ዐውደ ምሕረት
Photo
ከወደቁ አይቀር .....#ለጽዮን
____________________
አንዳንድ ውድቀቶች ካለ አስፍላጊ አቋቋሞች በእጅጉ የተሻሉ ናቸው ። ለምሳሌ ከሐውልቱ እንደምናየው ለጽዮን መውደቅ በእውነቱ ዋጋ ያለውና የተሻለ አወዳደቅ ነው::
#ይህ በመጠኑና በውበቱ ከፍ ያለው ሃውልት አሁን ሳይወድቅ ቆሞ ካለውና በቅርቡ ከሮም ከመጣው ዕድሜ ይሁን በሰው ሀገር ያለ ቦታው መቆሙ የሞራል መላሸቅ ያስከተለበት የሚመስለሁ እንደ አዛውንት ጎብጦ በመደገፊያ በግድ ከቆመው ሐውልት በተለየ መልኩ በፊት ለፊቱ ወድቆ ይታያል::
ይህ የአክሱም ሐውልት ከመሐመድ ግራኝ ወራራ በኋላ የተነሳችው ሴቷ ግራኝ ዮዲት ጉዲት ካስከተለችው ጥፋቶች መካከል የጥፉቷን ግንባር ቀደም ገፈት ቀማሽ የሆነ ታሪካዊ የሀገር ቅርስ ነው :: ዮዲት በክርስቲያንኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ባደረባት የተሳሳት ጥላቻ ኃያሌ የጭካኔ ተግባራትን በክርስቲያኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ያስከተለች የታሪክ ጠባሳ ነች ::
#ከበዙ ጥፉቶች በኃላ ወደ እዚህ ወደ አክሱም ሐውልት መቆሚያ አካባቢ ስትደርስም ጭፍሮቿ እንደለመዱት የእክሱምን ሐውልቶች ይጥሏቸውና ይሰባብሯቸው ዘንድ ተራኮቱ ዮዲትም ሁሉንም ሐውልቶች አትጣሏቸው አንዱንና ትልቁን ለዐይንም የሚማርከውን ሐውልት ብቻ ጣሉት ሌሎቹን ግን እንዳትነኩ ስትል ትዕዛዝ አስተላለፈች ጭፍሮቿም ለምን? ሲሉ ጠየቁ
በሌሎች ቦታዎች እዳደረግን ሁሉንም ብንሰባብርና ብናወድማቸው መጪው ትውልድ ሲያቸው አንድ ጊዜ ተበሳጭቶ ብስጭቱን ይተወዋል የሚያምረውን ና ተለቅ የሚለውን ሃውልት ብቻ ብንጥለውና ሌላው ብንተውለት ግን ባየውና በሰማው ቁጥር ይህ ትልቁኮ ባይወድቅ ከነዚኞቹ በላይ ውብ የሀገር ቅርስ ሆኖ ይታይ ነበር እያለ ዘላለም ዓለሙን እየተቃጠለ ሲብሰለሰል ይኖራል ገባችሁ ስትልም አምቧረቀችባቸው::
#ሐውልቱ ግን ለትውልዱ ቁጭት ሳይሆን ትምህር ይሆን ዘንድ ወደ ጽዮን ወደቀ ተንበርከኮም ሰገደላት ። የጌታዬ እናት በፊትሽ እቆም ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እያለም ተሳለማት ሉቃ1÷43። ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ ልብ ያለውም ልብ ያድርግ "በፈሊጥ ካልገባው በፍልጥ " እንዲሉ ። ሰው ሁለት ጊዜ ይማራል ይላሉ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን አንድ በሣር " ሀ " ብሎ ካልሆነም በአሳር " ዋ "ብሎ ። ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ብራና ዳምጠው ቀለም በጥብጠው በሣር ስግደት እንደሚገባት ሲያስተምሩን ካልገባን በአሳር ጎንበስ ማለታችን አይቀርምና ከአሳሩ በፊት በሳሩ ተማሩ እንላለን።
“ #የአስጨናቂዎችሽም_ልጆች_አንገታቸውን_ደፍተው_ወደ_አንቺ_ይመጣሉ ፥ የናቁሽም ሁሉ #ወደ_እግርሽ_ጫማ ይሰግዳሉ፤ #የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል #ቅዱስ_የሆንሽ_ጽዮን ይሉሻል።”
#ኢሳ 60፥14
አ.አ ኢትዮጵያ
ተርቢኖስ ዘተክለ ኤል
ኅዳር 21/2013ዓ.ም የተከተበ
____________________
አንዳንድ ውድቀቶች ካለ አስፍላጊ አቋቋሞች በእጅጉ የተሻሉ ናቸው ። ለምሳሌ ከሐውልቱ እንደምናየው ለጽዮን መውደቅ በእውነቱ ዋጋ ያለውና የተሻለ አወዳደቅ ነው::
#ይህ በመጠኑና በውበቱ ከፍ ያለው ሃውልት አሁን ሳይወድቅ ቆሞ ካለውና በቅርቡ ከሮም ከመጣው ዕድሜ ይሁን በሰው ሀገር ያለ ቦታው መቆሙ የሞራል መላሸቅ ያስከተለበት የሚመስለሁ እንደ አዛውንት ጎብጦ በመደገፊያ በግድ ከቆመው ሐውልት በተለየ መልኩ በፊት ለፊቱ ወድቆ ይታያል::
ይህ የአክሱም ሐውልት ከመሐመድ ግራኝ ወራራ በኋላ የተነሳችው ሴቷ ግራኝ ዮዲት ጉዲት ካስከተለችው ጥፋቶች መካከል የጥፉቷን ግንባር ቀደም ገፈት ቀማሽ የሆነ ታሪካዊ የሀገር ቅርስ ነው :: ዮዲት በክርስቲያንኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ባደረባት የተሳሳት ጥላቻ ኃያሌ የጭካኔ ተግባራትን በክርስቲያኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ያስከተለች የታሪክ ጠባሳ ነች ::
#ከበዙ ጥፉቶች በኃላ ወደ እዚህ ወደ አክሱም ሐውልት መቆሚያ አካባቢ ስትደርስም ጭፍሮቿ እንደለመዱት የእክሱምን ሐውልቶች ይጥሏቸውና ይሰባብሯቸው ዘንድ ተራኮቱ ዮዲትም ሁሉንም ሐውልቶች አትጣሏቸው አንዱንና ትልቁን ለዐይንም የሚማርከውን ሐውልት ብቻ ጣሉት ሌሎቹን ግን እንዳትነኩ ስትል ትዕዛዝ አስተላለፈች ጭፍሮቿም ለምን? ሲሉ ጠየቁ
በሌሎች ቦታዎች እዳደረግን ሁሉንም ብንሰባብርና ብናወድማቸው መጪው ትውልድ ሲያቸው አንድ ጊዜ ተበሳጭቶ ብስጭቱን ይተወዋል የሚያምረውን ና ተለቅ የሚለውን ሃውልት ብቻ ብንጥለውና ሌላው ብንተውለት ግን ባየውና በሰማው ቁጥር ይህ ትልቁኮ ባይወድቅ ከነዚኞቹ በላይ ውብ የሀገር ቅርስ ሆኖ ይታይ ነበር እያለ ዘላለም ዓለሙን እየተቃጠለ ሲብሰለሰል ይኖራል ገባችሁ ስትልም አምቧረቀችባቸው::
#ሐውልቱ ግን ለትውልዱ ቁጭት ሳይሆን ትምህር ይሆን ዘንድ ወደ ጽዮን ወደቀ ተንበርከኮም ሰገደላት ። የጌታዬ እናት በፊትሽ እቆም ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እያለም ተሳለማት ሉቃ1÷43። ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ ልብ ያለውም ልብ ያድርግ "በፈሊጥ ካልገባው በፍልጥ " እንዲሉ ። ሰው ሁለት ጊዜ ይማራል ይላሉ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን አንድ በሣር " ሀ " ብሎ ካልሆነም በአሳር " ዋ "ብሎ ። ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ብራና ዳምጠው ቀለም በጥብጠው በሣር ስግደት እንደሚገባት ሲያስተምሩን ካልገባን በአሳር ጎንበስ ማለታችን አይቀርምና ከአሳሩ በፊት በሳሩ ተማሩ እንላለን።
“ #የአስጨናቂዎችሽም_ልጆች_አንገታቸውን_ደፍተው_ወደ_አንቺ_ይመጣሉ ፥ የናቁሽም ሁሉ #ወደ_እግርሽ_ጫማ ይሰግዳሉ፤ #የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል #ቅዱስ_የሆንሽ_ጽዮን ይሉሻል።”
#ኢሳ 60፥14
አ.አ ኢትዮጵያ
ተርቢኖስ ዘተክለ ኤል
ኅዳር 21/2013ዓ.ም የተከተበ
ዐውደ ምሕረት
Photo
#ይህ_ጎልያድን የገደለ #ሐዲስ_ዳዊት ነው!
