩህኅ መልአክ ኀዳጌ በቀል
በልመናው በጸሎቱ ያስምረናል ቅዱስ ሚካኤል
አዝ...........
የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ቅዱስ ሚካኤል
ለሰው ልጆች የምታዝን ምታማልድ ከልዑል
እነሆ ሕይወታችንን ባርክልን አደራህን
በኑሯችን ሁሉ ጠብቀን ባለን ዘመን
አዝ............
ሳለን በዓለም ዲያብሎስ እንዳይጥለን ጥንተ ጠላት
ድል አድራጊው ጠብቀን ሚካኤል ሆይ ሊቀ መላእክት
መካሬ ጽድቅ እውቀትን ሙላን ግለጥልን
በእምነት በተስፋ በፍቅር መኖርን
🛑 በዘማሪ ዳዊት ክብሩ /ዘምክሐ/ 🛑
ሙሉ ዝማሬውን በዚህ ተጭነው ይመልከቱት ይዘምሩ 👇👇👇
https://youtube.com/watch?v=mXiS3w0dARg&feature=share7
የዋኅ መልአክ
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል
ታዳጊያችን ነህ ምክሩ ለልዑል
የአምላክ ኀይሉ መገለጫው ነህ
የእልፍ አእላፍ መላእክት መስፍናቸው ነህ
አዝ.........
ለሠራዊተ ሰማይ መላእክት አለቃቸው
ለፍጥረቱ ለባሕር ለየብሱ አጽንኦታቸው
የዋኅ ርኅሩህኅ መልአክ ኀዳጌ በቀል
በልመናው በጸሎቱ ያስምረናል ቅዱስ ሚካኤል
አዝ...........
የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ ቅዱስ ሚካኤል
ለሰው ልጆች የምታዝን ምታማልድ ከልዑል
እነሆ ሕይወታችንን ባርክልን አደራህን
በኑሯችን ሁሉ ጠብቀን ባለን ዘመን
አዝ............
ሳለን በዓለም ዲያብሎስ እንዳይጥለን ጥንተ ጠላት
ድል አድራጊው ጠብቀን ሚካኤል ሆይ ሊቀ መላእክት
መካሬ ጽድቅ እውቀትን ሙላን ግለጥልን
በእምነት በተስፋ በፍቅር መኖርን
🛑 በዘማሪ ዳዊት ክብሩ /ዘምክሐ/ 🛑
ሙሉ ዝማሬውን በዚህ ተጭነው ይመልከቱት ይዘምሩ 👇👇👇
https://youtube.com/watch?v=mXiS3w0dARg&feature=share7
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
YouTube
🛑አዲስ ዝማሬ "አንቺ ነሽ " ዘማሪ ዳዊት ክብሩ ◈New Mezmur "Anchi Nesh" Z Dawit Kibru (Lyrics)
መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ያመሰገነሽ፤
ወላዲተ አምላክ ድንግል አንቺ ነሽ።
የመለኮት ማደሪያ ነሽ የብርሃን ድንኳን፤
ለመላእክት እኅት መሪ የኾንሽ ለጻድቃን።
የሕዝብ ሁሉ ኸኸ እናት ኸኸ የሁሉ እመቤት፤
የዓዳም ተስፋ ስንቅ የሆንሽ የዳነብሽ ከሞት
አንቺ ነሽ /2/ ብፅዕት ኪዳነ ምሕረት፤
ለዓለም ሁሉ መዳን ምክንያት የቃል እናት ታቦት
ለዓለም ሁሉ መድኃኒት የቃልኪዳኑ ታቦት።
ወርቅ የተጎናጽፈሽ፥…
ወላዲተ አምላክ ድንግል አንቺ ነሽ።
የመለኮት ማደሪያ ነሽ የብርሃን ድንኳን፤
ለመላእክት እኅት መሪ የኾንሽ ለጻድቃን።
የሕዝብ ሁሉ ኸኸ እናት ኸኸ የሁሉ እመቤት፤
የዓዳም ተስፋ ስንቅ የሆንሽ የዳነብሽ ከሞት
አንቺ ነሽ /2/ ብፅዕት ኪዳነ ምሕረት፤
ለዓለም ሁሉ መዳን ምክንያት የቃል እናት ታቦት
ለዓለም ሁሉ መድኃኒት የቃልኪዳኑ ታቦት።
ወርቅ የተጎናጽፈሽ፥…
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
🛑አዲስ ዝማሬ🛑
"የፋርስ ኮከብ"
በዘማሪት ሰብለ ስፍር
በቅርብ ቀን ይጠብቁን !!!
"የፋርስ ኮከብ"
በዘማሪት ሰብለ ስፍር
በቅርብ ቀን ይጠብቁን !!!
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በቅርብ ቀን ይጠብቁን !!!!
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
የተከበራችሁ የቴሌግራም ቻናሌ ተከታዮቼ ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን አዲስ የከፈትኩትን የዩትዩብ ቻናሌን እንዲሁም የቲክቶክ ቻናሌን፤ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ሌሎችንም በመጋበዝ አዳዲስ ስራዎችን አገልግሎቶችንም በመከታተል አገልግሎቱን ያበረታቱልኝ ስል በእግዚአብሔር ስም እጠይቃለሁኝ እግዚአብሔር ያክብርልኝ !!! 🙏🙏🙏
Youtube - https://youtube.com/@ZemariDawitkibru2405?si=63myQkvvdUPGM8JY
Telegram - https://tttttt.me/zdk24_5_21_official
Tiktok - https://www.tiktok.com/@davekb24?is_from_webapp=1&sender_device=pc
Instagram - https://www.instagram.com/dkibru402/?igshid=YTQwZjQ0NmI0OA%3D%3D
Facebook - https://www.facebook.com/deve.zman.9/
Youtube - https://youtube.com/@ZemariDawitkibru2405?si=63myQkvvdUPGM8JY
Telegram - https://tttttt.me/zdk24_5_21_official
Tiktok - https://www.tiktok.com/@davekb24?is_from_webapp=1&sender_device=pc
Instagram - https://www.instagram.com/dkibru402/?igshid=YTQwZjQ0NmI0OA%3D%3D
Facebook - https://www.facebook.com/deve.zman.9/
Telegram
የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
" ወቅታዊ እና አዳዲስ ወረቦችን ዝማሬዎችን ከነግጥሞቻቸው እና የቤተክርስቲያናችንን ወቅታዊ ትምህርቶችን ያገኛሉ !!!!! "
