#ፍጻሜ_ሥጋ
አንዳንድ ቀን አለ . . .!
በደማቅ ቀለማት ከልብ የሚታተም
ልክ እንደፏፏቴ ካ'ለት የሚላተም።
በዚያ ቀን ...!
ጽልመት አሸንፋ የጠራች ጨረቃ፣
ሆደ ሠፊን ሰማይ አበራችው ደምቃ፤
ገዴ ዕጣ ክፍሌ . . .
አንዲት ፍኩ ኮከብ ፣ መለዮ ሰንደቋ።
ያን ቀን ...!
የምኞቴ እውነት ፣ የጸሎቴ ብሥራት
የልመናዬ ጥግ ፣ የሥለቴ ስምረት።
ጎኔ ተኝታለች፤
በዙሪያዬ ጸንታ ዕቅፌ ገብታለች።
ለደቂቃ ቅጽበት
በዐይኔ ዕቅፋት
በአንድ ጥቅሻ ፤
በከንፈርሽ ነጻ የልቤ ጥቀርሻ።
ይህ ቀን . . .!
ዐርብ ዕለት
ምሽት ኹለት ሰዓት ፣
እንዲሁም .
ጥንድ እውነት።
ያነፋስ ውብ ዜማ ፣ የቀልቤ ውልብታ
ያ'ብሪ ትሎች ፋና . . .
ምንጩ ያልታወቀ የነፍስ ፈገግታ።
(. . . ሠንቆ ነበረ . . . )
ፍጥረታት አኩርፈው ሰማይ ከል ለብሶ ፣
ትንቢት ተፈጽሞ . .
የሾኽ አክሊል ደፍቶ ቃል ሥጋ ተላብሶ።
ከእልፍ እንስት ዐይኖች ፣ እንባ እየጎረፈ፤
ፍጹሙ ፍቅራችን ፣
በፍጻሜው ዕለት ፣
የነፍስ ሐቃችን ውል ፣ እየተጠለፈ ፤
ሰውኛ ግብራችን . . .
የተፈጥሮን ኩርፊያ በጻድቅ ደም ጻፈ።
እናም በዚኽ ዕለት
የነፍሳችን ክብር በ'ርቃን ከታሠረ ፤
ሥጋ ፍጻሜ ነው !
በ'ርቃንሽ ተዋርዶ በደምሽ ከበረ።
🔘ተስፍሁን ከበደ🔘
አንዳንድ ቀን አለ . . .!
በደማቅ ቀለማት ከልብ የሚታተም
ልክ እንደፏፏቴ ካ'ለት የሚላተም።
በዚያ ቀን ...!
ጽልመት አሸንፋ የጠራች ጨረቃ፣
ሆደ ሠፊን ሰማይ አበራችው ደምቃ፤
ገዴ ዕጣ ክፍሌ . . .
አንዲት ፍኩ ኮከብ ፣ መለዮ ሰንደቋ።
ያን ቀን ...!
የምኞቴ እውነት ፣ የጸሎቴ ብሥራት
የልመናዬ ጥግ ፣ የሥለቴ ስምረት።
ጎኔ ተኝታለች፤
በዙሪያዬ ጸንታ ዕቅፌ ገብታለች።
ለደቂቃ ቅጽበት
በዐይኔ ዕቅፋት
በአንድ ጥቅሻ ፤
በከንፈርሽ ነጻ የልቤ ጥቀርሻ።
ይህ ቀን . . .!
ዐርብ ዕለት
ምሽት ኹለት ሰዓት ፣
እንዲሁም .
ጥንድ እውነት።
ያነፋስ ውብ ዜማ ፣ የቀልቤ ውልብታ
ያ'ብሪ ትሎች ፋና . . .
ምንጩ ያልታወቀ የነፍስ ፈገግታ።
(. . . ሠንቆ ነበረ . . . )
ፍጥረታት አኩርፈው ሰማይ ከል ለብሶ ፣
ትንቢት ተፈጽሞ . .
የሾኽ አክሊል ደፍቶ ቃል ሥጋ ተላብሶ።
ከእልፍ እንስት ዐይኖች ፣ እንባ እየጎረፈ፤
ፍጹሙ ፍቅራችን ፣
በፍጻሜው ዕለት ፣
የነፍስ ሐቃችን ውል ፣ እየተጠለፈ ፤
ሰውኛ ግብራችን . . .
የተፈጥሮን ኩርፊያ በጻድቅ ደም ጻፈ።
እናም በዚኽ ዕለት
የነፍሳችን ክብር በ'ርቃን ከታሠረ ፤
ሥጋ ፍጻሜ ነው !
በ'ርቃንሽ ተዋርዶ በደምሽ ከበረ።
🔘ተስፍሁን ከበደ🔘
👍2