________________________________
#ገድለ_ጊዮርጊስ
#በተኵላና_በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ #አንበሳውንና_ዘንዶውን ትረግጣለህ። #በእኔ_ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ። #ይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤አድነዋለሁ አከብረውማለሁ። " #መዝ 90(91)÷13-15
ይህ #የእግዚአብሔር_ቃል ነው ፤ እንግዲህ #እግዚአብሔር_ያከበረውን ማን ያቃልለዋል? #ማንም!
________________________________
#ገድለ_ጊዮርጊስ
#በተኵላና_በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ #አንበሳውንና_ዘንዶውን ትረግጣለህ። #በእኔ_ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ። #ይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤አድነዋለሁ አከብረውማለሁ። " #መዝ 90(91)÷13-15
ይህ #የእግዚአብሔር_ቃል ነው ፤ እንግዲህ #እግዚአብሔር_ያከበረውን ማን ያቃልለዋል? #ማንም!
#ሐዲስ_ሱራፊ
_________
#ተክለ_ሃይማኖት
_____________
#ሱራፊ ማለት መልአክ፣ ከካህናተ ሰማይ አንዱ ማለት ነው፡፡ ሱራፌን፣ ሱራፌል፣ ሱራፌም
(በፅርዕ ሴራፊም፣ በዕብራይስጥ ስራፊም) ማለት የነገድ ስም፣ ልዑላን መላእክት፣
ሊቃናት፣ የሚያጥኑ፣ ካህናት፣ ቀሳውስት፣ ቀዳሾች ማለት ነው /ኪዳነ ወልድ ክፍሌ/ ከዚህ
ላይ ሱራፊ ነጠላ ቍጥርን ሲያመለክት፤ ሱራፌል ደግሞ ብዙ ቍጥርን ያመለክታል፡፡
ሱራፌል ለቅዱሳን በሰው አምሳል በመገለጣቸው ሽማግሌዎች ተብለው ተጠርተዋል /
ኢሳ.24፥23፤ መሳ.13፥2-25፤ /፡፡ በግእዝ ቋንቋ ደግሞ ካህናተ ሰማይ ይባላሉ፡፡ ካህናተ
ሰማይ ሱራፌል ቁጥራቸው 24 እንደሆነ ባለ እራዮ ዮሐን ጽፎልናል ይህ ግን 24ሰዓት ያለ
እረፍት የሚያመሰግኑ መሆናቸውን ለማመልከት የተጠቀመበት አገላለጽ ነው እንጂ
ቁጥራቸውስ 24ብቻ ሆኖ አይደለም ።
ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ ስማቸውን ጭምር
በመጥቀስ ለኻያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ሰላምታ አቅሮቦላቸዋል። በአብ መንበር ዙሪያ ላሉ
ለ24ቱ ሰማያውያን ካህናት ሰላምታ ይገባል፤ በእጆቻቸው ውስጥ ላለ ማዕጠንትም
ሰላምታ ይገባል፤ በራሶቻቸው ላይ ላሉ አክሊላትም ሰላምታ ይገባል፤ አካኤል፣ ፋኑኤል፣
ጋኑኤል፣ ታድኤል፣ እፍድኤል፣ ዘራኤል፣ ኤልኤል፣ ተዳኤል፣ ዮካኤል፣ ገርድኤል፣ ልፍድኤል፣
መርዋኤል፣ ኑራኤል፣ ክስልቱኤል፣ ኡራኤል፣ ባቱኤል፣ ሩአኤል፣ ሰላትኤል፣ ጣውርኤል፣
እምኑኤል፣ ፔላልኤል፣ታልዲኤል፣ ፐስልዱኤል፣ አሌቲኤል ለተባሉ ስሞቻቸውም ሰላምታ
ይገባል) በማለት አወድሷቸዋል (አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ተአምኆ ቅዱሳን ንባቡና
ትርጓሜው / መጋቢ ሐዲስ ሮዳስ እንደተረጎመው)
ዛሬ በዚህች መጠነኛ ጽሁፍ ኅዳር 24ቀን ከነዚህ ካህናተ ሰማይ ሱራፌል ጋር ተደምሮ
የሥላሴን መንበር ያጠነ አዲሱን ምድራዊ ሱራፊን ተክለ ሃይማኖት /ተክለ ኤልን /
እናስተዋውቃችዋለን። ካህናተ ሰማይ ሱራፌል ከዘር የተገኙ ምድራዊያን አይደለም ተክለ
ኤል ተክለ ሃይማኖት ግን ከሕግ ዘር የተገኘ ምድራዊ ሰው የሆነ ሐዲስ ሱራፊ ነው።
‹ተክል› ማለት ፍሬያማ ዕንጨት፣ ዛፍ፣ ቅመም፣ ቅጠላ ቅጠል፣፣ የሚሸተት፣ቢበሉት ጥጋብ
፣ቢያርፉበት ጥላ የሚሆን ገነታዊ ዕፅ፣ እንዲሁም ሕግ ሥርዓት ማለት ነው /
ማቴ.15፥13/፡፡
"ኤል" ማለት ደግሞ እግዚአብሔር ማለት ነው :: ስመ መላእክት ስመ እግዚአብሔርን ያዘሉ
በመሆናቸው የሁሉም ቅዱሳን መላእክ ስም "ኤል" የሚል መቀጽል አለው ለምሳሌ ከላይ
የጠቀስናቸው የሃያራቱን ካህናተ ሰማይ የሱራፌልን ስም መመልከት ይቻላል :- አካኤል፣
ፋኑኤል፣ ጋኑኤል ወ.ዘ.ተ ስለዚህ "ተክለ ኤል " ማለታችንም ይህ ሐዲስ ሱራፊ ስሙ
ከስማቸው ጭምር የሚገጥም መሆኑን ለመግለጥ ነው። የእግዚአብሔር ተክል ተክለ
እግዚአብሔር ማለታችን ነው :: ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ባስልዮስ ዘ ቄሳሪያ እኔስ እግዚአብሔር
ባልኩ ጊዜ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለቴ ነው ብሎ እንደተናገረ " ተክለ ኤል" ተክለ
እግዚአብሔር ሲባልም የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተክል የሚል ትርጉም ይሰጣል ።
# አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የተወለዱት በሸዋ ክፍለ ሀገር ዛሬ ኢቲሳ በመባል
በሚታወቀው ከከሰም ጅረት አካባቢ ባለ ቦታ በጥንቱ ፈጠጋር ቡልጋ በደብረ ጽላልሽ
አውራጃ ዞረሬ በተባለው ሥፍራ በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ዘርዐ ዮሐንስ