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
❤መድኃኔዓለም❤
#"ከአዳም ጎን አንዲት አፅም መንሣት ምን ይደንቅ!? ከእርሱ ሴትን ፈጠረ።የሰው ፍጥረትንም ሁሉ ፈጠረ።ጌታ የአብ ቃል ተሰጠ።" (ቅዱስ ኤፍሬም)
#እንደ ክርስቲያን ይህንን ቃል በሐሙስ ውዳሴ ማርያም ላይ ባነበብን ቁጥር የቀራንዮ በግ መድኃኔዓለም በዕፀ መስቀል ላይ ከፍ ብሎ ተሰቅሎ ስለኛ ሲሞሸር እኛንም ሲሞሽረን እንመለከተዋለን።ጌታችን ይህንን ስቅለቱን "ክብር" በማለት ጠርቶታል።"ጌታችን ኢየሱስም መለሰላቸው እንዲህ ሲል የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ ሰዓቱ ደርሶአል።"(ዮሐ 12:23) እሰቀላለሁ እሞታለሁ ማለቱ ነው።ክብሩማ ለእኛ ነው፤ፍቅር ስለሆነ በሥጋ ማርያም ድንግል ስለተዛመድንም የእኛን ክብር የራሱ ክብር አድርጎ ተናገረ።"የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ" የሚለው አነጋገር የሰው ልጅ የተባለ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ሲከብር (ሲሰቀል)፤በእርሱ የባሕርይ አምላክነት (መድኃኒትነት) ያመኑ ሁሉ ከብረው በቀኙ እንደሚቆሙ (እንደሚድኑ) ያሳያል።ለዚህ ነው በቀኙ የተሰቀለው ወንበዴ በመድኃኒትነቱ አምኖ የዳነው።
እንዴት በዚህ ቃል የመድኃኔ ዓለምን የሙሽርነቱን በዓል እንመለከታለን? ቢሉ
#"ከአዳም ጎን አንዲት አፅም መንሣት ምን ይደንቅ!?" እውነት ነው ያለ ተረፈ ደዌ፣ያለ ሕማም፣ያለ ቁስል የሆነ ነውና ይደንቃል።ከዚህ በላይ ደዌአችንን ከመቀበል ጋር ፤ ሕማማችንን ከመሸከም ጋር ፤ ቁስላችንን ከመቁሰል ጋር የሆነ "ከዳግማዊ አዳም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጎን የንጹሕ ውኃና የትኩስ ደም መፍሰስ ምን ይደንቅ!!!?"
#"ከእርሱ ሴትን ፈጠረ" ከቀዳማዊ አዳም ጎን ከተነሣ አፅም ሴትን(ሔዋንን) በጥንተ ተፈጥሮ ፈጠረ።ዳግማዊ አዳም መድኃኒታችን ከጎኑ ባፈሰሰው ውኃና ደምም ቅድስት ቤተክርስቲያንን በአዲስ ተፈጥሮ ሠራ።ሴትን ራሷ ከሆነው ወንድ እንዳስገኛት፤ቤተክርስቲያንንም ራሷ ከሆነላት ከራሱ አስገኝቷታል። አባታችን አዳም "ይህቺ አጥንት ከአጥንቴ ሥጋዋም ከሥጋዬ ነው ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል" እንዳለ፤ መድኃኔዓለምም "ይህቺ ጥምቀት ከጎኔ ከፈሰሰው ውኃ ፤ ማዕዷም ከእኔ ሥጋና ደም ነው ፤ ከእኔ ከክርስቶስ ተገኝታለችና ቤተክርስቲያን ትባል" ይላል።ሔዋን መባሏ የሕያዋን እናት በመሆኗ ነበር ፤ ቤተክርስቲያንም የሕያዋን (የክርስቲያኖች) እናት ናት።
#"የሰው ፍጥረትንም ሁሉ ፈጠረ" ከአዳምና ከሔዋን "ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሏት" ባለው አምላካዊ ቡራኬው የሰው ፍጥረትን ሁሉ እንደፈጠረ ፤ "ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ ስም አጥምቋቸው።" በሚለው አምላካዊ ትእዛዙ ክርስቲያኖችን ሁሉ ፈጠረ።
#"ጌታ የአብ ቃል ተሰጠ" የጌቶች ጌታ፣ ቃለ አብ ፣የዓለም መድኃኒት በሥጋ ማርያም ተገልጦ ለሕማም ፣ ለመስቀል ፣ ለሞት ተላልፎ ተሰጠልን።"ሕፃን ተወልዶልናል ወንድ ልጅም ተሰጥቶናል" እንዲል።እንዲህ ባለ መልኩ በዙፋኑ ዕፀ መስቀል ላይ ነግሦ አነገሠን፤ተሞሽሮ ሞሸረን፤ተርቦ አጠገበን፤ተጠምቶ አረካን፤ተራቁቶ አለበሰን፤ቆስሎ ፈወሰን፤ሞቶ ሕይወትን ሰጠን!!!
የመድኃኔዓለም ቸርነቱ አይለየን!!!
የመስቀሉን ፍቅር ያሳድርብን!!!
የካቲት 27/2016 ዓ.ም
ኢዮብ ክንፈ
#"ከአዳም ጎን አንዲት አፅም መንሣት ምን ይደንቅ!? ከእርሱ ሴትን ፈጠረ።የሰው ፍጥረትንም ሁሉ ፈጠረ።ጌታ የአብ ቃል ተሰጠ።" (ቅዱስ ኤፍሬም)
#እንደ ክርስቲያን ይህንን ቃል በሐሙስ ውዳሴ ማርያም ላይ ባነበብን ቁጥር የቀራንዮ በግ መድኃኔዓለም በዕፀ መስቀል ላይ ከፍ ብሎ ተሰቅሎ ስለኛ ሲሞሸር እኛንም ሲሞሽረን እንመለከተዋለን።ጌታችን ይህንን ስቅለቱን "ክብር" በማለት ጠርቶታል።"ጌታችን ኢየሱስም መለሰላቸው እንዲህ ሲል የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ ሰዓቱ ደርሶአል።"(ዮሐ 12:23) እሰቀላለሁ እሞታለሁ ማለቱ ነው።ክብሩማ ለእኛ ነው፤ፍቅር ስለሆነ በሥጋ ማርያም ድንግል ስለተዛመድንም የእኛን ክብር የራሱ ክብር አድርጎ ተናገረ።"የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ" የሚለው አነጋገር የሰው ልጅ የተባለ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ሲከብር (ሲሰቀል)፤በእርሱ የባሕርይ አምላክነት (መድኃኒትነት) ያመኑ ሁሉ ከብረው በቀኙ እንደሚቆሙ (እንደሚድኑ) ያሳያል።ለዚህ ነው በቀኙ የተሰቀለው ወንበዴ በመድኃኒትነቱ አምኖ የዳነው።
እንዴት በዚህ ቃል የመድኃኔ ዓለምን የሙሽርነቱን በዓል እንመለከታለን? ቢሉ
#"ከአዳም ጎን አንዲት አፅም መንሣት ምን ይደንቅ!?" እውነት ነው ያለ ተረፈ ደዌ፣ያለ ሕማም፣ያለ ቁስል የሆነ ነውና ይደንቃል።ከዚህ በላይ ደዌአችንን ከመቀበል ጋር ፤ ሕማማችንን ከመሸከም ጋር ፤ ቁስላችንን ከመቁሰል ጋር የሆነ "ከዳግማዊ አዳም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጎን የንጹሕ ውኃና የትኩስ ደም መፍሰስ ምን ይደንቅ!!!?"