ወይም ጸጋ ዘአብ (የአብ ሥጦታ) ከሚባል ካህን እና ሣራ ወይም እግዚእ ኅረያ
(እግዚአብሔር የመረጣት)በመባል ከምትታወቅ ደጋግ ከሆኑ ባልና ሚስቶች በመላእክ
አብሳሪነት መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ገደማ ነው።
ወላጆቻቸውም ፍስሐ ጺዮን ።(የፂዮን ደስታዋ)ብለው ሰየሟቸው፡፡ ጻድቁ በተወለዱ
በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹ አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ
አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› በማለት የፈጠራቸውን አምላክ አመስግነዋል። ይህን ጊዜ
እናታቸው እግዚ ኀረያም በመገረም ሆና " ይህ ሥራ የአባት ነው ላንተ የሚገባህ ጡት
መጥባት ነው" ብላ ለህጻኑ ጡቷን አጎረሰችሁ ፡፡ ይህም የህጻኑ ሁኔታ መላእካዊ ግብሩን
ገና በህጻንነት የገለጠ ነበር ቀን ከለሊት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ ማመስገን የመላእክት
መገለጫ ነውና ኢሳ 6÷6 ። ካህኑ ፀጋ ዘአብ የወቅቱን የቤተ ክርሰቲያን አገልግሎታቸውን
ጨርሰው ወደ ቤታቸው ሲገቡ ሚስታቸው እግዚእ ኀረያ በመገረም ሆና የሦስት ቀን
ልጃቸው ፍስሐ ፂዮን እንዴት ባለ ምስጋና ፈጣሪያቸውን እንዳመሰገነ ነገረቻቸው ጸጋ
ዘአብም ህጻኑን ተቀብለው ታቅፈው እየሳሙ ልጄ ሺህ ዘመን ኑርልኝ እንዲ እያልክ በቤተ
መቅደስ ስትቀድስ ዐይህ ዘንድ እመኛለው አሉ።ከዚህም በኃላ ፍስሐ ጺዮን በሰውና
በእግዚአብሔር ፊት በጥበብና በሞገስ አደገ።
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ከአብሮ አደግ ጓደኞቹ ጋር በዱር ፈረስ ሲጋልብ
ጦር ሲሰብቅ ተገናኝቶት ፍስሐ ጺዮን የሚለውን ስሙን በፈጣሪው ትዛዝ መሠረት ለውጦ
ከእንግዲህ ወዲህ "ተክለሃይማኖት" እየተባልክ ተጠራ እንጂ ስም ፍስሐ ጺዮን አይሁን
አላቸው አበው ስምን መላእክ ያወጣዋል እንዲሉ ፡፡ አያይዞም ፈረስ መጋለብ ጦር መስበቅ
ቀስት መወርወር እንሰሳት ማደንን ተው ከእንግዲህ ወዲህ መስቀል ጨብጥ በወንጌል
ስበክ ከአፍህ በሚወረወር በቃለ እግዚአብሔር መረብነት ሰው አድን አለው ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስም በመላእኩ ክንፍ ላይ ተገልጦ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጌሃለሁ ብሎ
በሐዋርያት ሾመት ሐዋርያ አድርጎ ሾመው። ጓደኞቹም ከያሉበት ተሰብስበው ወደ ተክለ
ሃይማኖት ቀረቡ ከፊቱ የሚወጣው ብርሃን ግን አላስተያይ አላቸው ስለዚህ ፊትህን ማየት
አቃተን ተሸፋፈንልን ሲሉ ተማጠኑት። ሙሴ ከሲና ተራራ ከእግዚአብሔር ጋር ተነጋግሮ
በወረደ ጊዜ አሮንና የእስራኤል ልጆች ሁሉ ሙሴ ሆይ ከፊትህ የሚወጣው ብርሃን
አላስተያይ ብሎናልና እባክህ ፊትህን ሸፍንልኝ እንዳሉት ዘጽ 34÷29_35
# ጻድቁ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው ዲቊናን፤ በ22 ዓመታቸው ደግሞ ቅስናን ከግብፃዊው
ጳጳስ ከአባ ጌርሎስ ወይም (ከአባ ቄርሎስ) ዘንድ ተቀብለዋል፡፡ ሐዋርያዊ ተግባርንም
በከተታ እና በፈጠጋር (በጽላልሽና በአካባቢዋ፣በዳሞት በምድረ ወላይታ፣በአምሓራና በሸዋ
በሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ፣ በኣድያማተ ትግራይ፣በገዳመ ዋሊ (ዋልድባ) ፣በገነተ
ማርያም ላስታ በደብረ ዘመዶ ማርያም ገዳም፣ በኤርትራ ገዳማት ፣በደብረ ዳሞ አቡነ
አረጋዊ ገዳም ወዘተ በአገሪቱ ወንጌል ባልተዳረሰበት ቦታ ሁሉ እየተዘዋወሩ በመላዋ
ኢትዮጵያ ወንጌልን አስፍተዋል።
ጻድቁ አባታችን ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣
እንደ ገበሬ ታጥቀው፣ ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በብሕትውና
በመኖራቸው፤ እርሳቸው በአሚነ ሥላሴ ጸንተው ሌሎችንም እንዲጸኑና እንዲያምኑ
በማድረጋቸው፤ እንደዚሁም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ
እየተዘዋወሩ በመስበክ በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን
በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ዛሬም በአጸደ ነፍስ ሆነው የሚፈውሱ
_________
#ተክለ_ሃይማኖት
_____________
#ሱራፊ ማለት መልአክ፣ ከካህናተ ሰማይ አንዱ ማለት ነው፡፡ ሱራፌን፣ ሱራፌል፣ ሱራፌም
(በፅርዕ ሴራፊም፣ በዕብራይስጥ ስራፊም) ማለት የነገድ ስም፣ ልዑላን መላእክት፣
ሊቃናት፣ የሚያጥኑ፣ ካህናት፣ ቀሳውስት፣ ቀዳሾች ማለት ነው /ኪዳነ ወልድ ክፍሌ/ ከዚህ
ላይ ሱራፊ ነጠላ ቍጥርን ሲያመለክት፤ ሱራፌል ደግሞ ብዙ ቍጥርን ያመለክታል፡፡
ሱራፌል ለቅዱሳን በሰው አምሳል በመገለጣቸው ሽማግሌዎች ተብለው ተጠርተዋል /
ኢሳ.24፥23፤ መሳ.13፥2-25፤ /፡፡ በግእዝ ቋንቋ ደግሞ ካህናተ ሰማይ ይባላሉ፡፡ ካህናተ
ሰማይ ሱራፌል ቁጥራቸው 24 እንደሆነ ባለ እራዮ ዮሐን ጽፎልናል ይህ ግን 24ሰዓት ያለ
እረፍት የሚያመሰግኑ መሆናቸውን ለማመልከት የተጠቀመበት አገላለጽ ነው እንጂ
ቁጥራቸውስ 24ብቻ ሆኖ አይደለም ።
ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ ስማቸውን ጭምር
በመጥቀስ ለኻያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ሰላምታ አቅሮቦላቸዋል። በአብ መንበር ዙሪያ ላሉ
ለ24ቱ ሰማያውያን ካህናት ሰላምታ ይገባል፤ በእጆቻቸው ውስጥ ላለ ማዕጠንትም
ሰላምታ ይገባል፤ በራሶቻቸው ላይ ላሉ አክሊላትም ሰላምታ ይገባል፤ አካኤል፣ ፋኑኤል፣
ጋኑኤል፣ ታድኤል፣ እፍድኤል፣ ዘራኤል፣ ኤልኤል፣ ተዳኤል፣ ዮካኤል፣ ገርድኤል፣ ልፍድኤል፣
መርዋኤል፣ ኑራኤል፣ ክስልቱኤል፣ ኡራኤል፣ ባቱኤል፣ ሩአኤል፣ ሰላትኤል፣ ጣውርኤል፣
እምኑኤል፣ ፔላልኤል፣ታልዲኤል፣ ፐስልዱኤል፣ አሌቲኤል ለተባሉ ስሞቻቸውም ሰላምታ
ይገባል) በማለት አወድሷቸዋል (አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ተአምኆ ቅዱሳን ንባቡና
ትርጓሜው / መጋቢ ሐዲስ ሮዳስ እንደተረጎመው)
ዛሬ በዚህች መጠነኛ ጽሁፍ ኅዳር 24ቀን ከነዚህ ካህናተ ሰማይ ሱራፌል ጋር ተደምሮ
የሥላሴን መንበር ያጠነ አዲሱን ምድራዊ ሱራፊን ተክለ ሃይማኖት /ተክለ ኤልን /
እናስተዋውቃችዋለን። ካህናተ ሰማይ ሱራፌል ከዘር የተገኙ ምድራዊያን አይደለም ተክለ
ኤል ተክለ ሃይማኖት ግን ከሕግ ዘር የተገኘ ምድራዊ ሰው የሆነ ሐዲስ ሱራፊ ነው።
‹ተክል› ማለት ፍሬያማ ዕንጨት፣ ዛፍ፣ ቅመም፣ ቅጠላ ቅጠል፣፣ የሚሸተት፣ቢበሉት ጥጋብ
፣ቢያርፉበት ጥላ የሚሆን ገነታዊ ዕፅ፣ እንዲሁም ሕግ ሥርዓት ማለት ነው /
ማቴ.15፥13/፡፡
"ኤል" ማለት ደግሞ እግዚአብሔር ማለት ነው :: ስመ መላእክት ስመ እግዚአብሔርን ያዘሉ
በመሆናቸው የሁሉም ቅዱሳን መላእክ ስም "ኤል" የሚል መቀጽል አለው ለምሳሌ ከላይ
የጠቀስናቸው የሃያራቱን ካህናተ ሰማይ የሱራፌልን ስም መመልከት ይቻላል :- አካኤል፣
ፋኑኤል፣ ጋኑኤል ወ.ዘ.ተ ስለዚህ "ተክለ ኤል " ማለታችንም ይህ ሐዲስ ሱራፊ ስሙ
ከስማቸው ጭምር የሚገጥም መሆኑን ለመግለጥ ነው። የእግዚአብሔር ተክል ተክለ
እግዚአብሔር ማለታችን ነው :: ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ባስልዮስ ዘ ቄሳሪያ እኔስ እግዚአብሔር
ባልኩ ጊዜ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለቴ ነው ብሎ እንደተናገረ " ተክለ ኤል" ተክለ
እግዚአብሔር ሲባልም የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተክል የሚል ትርጉም ይሰጣል ።
# አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የተወለዱት በሸዋ ክፍለ ሀገር ዛሬ ኢቲሳ በመባል
በሚታወቀው ከከሰም ጅረት አካባቢ ባለ ቦታ በጥንቱ ፈጠጋር ቡልጋ በደብረ ጽላልሽ
አውራጃ ዞረሬ በተባለው ሥፍራ በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ዘርዐ ዮሐንስ
ወይም ጸጋ ዘአብ (የአብ ሥጦታ) ከሚባል ካህን እና ሣራ ወይም እግዚእ ኅረያ
(እግዚአብሔር የመረጣት)በመባል ከምትታወቅ ደጋግ ከሆኑ ባልና ሚስቶች በመላእክ
አብሳሪነት መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ገደማ ነው።
ወላጆቻቸውም ፍስሐ ጺዮን ።(የፂዮን ደስታዋ)ብለው ሰየሟቸው፡፡ ጻድቁ በተወለዱ
በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹ አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ
አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› በማለት የፈጠራቸውን አምላክ አመስግነዋል። ይህን ጊዜ
እናታቸው እግዚ ኀረያም በመገረም ሆና " ይህ ሥራ የአባት ነው ላንተ የሚገባህ ጡት
መጥባት ነው" ብላ ለህጻኑ ጡቷን አጎረሰችሁ ፡፡ ይህም የህጻኑ ሁኔታ መላእካዊ ግብሩን
ገና በህጻንነት የገለጠ ነበር ቀን ከለሊት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ ማመስገን የመላእክት
መገለጫ ነውና ኢሳ 6÷6 ። ካህኑ ፀጋ ዘአብ የወቅቱን የቤተ ክርሰቲያን አገልግሎታቸውን
ጨርሰው ወደ ቤታቸው ሲገቡ ሚስታቸው እግዚእ ኀረያ በመገረም ሆና የሦስት ቀን
ልጃቸው ፍስሐ ፂዮን እንዴት ባለ ምስጋና ፈጣሪያቸውን እንዳመሰገነ ነገረቻቸው ጸጋ
ዘአብም ህጻኑን ተቀብለው ታቅፈው እየሳሙ ልጄ ሺህ ዘመን ኑርልኝ እንዲ እያልክ በቤተ
መቅደስ ስትቀድስ ዐይህ ዘንድ እመኛለው አሉ።ከዚህም በኃላ ፍስሐ ጺዮን በሰውና
በእግዚአብሔር ፊት በጥበብና በሞገስ አደገ።
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ከአብሮ አደግ ጓደኞቹ ጋር በዱር ፈረስ ሲጋልብ
ጦር ሲሰብቅ ተገናኝቶት ፍስሐ ጺዮን የሚለውን ስሙን በፈጣሪው ትዛዝ መሠረት ለውጦ