#"ከእርሱ ሴትን ፈጠረ" ከቀዳማዊ አዳም ጎን ከተነሣ አፅም ሴትን(ሔዋንን) በጥንተ ተፈጥሮ ፈጠረ።ዳግማዊ አዳም መድኃኒታችን ከጎኑ ባፈሰሰው ውኃና ደምም ቅድስት ቤተክርስቲያንን በአዲስ ተፈጥሮ ሠራ።ሴትን ራሷ ከሆነው ወንድ እንዳስገኛት፤ቤተክርስቲያንንም ራሷ ከሆነላት ከራሱ አስገኝቷታል። አባታችን አዳም "ይህቺ አጥንት ከአጥንቴ ሥጋዋም ከሥጋዬ ነው ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል" እንዳለ፤ መድኃኔዓለምም "ይህቺ ጥምቀት ከጎኔ ከፈሰሰው ውኃ ፤ ማዕዷም ከእኔ ሥጋና ደም ነው ፤ ከእኔ ከክርስቶስ ተገኝታለችና ቤተክርስቲያን ትባል" ይላል።ሔዋን መባሏ የሕያዋን እናት በመሆኗ ነበር ፤ ቤተክርስቲያንም የሕያዋን (የክርስቲያኖች) እናት ናት።
#"የሰው ፍጥረትንም ሁሉ ፈጠረ" ከአዳምና ከሔዋን "ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሏት" ባለው አምላካዊ ቡራኬው የሰው ፍጥረትን ሁሉ እንደፈጠረ ፤ "ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ ስም አጥምቋቸው።" በሚለው አምላካዊ ትእዛዙ ክርስቲያኖችን ሁሉ ፈጠረ።
#"ጌታ የአብ ቃል ተሰጠ" የጌቶች ጌታ፣ ቃለ አብ ፣የዓለም መድኃኒት በሥጋ ማርያም ተገልጦ ለሕማም ፣ ለመስቀል ፣ ለሞት ተላልፎ ተሰጠልን።"ሕፃን ተወልዶልናል ወንድ ልጅም ተሰጥቶናል" እንዲል።እንዲህ ባለ መልኩ በዙፋኑ ዕፀ መስቀል ላይ ነግሦ አነገሠን፤ተሞሽሮ ሞሸረን፤ተርቦ አጠገበን፤ተጠምቶ አረካን፤ተራቁቶ አለበሰን፤ቆስሎ ፈወሰን፤ሞቶ ሕይወትን ሰጠን!!!
የመድኃኔዓለም ቸርነቱ አይለየን!!!
የመስቀሉን ፍቅር ያሳድርብን!!!
የካቲት 27/2016 ዓ.ም
ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
❤ #በዓለ_ወልድ❤
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።የሚኰንንስ ማንነው?የሞተው ይልቁንም በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፤ደግሞም ስለኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።" (ሮሜ 8:34)
ይህ የብርሃነ ዓለም የቅዱስ ጳውሎስ ቃል የቅድስት ቤተክርስትያናችን የሃይማኖት ጸሎት ነው።
በቅድስት ቤተክርስቲያን የምናምነውን እንጸልያለን፤ የምንጸልየውን እናምናለን።በሌላ አነጋገር ሃይማኖታችንን እንጸልየዋለን ፤ ጸሎታችንም ሃይማኖታችን ነው።ሃይማኖት በእግዚአብሔር ማመን፤በእርሱ መታመን ፤ እርሱንም ብቻ ተስፋ ማድረግ ነው።ሃይማኖታችን ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው።ሃይማኖትን የሰጠንም እግዚአብሔር ነው።"ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት" እንዲል (ይሁዳ 1:3)።በመሆኑም ከእግዚአብሔር የተሰጠንን ሃይማኖት ( በእርሱ ማመንን ) ለሰጠን ለእርሱ በጸሎት መልክ እናቀርበዋለን።ይህንንም የምናደርገው እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበትን ነገር ፍለጋ ነው።"ያለ ሃይማኖት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም"ና (ዕብ 11:6)።
በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ የተመሠረተች የማዕዘኗ ራስ ድንጋይም ኢየሱስ ክርስቶስ የሆነላት (ኤፌ 2:20) ቅድስት ቤተክርስቲያን የሐዋርያው ሃይማኖት ሃይማኖቷ ነውና ትጸልየዋለች።የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይህንን እንዴት እንደምትጸልየው ከመመልከታችን በፊት የቃሉን መልእክት በአጭሩ እንመልከት።
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው" ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "ምስለ ጻድቅ ትጸድቅ" (ከጻድቅ ጋር ጻድቅ ትሆናለህ) ማለትም ለጻድቅ የጽድቁን ዋጋ ትሰጠዋለህ(መዝ 17:25) በማለት እንደተናገረው ለጻድቃን ጽድቃቸውን መስክሮ ዋጋቸው መንግሥተሰማያትን ሰጥቶ የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።
"የሚኰንንስ ማንነው?" አልመለስ የሚሉትን በሥጋ የሚቀስፋቸው በነፍስ የሚፈርድባቸው ማን ነው? አንድም በርቱዕ ፍርዱ ሥጋንም ነፍስንም በአንድነት በገሃነም የሚቀጣ ማንነው?(ማቴ 10:28)
"የሞተው" በዕፀ መስቀል ላይ ቅዱስ ሥጋውን ከክብርት ነፍሱ በመልካም ፈቃዱ የለየው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በሞቱ ጊዜም ፈርዷል።በቀኙ የተሰቀለውን ሲያጸድቀው (የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነውና) በግራው የተሰቀለውን ኰንኖታል።ሞቱም መፋረጃ ነው፤በሞቱ ያመኑ ሲድኑ ያላመኑት ግን ይኰነናሉ።
"ይልቁንም ከሙታን ተለይቶ የተነሣው" በኩረ ትንሣኤአችን ሆኖ በባሕርይ ሥልጣኑ ከሞት የተነሣው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በትንሣኤውም ጊዜ ፈርዷል።"እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ።የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኃያልም ሰው፤ጠላቶቹን በኋላቸው መታቸው የዘለዓለምን ኀሣር ሰጣቸው።"(መዝ 77:65-66) ተብሎ እንደተነገረ የትንሣኤው ተቃዋሚ የሆኑትን አይሁድን፣መናፍቃንንና አጋንንትን ሲፈርድባቸው በአንጻሩ ትንሣኤውን በፍጹም ልባቸው ያመኑትን ሐዋርያትን እስከ ምድር ዳር ድረስ የትንሣኤው ምስክሮች አድርጓቸዋል(ሐዋ 1:8 ና 21-22)የጌታ ትንሣኤውም መፋረጃ ነው።በትንሣኤው ያመኑት ሲድኑ ያላመኑት ግን ይፈረድባቸዋልና።
"በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው" በእግዚአብሔርነቱ ሥልጣን የሚኖር አንድም በአምላክነቱ ከአባቱ እኩል የሆነው ንጉሣችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።እንግዲህ እግዚአብሔር ከሆነ ሥራው ምንድንነው መሥራት መቅጻት፣ማምሸት ማንጋት፣መግደል ማዳን፣ማጽደቅ መኰነን፤ሥነፍጥረትን ሁሉ ማስተዳደር ነው።ይህ ሁሉ የፍርድ ሥራ ይባላል።ሞቱም ትንሣኤውም መፋራጃ የሆነው ከእርሱ ፈራጅነት (እግዚአብሔርነት ) የተነሣ ነው።