ከእንግዲህ ወዲህ "ተክለሃይማኖት" እየተባልክ ተጠራ እንጂ ስም ፍስሐ ጺዮን አይሁን
አላቸው አበው ስምን መላእክ ያወጣዋል እንዲሉ ፡፡ አያይዞም ፈረስ መጋለብ ጦር መስበቅ
ቀስት መወርወር እንሰሳት ማደንን ተው ከእንግዲህ ወዲህ መስቀል ጨብጥ በወንጌል
ስበክ ከአፍህ በሚወረወር በቃለ እግዚአብሔር መረብነት ሰው አድን አለው ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስም በመላእኩ ክንፍ ላይ ተገልጦ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጌሃለሁ ብሎ
በሐዋርያት ሾመት ሐዋርያ አድርጎ ሾመው። ጓደኞቹም ከያሉበት ተሰብስበው ወደ ተክለ
ሃይማኖት ቀረቡ ከፊቱ የሚወጣው ብርሃን ግን አላስተያይ አላቸው ስለዚህ ፊትህን ማየት
አቃተን ተሸፋፈንልን ሲሉ ተማጠኑት። ሙሴ ከሲና ተራራ ከእግዚአብሔር ጋር ተነጋግሮ
በወረደ ጊዜ አሮንና የእስራኤል ልጆች ሁሉ ሙሴ ሆይ ከፊትህ የሚወጣው ብርሃን
አላስተያይ ብሎናልና እባክህ ፊትህን ሸፍንልኝ እንዳሉት ዘጽ 34÷29_35
# ጻድቁ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው ዲቊናን፤ በ22 ዓመታቸው ደግሞ ቅስናን ከግብፃዊው
ጳጳስ ከአባ ጌርሎስ ወይም (ከአባ ቄርሎስ) ዘንድ ተቀብለዋል፡፡ ሐዋርያዊ ተግባርንም
በከተታ እና በፈጠጋር (በጽላልሽና በአካባቢዋ፣በዳሞት በምድረ ወላይታ፣በአምሓራና በሸዋ
በሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ፣ በኣድያማተ ትግራይ፣በገዳመ ዋሊ (ዋልድባ) ፣በገነተ
ማርያም ላስታ በደብረ ዘመዶ ማርያም ገዳም፣ በኤርትራ ገዳማት ፣በደብረ ዳሞ አቡነ
አረጋዊ ገዳም ወዘተ በአገሪቱ ወንጌል ባልተዳረሰበት ቦታ ሁሉ እየተዘዋወሩ በመላዋ
ኢትዮጵያ ወንጌልን አስፍተዋል።
ጻድቁ አባታችን ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣
እንደ ገበሬ ታጥቀው፣ ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በብሕትውና
በመኖራቸው፤ እርሳቸው በአሚነ ሥላሴ ጸንተው ሌሎችንም እንዲጸኑና እንዲያምኑ
በማድረጋቸው፤ እንደዚሁም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ
እየተዘዋወሩ በመስበክ በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን
በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ዛሬም በአጸደ ነፍስ ሆነው የሚፈውሱ
ሐዲስ ሐዋርያ ሐዲስ ሱራፊ ናቸው።
በየ ደረሱበት ሥፍራ ሁሉ ከሥራቸው ጽናት ከተአምራታቸው ብዛት የተነሳ አንተ ሰውነህን
ወይስ መላእክ ነህን ንገረን ይሏቸው ነበር። እርሳቸውም ከንቱ ውዳሴን ነፍሳቸው አጥብቃ
ትጸየፈው ነበርና አባቶቼ እንደ እናንተ ምድራዊ ሰው እንጂ መላእክ እሆን ዘንድ እኔ ማነኝ?
እያሉ የሚያቃጥል የትዕትናን እንባ ከዐይኖቻቸው ይፈስ ነበር ። “እግዚአብሔር
ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ” 1ጴጥ 5÷ 5 እንደተባለ ይህንን
ይህን የትዕትና ሥራ ሲከተል ትዕትናው ፀጋውን አብዝታለት ያኔ በተወለደ በሦስተኛው ቀን
ሥላሴን በአንድነት ሦስትነቱ በማመስኑ ተደንቆ ልጄ ሺህ ዘመን ኑርልኝ እንዲህ እያልክ
በቤተ መቅደስ ስትቀድስ አይህ ዘንድ እመኛለው ብሎ የመረቀው የአባቱ ምርቃት ደርሳለት
ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ ድንገት ነጥቆ ወስዶ
ከፀሐይ ይልቅ ወደ ምታበራ ሀገር አደረሰው ።
# አራቱ እንስሶችና ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት ወደቁ፥ እያንዳንዳቸውም በገናንና
የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያዙ አባታችንም ደግሞ እንደነርሱ ያዘ
በምድር ብቻ ያይደለ በሰማያዊ መቅደስ ጭምር ገብቶ ከሱራፌል ጋር ሱራፊ ሆኖ ክንፉን
ከክንፋቸው ገጥሞ ምስጋናው ከምስጋናቸው አንድ ሆኖ በወርቁን ማዕጥንት ይሰልስ
ይቀድስ ዘንድ ጀመረ ራእይ 5፥8 የቅዱስ ጳውሎስን ነገሩን ትምህርቱን የተከተለ ብጹህ
አባታችን ተክለ ሃይማኖት ወደ ሰማይ በመመንጠቅም ተከተለው፡፡ በመከራው መስሎታልና
በክብሩ መሰለው “ ወደ ገነት ተነጠቀ ሰውም ሊናገረው የማይገባወን የማይነገረውንም
ቃል ሰማ ተብሎ እንደ ተጻፈ 2ቆሮ 12÷4 ስለዚህ በገድሉ መጻሕፍ እንዲ ሲል ሰማነው
"ተክለ ሃይማኖት ክፍልህ ከሃያ አራቱ ካህናቶቼ ጋር ይሁን የሚል ቃል ከዙፋኑ ውስጥ ወጣ
የወርቅ ጽና አምጥተው ሰጡኝና ከእነርሱ ጋር በአንንድነት አጠንኩ ምስጋዬ ከምስጋናቸው
ጋር ልብሴም እንደ ልብሳቸው ሆነ ፈጣሪዬንም በሦስትነቱ ተገልጦ አየሁት" ገ/ተ
ሃይማኖት ዘአርብ 43÷ 29
# የሐዲሱ_ሱራፊ_የአባታች_የቅዱስ_ተክለ_ሃይማኖት እረድኤትና በረከታቸው በአገራችን
በኢትዮጵያና በሕዝበ ክርስቲያኖች ሁሉ ላይ ጸንቶ ይኑር ! በወርቅ ጥናውም ዘወትር እያጠነ
መዓዛ ክርስቶስን የምንሸት እውነተኛ ክርስቲያኖች አድርጎ የመንግሥቱ ወራሾች የስሙ
ቀዳሾች እንድንሆን ያድርገን ለዘላለሙ አሜን!