"ስለኛ የሚማልደው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" አንድ ጊዜ ፈጽሞ ባቀረባት የዘለዓለማዊ ክህነት አገልግሎት (ለዘለዓለም የሚሆን መሥዋዕት አቅራቢነት) ያዳነን ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።"የሚማልደው" የሚለው ቃል በትንቢት አንቀጽ (future tense) ቢጻፍም የሚገልጸው ግን የተፈጸመን ድርጊት ነው።እንዲህ ያሉ አገላለጾች በቅዱሳት መፃሕፍት ይገኛሉ።ለምሳሌ"ሕፃን ተወልዶልናልና" ተብሎ የተነገረው ወደፊት ስለሚወለደው አምላካችን ነው።"እንደ መልከ ጼዴቅ ሥርዓት አንተ ለዘለዓለም ካህን ነህ"(መዝ 109:4) ተብሎ የተነገረለት አምላካችን የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅ ይፈርድ እንደነበር ለዘለዓለሙ የሚፈርድ ነው።ይህች የክህነት አገልግሎቱም መፋረጃ ናት።በዚህ የዘለዓለም ክህነት አገልግሎቱ የሠዋውን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የተቀበለ ሲድን ያልተቀበለ ግን ይፈረድበታልና። ይህ ሁሉ በጥቅሉ የሚያጸድቅም የሚኰንንም እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ማለት ነው።ሞቱም፣ትንሣኤውም፣ዳግም ምጽአቱም በቅድስት ቤተክርስቲያን በዓላተ ወልድ (የወልድ በዓላት) ናቸው።
የካቲት 29/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።የሚኰንንስ ማንነው?የሞተው ይልቁንም በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፤ደግሞም ስለኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።" (ሮሜ 8:34)
ይህ የብርሃነ ዓለም የቅዱስ ጳውሎስ ቃል የቅድስት ቤተክርስትያናችን የሃይማኖት ጸሎት ነው።
በቅድስት ቤተክርስቲያን የምናምነውን እንጸልያለን፤ የምንጸልየውን እናምናለን።በሌላ አነጋገር ሃይማኖታችንን እንጸልየዋለን ፤ ጸሎታችንም ሃይማኖታችን ነው።ሃይማኖት በእግዚአብሔር ማመን፤በእርሱ መታመን ፤ እርሱንም ብቻ ተስፋ ማድረግ ነው።ሃይማኖታችን ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው።ሃይማኖትን የሰጠንም እግዚአብሔር ነው።"ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት" እንዲል (ይሁዳ 1:3)።በመሆኑም ከእግዚአብሔር የተሰጠንን ሃይማኖት ( በእርሱ ማመንን ) ለሰጠን ለእርሱ በጸሎት መልክ እናቀርበዋለን።ይህንንም የምናደርገው እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበትን ነገር ፍለጋ ነው።"ያለ ሃይማኖት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም"ና (ዕብ 11:6)።
በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ የተመሠረተች የማዕዘኗ ራስ ድንጋይም ኢየሱስ ክርስቶስ የሆነላት (ኤፌ 2:20) ቅድስት ቤተክርስቲያን የሐዋርያው ሃይማኖት ሃይማኖቷ ነውና ትጸልየዋለች።የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይህንን እንዴት እንደምትጸልየው ከመመልከታችን በፊት የቃሉን መልእክት በአጭሩ እንመልከት።
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው" ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "ምስለ ጻድቅ ትጸድቅ" (ከጻድቅ ጋር ጻድቅ ትሆናለህ) ማለትም ለጻድቅ የጽድቁን ዋጋ ትሰጠዋለህ(መዝ 17:25) በማለት እንደተናገረው ለጻድቃን ጽድቃቸውን መስክሮ ዋጋቸው መንግሥተሰማያትን ሰጥቶ የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።
"የሚኰንንስ ማንነው?" አልመለስ የሚሉትን በሥጋ የሚቀስፋቸው በነፍስ የሚፈርድባቸው ማን ነው? አንድም በርቱዕ ፍርዱ ሥጋንም ነፍስንም በአንድነት በገሃነም የሚቀጣ ማንነው?(ማቴ 10:28)
"የሞተው" በዕፀ መስቀል ላይ ቅዱስ ሥጋውን ከክብርት ነፍሱ በመልካም ፈቃዱ የለየው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በሞቱ ጊዜም ፈርዷል።በቀኙ የተሰቀለውን ሲያጸድቀው (የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነውና) በግራው የተሰቀለውን ኰንኖታል።ሞቱም መፋረጃ ነው፤በሞቱ ያመኑ ሲድኑ ያላመኑት ግን ይኰነናሉ።
"ይልቁንም ከሙታን ተለይቶ የተነሣው" በኩረ ትንሣኤአችን ሆኖ በባሕርይ ሥልጣኑ ከሞት የተነሣው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በትንሣኤውም ጊዜ ፈርዷል።"እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ።የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኃያልም ሰው፤ጠላቶቹን በኋላቸው መታቸው የዘለዓለምን ኀሣር ሰጣቸው።"(መዝ 77:65-66) ተብሎ እንደተነገረ የትንሣኤው ተቃዋሚ የሆኑትን አይሁድን፣መናፍቃንንና አጋንንትን ሲፈርድባቸው በአንጻሩ ትንሣኤውን በፍጹም ልባቸው ያመኑትን ሐዋርያትን እስከ ምድር ዳር ድረስ የትንሣኤው ምስክሮች አድርጓቸዋል(ሐዋ 1:8 ና 21-22)የጌታ ትንሣኤውም መፋረጃ ነው።በትንሣኤው ያመኑት ሲድኑ ያላመኑት ግን ይፈረድባቸዋልና።
"በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው" በእግዚአብሔርነቱ ሥልጣን የሚኖር አንድም በአምላክነቱ ከአባቱ እኩል የሆነው ንጉሣችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።እንግዲህ እግዚአብሔር ከሆነ ሥራው ምንድንነው መሥራት መቅጻት፣ማምሸት ማንጋት፣መግደል ማዳን፣ማጽደቅ መኰነን፤ሥነፍጥረትን ሁሉ ማስተዳደር ነው።ይህ ሁሉ የፍርድ ሥራ ይባላል።ሞቱም ትንሣኤውም መፋራጃ የሆነው ከእርሱ ፈራጅነት (እግዚአብሔርነት ) የተነሣ ነው።