............. ይቆየን............
ኀዳር 24/2013ዓ.ም
በየ ደረሱበት ሥፍራ ሁሉ ከሥራቸው ጽናት ከተአምራታቸው ብዛት የተነሳ አንተ ሰውነህን
ወይስ መላእክ ነህን ንገረን ይሏቸው ነበር። እርሳቸውም ከንቱ ውዳሴን ነፍሳቸው አጥብቃ
ትጸየፈው ነበርና አባቶቼ እንደ እናንተ ምድራዊ ሰው እንጂ መላእክ እሆን ዘንድ እኔ ማነኝ?
እያሉ የሚያቃጥል የትዕትናን እንባ ከዐይኖቻቸው ይፈስ ነበር ። “እግዚአብሔር
ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ” 1ጴጥ 5÷ 5 እንደተባለ ይህንን
ይህን የትዕትና ሥራ ሲከተል ትዕትናው ፀጋውን አብዝታለት ያኔ በተወለደ በሦስተኛው ቀን
ሥላሴን በአንድነት ሦስትነቱ በማመስኑ ተደንቆ ልጄ ሺህ ዘመን ኑርልኝ እንዲህ እያልክ
በቤተ መቅደስ ስትቀድስ አይህ ዘንድ እመኛለው ብሎ የመረቀው የአባቱ ምርቃት ደርሳለት
ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ ድንገት ነጥቆ ወስዶ
ከፀሐይ ይልቅ ወደ ምታበራ ሀገር አደረሰው ።
# አራቱ እንስሶችና ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት ወደቁ፥ እያንዳንዳቸውም በገናንና
የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያዙ አባታችንም ደግሞ እንደነርሱ ያዘ
በምድር ብቻ ያይደለ በሰማያዊ መቅደስ ጭምር ገብቶ ከሱራፌል ጋር ሱራፊ ሆኖ ክንፉን
ከክንፋቸው ገጥሞ ምስጋናው ከምስጋናቸው አንድ ሆኖ በወርቁን ማዕጥንት ይሰልስ
ይቀድስ ዘንድ ጀመረ ራእይ 5፥8 የቅዱስ ጳውሎስን ነገሩን ትምህርቱን የተከተለ ብጹህ
አባታችን ተክለ ሃይማኖት ወደ ሰማይ በመመንጠቅም ተከተለው፡፡ በመከራው መስሎታልና
በክብሩ መሰለው “ ወደ ገነት ተነጠቀ ሰውም ሊናገረው የማይገባወን የማይነገረውንም
ቃል ሰማ ተብሎ እንደ ተጻፈ 2ቆሮ 12÷4 ስለዚህ በገድሉ መጻሕፍ እንዲ ሲል ሰማነው
"ተክለ ሃይማኖት ክፍልህ ከሃያ አራቱ ካህናቶቼ ጋር ይሁን የሚል ቃል ከዙፋኑ ውስጥ ወጣ
የወርቅ ጽና አምጥተው ሰጡኝና ከእነርሱ ጋር በአንንድነት አጠንኩ ምስጋዬ ከምስጋናቸው
ጋር ልብሴም እንደ ልብሳቸው ሆነ ፈጣሪዬንም በሦስትነቱ ተገልጦ አየሁት" ገ/ተ
ሃይማኖት ዘአርብ 43÷ 29
# የሐዲሱ_ሱራፊ_የአባታች_የቅዱስ_ተክለ_ሃይማኖት እረድኤትና በረከታቸው በአገራችን
በኢትዮጵያና በሕዝበ ክርስቲያኖች ሁሉ ላይ ጸንቶ ይኑር ! በወርቅ ጥናውም ዘወትር እያጠነ
መዓዛ ክርስቶስን የምንሸት እውነተኛ ክርስቲያኖች አድርጎ የመንግሥቱ ወራሾች የስሙ
ቀዳሾች እንድንሆን ያድርገን ለዘላለሙ አሜን!
............. ይቆየን............
ኀዳር 24/2013ዓ.ም
ዐውደ ምሕረት
Photo
#በኃይልህ ሰላም፥ #በጌጠኛ_ቤትህም_ልማት_ይሁን ! ። ስለ ወንድሞቼ ስለ ባልንጀሮቼም፦ በውስጥሽ ሰላም ይሁን አልሁ። ስለ #አምላካችን ስለ #እግዚአብሔር ቤት ላንቺ መልካምነትሽን ፈለግሁ።🙏
#መዝ 122÷7-9
#መዝ 122÷7-9
ዐውደ ምሕረት
Photo
#የመቅደሱ_ፈተናዎች
ፈተና በዓለም ሲገጥም በመቅደሱ ጥላ ተጠልሎ ፣ቆይቶ ፣ደጅ ተጠንቶ የጊዜው ጊዜ
ይታለፋል ። ግን በቤተ መቅደሱ ስንፈተን ወዴት ሄደን ፈተናውን ማለፍ ይቻለን ይሆን!?።
ከባድ ነው !“ መዝ 39(40)፥1
#እመ_አምላክ_ቅድስት_ድንግል_ማርያምን የገጠማት ከባዱ ፈተና ይህው የመቅደሱ
ፈተና ነበር።
ክቡራን የሆኑ ወላጆቿ ቅድስት ሐናና ቅዱስ እያቄም እግዚአብሔር የዓይናችን ማረፊያ
የልባችን ተስፈ የምትሆን ልጅ ቢሰጠን ውኃ ቀድታ ጥጥ ፈትላ ታገልግለን አንልም በቤትህ
የምታገለግል አድርገን ላንተው እንሰጣለን እንጂ ሲሉ በተሳሉት ስእለት መሠረት
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ነሐሴ ሰባት ቀን ጸንሰው ግንቦት አንድ ቀን ወለዷት
።
ሦስት ዓመት ሲሆናትም ቅድስ ሐና በስእለታችን መሠረት ለእግዚአብሔር ልንሰጣት
ያስፈልገናል ይዘናት ወደ ቤተ መቅደስ እንሂድ አለች ቅዱስ እያቄምም የልጅ ፍቅርሽ
ይውጣልሽ ብዬ እንጂ ዝም ያልኩት ነገሩንስ ሳስበው ነበር ካንቺ ከመጣማ በይ ነኝ
ስእለታችንን እንፈጽም አለ። “ሰነፎች ደስ አያሰኙትምና ለእግዚአብሔር ስእለት በተሳልህ
ጊዜ ትፈጽመው ዘንድ አትዘግይ፤ የተሳልኸውን ፈጽመው።” ተብሎ ተጽፎልና መክብብ 5፥4
# ወደ_ቤተ_መቅደስ ሲደርሱ የመጀመሪያው ፈተና መጣ በቤተ መቅደስ መኖሯስ ጥሩ ነገር
ነበር ግን የምግቧ ነገር እንዴት ይሆናል? የሚል ፈተና። ብዙቹ የቤተ መቅደሱ መተናዎች
ይህ እኮ ጥሩ ነበር ብለው የሚጀምሩ ሲሆኑ እመካከላቸው ግን የሚል አፍራሽ ቃል ወይም
ድርጊት የተቀላቀለበት ነው። ቄስ እገሌኮ ሲቀድሱ ድምጣቸው ውብ ነው ግን ሰዓት
ያስረዝማሉ ፤ ሰባኪ እንትና አቤት ትምህር አሰጣጡ ግን ትንታኔ ያበዛል ፤ ዘማሪማ እንደ
እሷ ያለ የትም አይገኝም ግን ወደ ዘፈን ትወስደዋለች ። ግን...ግን... ግን...