"ስለኛ የሚማልደው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" አንድ ጊዜ ፈጽሞ ባቀረባት የዘለዓለማዊ ክህነት አገልግሎት (ለዘለዓለም የሚሆን መሥዋዕት አቅራቢነት) ያዳነን ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።"የሚማልደው" የሚለው ቃል በትንቢት አንቀጽ (future tense) ቢጻፍም የሚገልጸው ግን የተፈጸመን ድርጊት ነው።እንዲህ ያሉ አገላለጾች በቅዱሳት መፃሕፍት ይገኛሉ።ለምሳሌ"ሕፃን ተወልዶልናልና" ተብሎ የተነገረው ወደፊት ስለሚወለደው አምላካችን ነው።"እንደ መልከ ጼዴቅ ሥርዓት አንተ ለዘለዓለም ካህን ነህ"(መዝ 109:4) ተብሎ የተነገረለት አምላካችን የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅ ይፈርድ እንደነበር ለዘለዓለሙ የሚፈርድ ነው።ይህች የክህነት አገልግሎቱም መፋረጃ ናት።በዚህ የዘለዓለም ክህነት አገልግሎቱ የሠዋውን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የተቀበለ ሲድን ያልተቀበለ ግን ይፈረድበታልና። ይህ ሁሉ በጥቅሉ የሚያጸድቅም የሚኰንንም እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ማለት ነው።ሞቱም፣ትንሣኤውም፣ዳግም ምጽአቱም በቅድስት ቤተክርስቲያን በዓላተ ወልድ (የወልድ በዓላት) ናቸው።
የካቲት 29/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from Mikha Denagil ምክሐ ደናግል
YouTube
' አትድከሚ ኢትዮጵያ " በዘማሪ ክብሮም ግዳይ | zemari kibrom giday | Atdekmi ethiopia | mahtot tube | new mezmur
አዲስ ዝማሬ ' አትድከሚ ኢትዮጵያ " በዘማሪ ክብሮም ግዳይ
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ቴሌግራም ቻናል
Telegram https://tttttt.me/Mikhadenagil
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ኢንስታግራም
Instagram https://www.instagram.com/mikhadenagi...
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም የዩቱብ ቻናል
Youtube https://www.youtube.com/…
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ቴሌግራም ቻናል
Telegram https://tttttt.me/Mikhadenagil
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ኢንስታግራም
Instagram https://www.instagram.com/mikhadenagi...
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም የዩቱብ ቻናል
Youtube https://www.youtube.com/…
"የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ።"(1ኛ ዮሐ 3:9)
ቅድስት ቤተክርስቲያን የክርስቲያኖች ጉባኤ ናት።ይህቺ ጉባኤ ደግሞ ለጌታዋ ለኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽሪት ናት።የሚስት ፈቃድ ወደ ባልዋ እንደሆነ ሁሉ የቅድስት ቤተክርስቲያን ፈቃድም ሙሽራዋ ወደ ሆነው ወደ ጌታዋ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።የእርሱን ፍለጋ እየተከተለች ፤ የእርሱን ዱካ እየረገጠች ፤ እርሱ ከገባበት ትገባለች።ይህንን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስንና የቅድስት ቤተክርስቲያንን ግንኙነት በራስና በአካል መግለጥም ይቻላል።ራስ(አእምሮ) አካልን እንደሚያዝዝ ፤ክርስቶስም ቅድስት ቤተክርስቲያንን ያዝዛታል።አካልም ለራስ (ለአእምሮ) እንደሚታዘዝ እንዲሁ ቅድስት ቤተክርስቲያንም ለራሷ ለኢየሱስ ክርስቶስ ትታዘዛለች።እርሱ ካዘዛትና ፤ ሠርቶ ካሳያት ፤ ከእርሱ ፈቃድ ውጪም የምታደርገው አንዳች ነገር የለም።አምላካችን ፈጽሞ ካስተማራት ትምህርት ሌላ እንግዳ ትምህርት ፤ ሠርቶ ካሳያትም ትሩፋት ውጪ የምትሠራ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን የለችም።
ጌታችን የፈጸማቸው ሥራዎች ሁሉ ዓላማቸው የዲያብሎስን ሥራ ማፍረስና እኛን ማዳን ነው።በሥጋ ማርያም ድንግል ተገልጦ ከፈጸማቸው ሥራዎች መካከል የሰውን መዳን የማይመለከት ምንም የለም።ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ ፤ እኛንም እንዲያድን ከፈጸማቸው ሥራዎች መካከል አንዱ ጾም ነው።
"ከዚያ ወዲያ ጌታችን ኢየሱስ ከዲያቢሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው" : ከጥምቀቱ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ በሚሆን ፈቃዱ ወደ ገዳመ ቆሮንጦስ ገብቷል።በገዛ ፈቃዱ ተመርቶ የጠፋ አዳምን ፍለጋ ያድነው ዘንድ በፈቃዱ ወደ ገዳመ ቆሮንጦስ ገባ።"ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ" ማለቱም ቀዳማዊ አዳም ከዲያብሎስ ተፈትኖ የወደቀባቸውን ፈተናዎች ድል ይነሣ ዘንድ ነው።እርሱ ከጥምቀቱ በኋላ በሦስቱ አርእስተ ኃጣውእ (የኃጢአት ራሶች)ተፈትኖና ድል ነሥቶ የጥምቀት ልጆች ሁላችን እነዚህ ፈተናዎች እንዳሉብንና ድል መንሣት እንደምንችል ነገረን ። "በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ።ነገር ግን አይዟችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ" እንዳለው (ዮሐ 16:33)
"አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ" : ዘመን የማይቆጥርለት አምላክ እኛን ዘመን በማይቆጠርባት መንግሥተ ሰማያት ያኖረን ዘንድ አርባ ተብሎ ጊዜ ተቆጠረለት።በአርባ ቀን ያገኛትን ልጅነት አዳም አስወስዶ ነበርና ለሱ ለመካስ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጦመ ።"ለፀሐይ ቀንን ያስገዛው ለጨረቃና ለከዋክብትም ሌሊትን ያስገዛቸው"(መዝ 135:8 ና 9) አምላክ ቀንና ሌሊት ጦመ።አዳም በመብል ቢወድቅ ጌታችን ግን በጾም አነሣው።በሥጋ የተራቡትን በተአምራት በነፍስ የተራቡትን በትምህርት የሚያጠግብ እርሱ በጽድቅ ያጠግበን ዘንድ ተራበ።
"ፈታኝም ቀርቦ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው" : ፈቅዶለት ነው እንጂ ዲያቢሎስማ ይህንን ያህል ድፍረት አይደፍርም ነበር።የእግዚአብሔር ባሕርይ ልጅ በዚህ ስስት ከመፈተኑ በፊት የእግዚአብሔር የጸጋ ልጆቹ አዳምና ሔዋን ተፈትነው ነበር።በዚህ የስስት ፈተና "ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፥ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ።"(ዘፍ 3:6) ዳግማዊ አዳም ኢየሱስ ክርስቶስ ግን፦
"ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው።"
ጌታችን ይህንን የስስት ፈተና በትሕርምት ድል ነሥቶ የዲያቢሎስን ሐሳብና ሥራ አፈረሰ።የዲያቢሎስ ሐሳቡ የክርስቶስን "የእግዚአብሔር ልጅነቱን" ማረጋገጥና ዓለም እንዳይድን በአይሁድ እንዳይሰቀል ማከላከል ሲሆን ሥራው ደግሞ ስስት ነው።ጌታችን ድንጋዮቹን እንጀራ ቢያደርግለት ኖሮ፤የኋላ መናፍቃን ተነሥተው እንደ ጌታ የሰይጣንን ቃል መፈጸም ይገባል ባሉ ነበር ። አዳም የሚኖረው "ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል" ነበር ። ይህቺውም ትእዛዙ ናት።"መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና" (ዘፍ 2:17) ባለው ትእዛዝ ። አዳም ይህቺን ትእዛዝ ቢጠብቅ በሕይወት ይኖር ነበር።"ተብሎ ተጽፎአል"(ዘዳ 8:3) የሚለው አነጋገር ሰይጣን በቃለ መፃሕፍት እንደሚሸነፍ የሚያረጋግጥ ነው።
ስስት የሚበላውን፣የሚጠጣውን፣የሚለበሰውን እጅግ መውደድ (መሳሳት) ነው።ለሚያልፈው የዓለም ነገር ሁሉ መጎምጀት ስስት ነው።ይህንን ፈተና ልክ እንደ ጌታችን በትሕርምት ድል መንሣት ይጠበቅብናል።ሁልጊዜም ቢሆን ስስትን የምናሸንፈው "ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣውን ቃል ሁሉ" በማሰብ ነው።ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃልም፦
የመጀመሪያው በነፍስ የተራቡትን የሚያጠግብ የቅዱስ ወንጌል ትምህርት ነው።ጌታችን በቅዱስ ወንጌሉ "ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት ወይም ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ነፍስ ከመብል ሰውነትስ ከልብስ አይበልጥምን?" በማለት አስተምሯል (ማቴ 6:25) እኔን የምትመስልን ነፍስ ካለመኖር ፈጥሬ ከሰጠኋችሁ ለጥቂት ጊዜ ነፍሳችሁ ከሥጋ ጋር ተዋሕዳ የምትቆይበትን መብል እንዴት እነሣችኋለሁ?፤ሥጋን ከአራቱ ባሕርያት ፈጥሬ ከሰጠኋችሁ ሥጋችሁ የሚለብሰውን አላቂ ልብስ እንዴት እነሣችኋለሁ? ማለቱ ነው።ይህም ብቻ አይደለም ለሰውነታችሁ ቤዛ የሚሆን ቅዱስ ሥጋዬን ክቡር ደሜን ከሰጣኋችሁ ፤ በመንግሥተ ሰማያትም የብርሃን ልብስን ካዘጋጀሁላችሁ ለሥጋችሁ የሚሆን መብልና ልብስን እንዴት እነሣችኋለሁ? ማለቱ ነው። እውነት ነው እጅግ ትልቁን የሰጠንን አምላክ በጥቂቱ የምንጠረጥረው ብዙዎች ነን።የጌታችን ተወዳጁ የሚሆን ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስም "ዓለምንና በዓለም ያለውን አትውደዱ፤ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት..." በማለት በስስት እንዳንሸነፍ መክሮናል።(1ኛ ዮሐ 2:15)
ስስትን "ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል" (ጌታችን ስለጾምና ምጽዋት ባስተማራት ትምህርት) ድል እናደርገዋለን ። " ስትጦሙም፥ እንደ ግብዞች አትጠውልጉ፤ ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ ፊታቸውን ያጠፋሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።አንተ ግን ስትጦም፥ በስውር ላለው አባትህ እንጂ እንደ ጦመኛ ለሰዎች እንዳትታይ ራስህን ተቀባ ፊትህንም ታጠብ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።"(ማቴ 6:16) እኛ ያልሳሳንለትን መብልንና ልብስንም ለሌላቸው መስጠት አለብን።በዚህም ጾም ከምጽዋት ጋር ትተባበራለች።
"ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል" ተአምር ነው።ስለዚህ ሰው በእግዚአብሔር ተአምር ጭምር እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም።ጌታችን በዘመነ ኤልያስ በነቢዩ ኤልያስ አድሮ በሰራፕታ ለነበረችው ባልቴት ጥቂቱን ዘይትና እፍኙን ዱቄት እንዳበረከተ እንዲሁ በዘመነ ሐዲስም ሁለት ዓሦችንና አምስት እንጀራዎችን አበርክቶ በተአምር አምስት ሺ ገበያ ሕዝብ አጥግቧል(1ኛ ነገ 17:7-17)።ራሱ ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስም የኖረው በእግዚአብሔር ተአምር ነው።"የእግዚአብሔርም ቃል እንዲህ ሲል ለእርሱ መጣለት።ከዚህ ተነሥተህ ወደ ምሥራቅ ሂድ፥ በዮርዳኖስም ትይዩ ባለው በኮራት ፈፋ ውስጥ ተሸሸግ።ከወንዙም ትጠጣለህ፥ ቍራዎችም በዚያ ይመግቡህ ዘንድ አዝዣለሁ። ሄደም እንደ እግዚአብሔር ቃልም አደረገ። ሄዶም በዮርዳኖስ ትይዩ ባለው በኮራት ፈፋ ውስጥ ተቀመጠ። ቍራዎቹ በየጥዋትና በየማታው እንጀራና ሥጋ ያመጡለት ነበር፤ ከወንዙም
ቅድስት ቤተክርስቲያን የክርስቲያኖች ጉባኤ ናት።ይህቺ ጉባኤ ደግሞ ለጌታዋ ለኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽሪት ናት።የሚስት ፈቃድ ወደ ባልዋ እንደሆነ ሁሉ የቅድስት ቤተክርስቲያን ፈቃድም ሙሽራዋ ወደ ሆነው ወደ ጌታዋ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።የእርሱን ፍለጋ እየተከተለች ፤ የእርሱን ዱካ እየረገጠች ፤ እርሱ ከገባበት ትገባለች።ይህንን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስንና የቅድስት ቤተክርስቲያንን ግንኙነት በራስና በአካል መግለጥም ይቻላል።ራስ(አእምሮ) አካልን እንደሚያዝዝ ፤ክርስቶስም ቅድስት ቤተክርስቲያንን ያዝዛታል።አካልም ለራስ (ለአእምሮ) እንደሚታዘዝ እንዲሁ ቅድስት ቤተክርስቲያንም ለራሷ ለኢየሱስ ክርስቶስ ትታዘዛለች።እርሱ ካዘዛትና ፤ ሠርቶ ካሳያት ፤ ከእርሱ ፈቃድ ውጪም የምታደርገው አንዳች ነገር የለም።አምላካችን ፈጽሞ ካስተማራት ትምህርት ሌላ እንግዳ ትምህርት ፤ ሠርቶ ካሳያትም ትሩፋት ውጪ የምትሠራ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን የለችም።
ጌታችን የፈጸማቸው ሥራዎች ሁሉ ዓላማቸው የዲያብሎስን ሥራ ማፍረስና እኛን ማዳን ነው።በሥጋ ማርያም ድንግል ተገልጦ ከፈጸማቸው ሥራዎች መካከል የሰውን መዳን የማይመለከት ምንም የለም።ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ ፤ እኛንም እንዲያድን ከፈጸማቸው ሥራዎች መካከል አንዱ ጾም ነው።
"ከዚያ ወዲያ ጌታችን ኢየሱስ ከዲያቢሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው" : ከጥምቀቱ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ በሚሆን ፈቃዱ ወደ ገዳመ ቆሮንጦስ ገብቷል።በገዛ ፈቃዱ ተመርቶ የጠፋ አዳምን ፍለጋ ያድነው ዘንድ በፈቃዱ ወደ ገዳመ ቆሮንጦስ ገባ።"ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ" ማለቱም ቀዳማዊ አዳም ከዲያብሎስ ተፈትኖ የወደቀባቸውን ፈተናዎች ድል ይነሣ ዘንድ ነው።እርሱ ከጥምቀቱ በኋላ በሦስቱ አርእስተ ኃጣውእ (የኃጢአት ራሶች)ተፈትኖና ድል ነሥቶ የጥምቀት ልጆች ሁላችን እነዚህ ፈተናዎች እንዳሉብንና ድል መንሣት እንደምንችል ነገረን ። "በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ።ነገር ግን አይዟችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ" እንዳለው (ዮሐ 16:33)
"አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ" : ዘመን የማይቆጥርለት አምላክ እኛን ዘመን በማይቆጠርባት መንግሥተ ሰማያት ያኖረን ዘንድ አርባ ተብሎ ጊዜ ተቆጠረለት።በአርባ ቀን ያገኛትን ልጅነት አዳም አስወስዶ ነበርና ለሱ ለመካስ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጦመ ።"ለፀሐይ ቀንን ያስገዛው ለጨረቃና ለከዋክብትም ሌሊትን ያስገዛቸው"(መዝ 135:8 ና 9) አምላክ ቀንና ሌሊት ጦመ።አዳም በመብል ቢወድቅ ጌታችን ግን በጾም አነሣው።በሥጋ የተራቡትን በተአምራት በነፍስ የተራቡትን በትምህርት የሚያጠግብ እርሱ በጽድቅ ያጠግበን ዘንድ ተራበ።
"ፈታኝም ቀርቦ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው" : ፈቅዶለት ነው እንጂ ዲያቢሎስማ ይህንን ያህል ድፍረት አይደፍርም ነበር።የእግዚአብሔር ባሕርይ ልጅ በዚህ ስስት ከመፈተኑ በፊት የእግዚአብሔር የጸጋ ልጆቹ አዳምና ሔዋን ተፈትነው ነበር።በዚህ የስስት ፈተና "ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፥ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ።"(ዘፍ 3:6) ዳግማዊ አዳም ኢየሱስ ክርስቶስ ግን፦
"ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው።"
ጌታችን ይህንን የስስት ፈተና በትሕርምት ድል ነሥቶ የዲያቢሎስን ሐሳብና ሥራ አፈረሰ።የዲያቢሎስ ሐሳቡ የክርስቶስን "የእግዚአብሔር ልጅነቱን" ማረጋገጥና ዓለም እንዳይድን በአይሁድ እንዳይሰቀል ማከላከል ሲሆን ሥራው ደግሞ ስስት ነው።ጌታችን ድንጋዮቹን እንጀራ ቢያደርግለት ኖሮ፤የኋላ መናፍቃን ተነሥተው እንደ ጌታ የሰይጣንን ቃል መፈጸም ይገባል ባሉ ነበር ። አዳም የሚኖረው "ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል" ነበር ። ይህቺውም ትእዛዙ ናት።"መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና" (ዘፍ 2:17) ባለው ትእዛዝ ። አዳም ይህቺን ትእዛዝ ቢጠብቅ በሕይወት ይኖር ነበር።"ተብሎ ተጽፎአል"(ዘዳ 8:3) የሚለው አነጋገር ሰይጣን በቃለ መፃሕፍት እንደሚሸነፍ የሚያረጋግጥ ነው።
ስስት የሚበላውን፣የሚጠጣውን፣የሚለበሰውን እጅግ መውደድ (መሳሳት) ነው።ለሚያልፈው የዓለም ነገር ሁሉ መጎምጀት ስስት ነው።ይህንን ፈተና ልክ እንደ ጌታችን በትሕርምት ድል መንሣት ይጠበቅብናል።ሁልጊዜም ቢሆን ስስትን የምናሸንፈው "ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣውን ቃል ሁሉ" በማሰብ ነው።ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃልም፦
የመጀመሪያው በነፍስ የተራቡትን የሚያጠግብ የቅዱስ ወንጌል ትምህርት ነው።ጌታችን በቅዱስ ወንጌሉ "ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት ወይም ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ነፍስ ከመብል ሰውነትስ ከልብስ አይበልጥምን?" በማለት አስተምሯል (ማቴ 6:25) እኔን የምትመስልን ነፍስ ካለመኖር ፈጥሬ ከሰጠኋችሁ ለጥቂት ጊዜ ነፍሳችሁ ከሥጋ ጋር ተዋሕዳ የምትቆይበትን መብል እንዴት እነሣችኋለሁ?፤ሥጋን ከአራቱ ባሕርያት ፈጥሬ ከሰጠኋችሁ ሥጋችሁ የሚለብሰውን አላቂ ልብስ እንዴት እነሣችኋለሁ? ማለቱ ነው።ይህም ብቻ አይደለም ለሰውነታችሁ ቤዛ የሚሆን ቅዱስ ሥጋዬን ክቡር ደሜን ከሰጣኋችሁ ፤ በመንግሥተ ሰማያትም የብርሃን ልብስን ካዘጋጀሁላችሁ ለሥጋችሁ የሚሆን መብልና ልብስን እንዴት እነሣችኋለሁ? ማለቱ ነው። እውነት ነው እጅግ ትልቁን የሰጠንን አምላክ በጥቂቱ የምንጠረጥረው ብዙዎች ነን።የጌታችን ተወዳጁ የሚሆን ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስም "ዓለምንና በዓለም ያለውን አትውደዱ፤ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት..." በማለት በስስት እንዳንሸነፍ መክሮናል።(1ኛ ዮሐ 2:15)