" #አሁን_ከሰማይ የወረድኩ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ" የሚል የሕይወት እንጀራ ክርስቶስን
የምትወልድ ሆና ሳለ ቁራሽ እንጀራ አጡላትና በመቅደስ መኖሯ ጥሩ ነበር ግን ምን ትበላ
ይሆን ? ብለው ተቸገሩ ዮሐ 6÷56 የብትውና ሕይወት ከሰዎችና ከዓለም ምኞት
የሚገለሉበትና የሚርቁበት ሕይወት እንጂ ከፈተና የሚገለሉበት ሕይወት አይደለም ይልቁኑ
ፈተና በብቸኞች (ባዕታዊያን)ላይ ይበረታል። በዐታዊቷ እመቤታችንም ወደ በዓቷ ከመግባቷ
እስከ መውጧታ በአያሌው ተፈትናለች።
ዲያቢሎስ ተንኮለኛ ነው አስቀድሞ በመቅደስ የሕይወት ፍሬ መገኛ የሆነች ጸዋሪተ ፍሬ
ኤፍራታን እመቤታችንን ምግብ የሌለ አስመሰሎ በእጅጉ ፈተናት በኋላ ልጇ ወዳጇን ኢየሱስ
ክርስቶስን ደግሞ በመቅደሱ በገዳመ ቆሮንቶስ ተገናኝቶ ድንጋዮን ዳቦ አርግና እንብላ እያለ
በምግብ መትረፍረፍ ይፈትን ዘንድ አለውና " በዘርህና በዘሯ መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ
እንደተባለ" ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን በመቅደሱ በገዳመ ቆሮንቶስ የገጠመውን የስስት
ፈተና በትእግሥት ድል የሚነሳው ነው እናቱ እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል
ማርያምም ይህን የመቅደስ ፈተና በቅዱስ ፋኑኤል እጅ በሚታይ በሰማያዊ መና
በተትረፈረፈ በረከት ድል የነሳችው ሆነች ።
#ሌላኛው_የመቅደስ ፈተና በቤተ መቅደሱ ጸንተን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሥራ
ሊሰራብን ባሰበ ጊዜ የሚገጥም የፈተና አይነት ነው 12 ዓመት በቤተ መቅደት ተቀምጣ
15ዓመት በሆናት ጊዜ መላእኩ ተልኩ መጥቶ ደስ ያለሽ ደስተኛይቱ ሆን ከሦስቱ አካላት
አንዱን አካል ከሦስቱ ቅዱስ አንዱን ቅዱስ ያለ ዘርዓ ብሕሲ (ያለ ወንድ ዘር) ትጸንሺዋለሽ
ትወልጅማለሽ ስሙንም አማኑኤል ትይዋሽ ብሎ አበሰራት ይህ ጊዜ አይሁድ ሴት ያለ ጋብቻ
ጸንሳ ከተገኘች በድንጋይ ተወግራ ትሙት የሚል ሕግ ነበራቸውና እንዳይወግሯት ጻድቁ
ዮሴፍ ይጠብቃት ዘንድ ተመረጠ አይሁድ ግን ቤተ መቅደሳችንን ታረክሳለች እንዴት ያለ
ወንድ ልትጸንስ ትችላለች አሉና ማየ ዘለፋ የተጸነሰ ጽንስ የሚያሶርድ መጠጥ ሰጧት
ጠጥታ የምትሞት መስሏቸው ቢያዮ ጨራሽ ፊቷ ከፀሐይ ሰባት እጅ አበራ በዚህ
ትተዋታል።
ከዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በኃላ በስምተኛው ቀን ሌላኛው የመቅደሱ ፈተና መጣ
ይገርዙት ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ይዘውት ሄዱ የማዳኑን ነገር ሳያይ እንዳይሞት ተስፋ
የተሰጠው ስምዖንን በቤተ መቅደስ አገኙትና ባረካቸው እንዲም አለ " ጌታ ሆይ፥ አሁን
እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ፤ ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን
ማዳንህን አይተዋልና፤ ........እነሆ፥ የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ፥ ይህ በእስራኤል
ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሞአል፥
በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል አላት።” ሉቃስ 2፥29-35 የስእለትም ልጅ
አይደለች መከራዋ ብዙ ነውና ። እረፍት ያጣች እርሷ የብዙ ደካሞች እረፍታችን ሆነች
መከረኛዋ እርሷ የመከረኞች ተስፋችን ሆነች ። በበዐቷ የተፈተነች ብቸኞች እኛኝ ከፈጣሪና
ከአእላፍ ቅዱሳን መላእክት ጋር አዛመደችን።
#የእመቤታችን_የቅድስት_ድንግል_ማርያም እረድኤትና በረከት በሀገራችን በኢትዮጵያ
በሕቦቿም በሕዝበ ክርስቲያኖች ላይ ዘለለዓለሙ ጸንቶ ይኑር!አሜን!
ኃ/ማርያም አ.አ ኢትዮጵያ
ታህሳስ3/2013ዓ.ም
ፈተና በዓለም ሲገጥም በመቅደሱ ጥላ ተጠልሎ ፣ቆይቶ ፣ደጅ ተጠንቶ የጊዜው ጊዜ
ይታለፋል ። ግን በቤተ መቅደሱ ስንፈተን ወዴት ሄደን ፈተናውን ማለፍ ይቻለን ይሆን!?።
ከባድ ነው !“ መዝ 39(40)፥1
#እመ_አምላክ_ቅድስት_ድንግል_ማርያምን የገጠማት ከባዱ ፈተና ይህው የመቅደሱ
ፈተና ነበር።
ክቡራን የሆኑ ወላጆቿ ቅድስት ሐናና ቅዱስ እያቄም እግዚአብሔር የዓይናችን ማረፊያ
የልባችን ተስፈ የምትሆን ልጅ ቢሰጠን ውኃ ቀድታ ጥጥ ፈትላ ታገልግለን አንልም በቤትህ
የምታገለግል አድርገን ላንተው እንሰጣለን እንጂ ሲሉ በተሳሉት ስእለት መሠረት
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ነሐሴ ሰባት ቀን ጸንሰው ግንቦት አንድ ቀን ወለዷት
።
ሦስት ዓመት ሲሆናትም ቅድስ ሐና በስእለታችን መሠረት ለእግዚአብሔር ልንሰጣት
ያስፈልገናል ይዘናት ወደ ቤተ መቅደስ እንሂድ አለች ቅዱስ እያቄምም የልጅ ፍቅርሽ
ይውጣልሽ ብዬ እንጂ ዝም ያልኩት ነገሩንስ ሳስበው ነበር ካንቺ ከመጣማ በይ ነኝ
ስእለታችንን እንፈጽም አለ። “ሰነፎች ደስ አያሰኙትምና ለእግዚአብሔር ስእለት በተሳልህ
ጊዜ ትፈጽመው ዘንድ አትዘግይ፤ የተሳልኸውን ፈጽመው።” ተብሎ ተጽፎልና መክብብ 5፥4
# ወደ_ቤተ_መቅደስ ሲደርሱ የመጀመሪያው ፈተና መጣ በቤተ መቅደስ መኖሯስ ጥሩ ነገር
ነበር ግን የምግቧ ነገር እንዴት ይሆናል? የሚል ፈተና። ብዙቹ የቤተ መቅደሱ መተናዎች
ይህ እኮ ጥሩ ነበር ብለው የሚጀምሩ ሲሆኑ እመካከላቸው ግን የሚል አፍራሽ ቃል ወይም
ድርጊት የተቀላቀለበት ነው። ቄስ እገሌኮ ሲቀድሱ ድምጣቸው ውብ ነው ግን ሰዓት
ያስረዝማሉ ፤ ሰባኪ እንትና አቤት ትምህር አሰጣጡ ግን ትንታኔ ያበዛል ፤ ዘማሪማ እንደ
እሷ ያለ የትም አይገኝም ግን ወደ ዘፈን ትወስደዋለች ። ግን...ግን... ግን...
" #አሁን_ከሰማይ የወረድኩ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ" የሚል የሕይወት እንጀራ ክርስቶስን
የምትወልድ ሆና ሳለ ቁራሽ እንጀራ አጡላትና በመቅደስ መኖሯ ጥሩ ነበር ግን ምን ትበላ
ይሆን ? ብለው ተቸገሩ ዮሐ 6÷56 የብትውና ሕይወት ከሰዎችና ከዓለም ምኞት
የሚገለሉበትና የሚርቁበት ሕይወት እንጂ ከፈተና የሚገለሉበት ሕይወት አይደለም ይልቁኑ
ፈተና በብቸኞች (ባዕታዊያን)ላይ ይበረታል። በዐታዊቷ እመቤታችንም ወደ በዓቷ ከመግባቷ
እስከ መውጧታ በአያሌው ተፈትናለች።
ዲያቢሎስ ተንኮለኛ ነው አስቀድሞ በመቅደስ የሕይወት ፍሬ መገኛ የሆነች ጸዋሪተ ፍሬ
ኤፍራታን እመቤታችንን ምግብ የሌለ አስመሰሎ በእጅጉ ፈተናት በኋላ ልጇ ወዳጇን ኢየሱስ
ክርስቶስን ደግሞ በመቅደሱ በገዳመ ቆሮንቶስ ተገናኝቶ ድንጋዮን ዳቦ አርግና እንብላ እያለ
በምግብ መትረፍረፍ ይፈትን ዘንድ አለውና " በዘርህና በዘሯ መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ
እንደተባለ" ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን በመቅደሱ በገዳመ ቆሮንቶስ የገጠመውን የስስት
ፈተና በትእግሥት ድል የሚነሳው ነው እናቱ እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል
ማርያምም ይህን የመቅደስ ፈተና በቅዱስ ፋኑኤል እጅ በሚታይ በሰማያዊ መና
በተትረፈረፈ በረከት ድል የነሳችው ሆነች ።
#ሌላኛው_የመቅደስ ፈተና በቤተ መቅደሱ ጸንተን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሥራ
ሊሰራብን ባሰበ ጊዜ የሚገጥም የፈተና አይነት ነው 12 ዓመት በቤተ መቅደት ተቀምጣ
15ዓመት በሆናት ጊዜ መላእኩ ተልኩ መጥቶ ደስ ያለሽ ደስተኛይቱ ሆን ከሦስቱ አካላት
አንዱን አካል ከሦስቱ ቅዱስ አንዱን ቅዱስ ያለ ዘርዓ ብሕሲ (ያለ ወንድ ዘር) ትጸንሺዋለሽ
ትወልጅማለሽ ስሙንም አማኑኤል ትይዋሽ ብሎ አበሰራት ይህ ጊዜ አይሁድ ሴት ያለ ጋብቻ
ጸንሳ ከተገኘች በድንጋይ ተወግራ ትሙት የሚል ሕግ ነበራቸውና እንዳይወግሯት ጻድቁ
ዮሴፍ ይጠብቃት ዘንድ ተመረጠ አይሁድ ግን ቤተ መቅደሳችንን ታረክሳለች እንዴት ያለ
ወንድ ልትጸንስ ትችላለች አሉና ማየ ዘለፋ የተጸነሰ ጽንስ የሚያሶርድ መጠጥ ሰጧት
ጠጥታ የምትሞት መስሏቸው ቢያዮ ጨራሽ ፊቷ ከፀሐይ ሰባት እጅ አበራ በዚህ
ትተዋታል።
ከዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በኃላ በስምተኛው ቀን ሌላኛው የመቅደሱ ፈተና መጣ
ይገርዙት ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ይዘውት ሄዱ የማዳኑን ነገር ሳያይ እንዳይሞት ተስፋ
የተሰጠው ስምዖንን በቤተ መቅደስ አገኙትና ባረካቸው እንዲም አለ " ጌታ ሆይ፥ አሁን
እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ፤ ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን
ማዳንህን አይተዋልና፤ ........እነሆ፥ የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ፥ ይህ በእስራኤል
ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሞአል፥
በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል አላት።” ሉቃስ 2፥29-35 የስእለትም ልጅ
አይደለች መከራዋ ብዙ ነውና ። እረፍት ያጣች እርሷ የብዙ ደካሞች እረፍታችን ሆነች
መከረኛዋ እርሷ የመከረኞች ተስፋችን ሆነች ። በበዐቷ የተፈተነች ብቸኞች እኛኝ ከፈጣሪና
ከአእላፍ ቅዱሳን መላእክት ጋር አዛመደችን።
#የእመቤታችን_የቅድስት_ድንግል_ማርያም እረድኤትና በረከት በሀገራችን በኢትዮጵያ
በሕቦቿም በሕዝበ ክርስቲያኖች ላይ ዘለለዓለሙ ጸንቶ ይኑር!አሜን!
ኃ/ማርያም አ.አ ኢትዮጵያ
ታህሳስ3/2013ዓ.ም
ዐውደ ምሕረት
Photo
"ድንግል ማርያም ለአምላክ የደስታ ማደሪያው ሆነችው"
ተአምረ ማርያም መቅድም
ዘዘወትር ቁ29
ተአምረ ማርያም መቅድም
ዘዘወትር ቁ29