ስስትን "ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል" (ጌታችን ስለጾምና ምጽዋት ባስተማራት ትምህርት) ድል እናደርገዋለን ። " ስትጦሙም፥ እንደ ግብዞች አትጠውልጉ፤ ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ ፊታቸውን ያጠፋሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።አንተ ግን ስትጦም፥ በስውር ላለው አባትህ እንጂ እንደ ጦመኛ ለሰዎች እንዳትታይ ራስህን ተቀባ ፊትህንም ታጠብ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።"(ማቴ 6:16) እኛ ያልሳሳንለትን መብልንና ልብስንም ለሌላቸው መስጠት አለብን።በዚህም ጾም ከምጽዋት ጋር ትተባበራለች።
"ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል" ተአምር ነው።ስለዚህ ሰው በእግዚአብሔር ተአምር ጭምር እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም።ጌታችን በዘመነ ኤልያስ በነቢዩ ኤልያስ አድሮ በሰራፕታ ለነበረችው ባልቴት ጥቂቱን ዘይትና እፍኙን ዱቄት እንዳበረከተ እንዲሁ በዘመነ ሐዲስም ሁለት ዓሦችንና አምስት እንጀራዎችን አበርክቶ በተአምር አምስት ሺ ገበያ ሕዝብ አጥግቧል(1ኛ ነገ 17:7-17)።ራሱ ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስም የኖረው በእግዚአብሔር ተአምር ነው።"የእግዚአብሔርም ቃል እንዲህ ሲል ለእርሱ መጣለት።ከዚህ ተነሥተህ ወደ ምሥራቅ ሂድ፥ በዮርዳኖስም ትይዩ ባለው በኮራት ፈፋ ውስጥ ተሸሸግ።ከወንዙም ትጠጣለህ፥ ቍራዎችም በዚያ ይመግቡህ ዘንድ አዝዣለሁ። ሄደም እንደ እግዚአብሔር ቃልም አደረገ። ሄዶም በዮርዳኖስ ትይዩ ባለው በኮራት ፈፋ ውስጥ ተቀመጠ። ቍራዎቹ በየጥዋትና በየማታው እንጀራና ሥጋ ያመጡለት ነበር፤ ከወንዙም
ይጠጣ ነበር።(1ኛ ነገ 17:2-6) በጥቂት ብቻ በእግዚአብሔር ተአምር የኖሩ ቅዱሳን ብዙ ናቸው።በተለይም ርእሰ ባሕታውያን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ናቸው።562 ዓመት ሙሉ የእናታቸውን ጡት ጨምሮ ያለ ምግብ ፣ ያለ ልብስና ያለ መጠለያ በጾምና በጸሎት ያውም ከብዙ ሺ ስግደቶችና ተጋድሎዎች ጋር ተጸምዶ መኖር ያልተደነቀ ምን ይደነቃል!?ይኸውም የሆነው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል (በተአምር) ነው እንጂ በሌላ አይደለም።እግዚአብሔር "ይሁን" ያለው ይሆናል፤"ይሁን" ያላለውም አይሆንምና።በተፈጥሮ ለሰው ምግብ እንዲያስፈልገው ያደረገ አምላክ እንዳያስፈልገውም ማድረግ ይችላል።አሁንም ቢሆን በጥቂት ብቻ በበረከቱ የሚያኖራቸው ደጋግ ክርስቲያኖች ሞልተዋል።
"ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል" አካላዊ ቃል ወልደ አብ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።ስለዚህ በእርሱ በማመን በሃይማኖት በር ገብተን፤በቀጠነችው መንገድ በፈቃደ ነፍስ ተጉዘን፤ሕይወት የሆነው እርሱ ጋር ደርሰን በሕይወት እንኖራለን።ይህንን ሐሳብ ራሱ አምላካችን እንዲህ ሲል ገልጦታል።"በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።" (ማቴ 7:13) ስለዚህ ሰው ጠባብ በር በተባለው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ አምላክነትና የዘለዓለም ሕይወትነት (1ኛ ዮሐ 5:20) አምኖ ፤ በቀጠነው መንገድ በእግዚአብሔር ፈቃድ ተጉዞ ፤ የአካላዊ ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብሎ፤ራሱ ሕይወት የሆነው እግዚአብሔር ጋር ይደርሳል።መነሻውም መገስገሻውም መዳረሻውም እውነተኛ አምላኩ ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል ማለት ነው።እግዚአብሔር በቸርነቱ ጾሙን ስስትን ድል የምንነሣበት ያድርግልን!!!
መጋቢት 2/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
"ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል" አካላዊ ቃል ወልደ አብ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።ስለዚህ በእርሱ በማመን በሃይማኖት በር ገብተን፤በቀጠነችው መንገድ በፈቃደ ነፍስ ተጉዘን፤ሕይወት የሆነው እርሱ ጋር ደርሰን በሕይወት እንኖራለን።ይህንን ሐሳብ ራሱ አምላካችን እንዲህ ሲል ገልጦታል።"በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።" (ማቴ 7:13) ስለዚህ ሰው ጠባብ በር በተባለው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ አምላክነትና የዘለዓለም ሕይወትነት (1ኛ ዮሐ 5:20) አምኖ ፤ በቀጠነው መንገድ በእግዚአብሔር ፈቃድ ተጉዞ ፤ የአካላዊ ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብሎ፤ራሱ ሕይወት የሆነው እግዚአብሔር ጋር ይደርሳል።መነሻውም መገስገሻውም መዳረሻውም እውነተኛ አምላኩ ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል ማለት ነው።እግዚአብሔር በቸርነቱ ጾሙን ስስትን ድል የምንነሣበት ያድርግልን!!!
መጋቢት 2/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
http://www.youtube.com/@ZemariDawitkibru2405 Youtube channel - Zemari Dawit kibru | Official ዘማሪ ዳዊት ክብሩ