ሆኖ ከተገኘ፤ እጅግ ከባድ ፀፀት ብቻም ሳይሆን ለደረሰባት አሰቃቂ አደጋ ጭምር ተጠያቂው እሱ መሆኑንን ጭምር አእምሮው ሹክ አለው....
በዚያን የፍርድ ውሳኔው በሚሰማበት ዕለት ሻምበል ብሩክ አዜብና አንዱአለም ፀአዳ ለብሰው አምረውና ደምቀው ውሣኔውን ሊሰሙ ወደ ፍርድ ቤት ሄዱ፡፡ እናቷ ወይዘሮ አመልማል በአካል አብራቸው መሄዱ ቢያቅታትም ልቧ ተከትሏቸዋል፡፡ በተለይ ሻምበል ብሩክ ሙሉ ጥቁር ሱፍ፣ ነጭ ሸሚዝና ፍንጥቅጥቅ ውሃ ሰማያዊ ክራቫት አስሮ
ሙሽራ መስሏል፡፡ ምን አስቦ ይሆን?.....
የወንጀል ችሎት... የፍትሐብሔር ችሎት... የሥራ ክርክር ልዩ ልዩ ችሎቶች በሚመረመሩበት በህግ የሚፈተሽበት
በአንቀጽ በሚተነተንበት ጠበቆች ወገባቸውን ጠበቅ አድርገው በሚሟገቱበት፡ ዳኞች በጥቁር ካባቸውን
ተጐናጽፈው፤ በግርማ ሞገስ ተሰይመው ፍርድ ወደ ሚሰጡበት አምባ.....ግማሹ ሲስቅ፣ ግማሹ ወደሚያለቅስበት፡
የፍትህ አደባባይ፤የተፈረደለት ሲፈነድቅ፤ የተፈረደበት አንገቱን ወደሚያቀረቅርበት፤ ወደ ፍርድ ቤት ሄዱ፡፡
ሶስቱ ዳኞች ካባቸውን ደርበው ከፍ ብሎ በተዘጋጀው መድረክ ላይ በግርማ ሞገስ ተሰይመዋል፡፡
በችሎቱ ውስጥ ታዳሚው ግጥም ብሎ ሞልቷል፡፡ ሞልቶ ተርፎም ከደጅ ድረስ ቆሟል። አንዳንዱ ልማድ ያለው እንጂ ጉዳይ ያለው ሆኖ አይደለም፡፡ እዚያ ፍርድ ቤት ሆነው የፍርድ ቤቱን ስርዓትና ደንብ
መመልከት፣ የህግ አንቀጾችን ማጥናት፣ የጠበቆችን የክርክር ስልት መከታተል፡ አንደሱስ የሆነባቸው ጥቂቶች አይደሉም፡፡ ከእነዚህ መካከል አንድ ታዳሚ ግን የፍርድ ቤቱን ደጃፍ የረገጠው ገና ዛሬ ነው፡፡
ሁለመናው አቆብቁቦ፤ በሰው መግደል ሙከራ ወንጀል ተከሳ የታሰረች ወጣት
ወደ ፍርድ ቤቱ አዳራሽ የምትገባበትን ጊዜ በናፍቆት እየተጠበባበቀ ይገኛል፡፡ ደጅ ደጁን አስር ጊዜ ያያል ።ከዚያም ያ
በናፍቆት ሲጠባበቀው የቆየው ስም ተጠራ :፡ልቡ ድው፧ ድው፤ አለችበት፡፡ አይኖቹ ወደ በሩ ተወረወሩ፡፡ ከዚያም ያቺ ወጣት በአጃቢ ፖሊስ አማካኝነት ታጅባ ወደ ፍርድ ቤቱ አዳራሽ ስትዘልቅ ተመለከተ ::
አይኖቹን ማመን አቃተው፡፡ ልክ ነው፡፡ ራሷ ናት፡፡ በግራ ጆሮዋ ላይ ጠባሳ
ተጋድሞባታል፡፡ መልኳም ትንሽ ተጐሳቁሏል፡፡ አንጀቱ ተርገፈገፈ፡፡
እንባው አመለጠው፡፡ እሱ እንደዚያ
በጉጉት ተውጦ ሁኔታዎችን ሲከታተል፤ አዜብ ደግሞ ተደብቃ የሱን ሁኔታ ትከታተል ነበር :: ተንኮሏ ስለሰራላት በጣም ተደስታ ነበር፡፡ የት አባቱ! ለሰራው
ግፍ አያንሰውም እያለች ነበር፡፡ በልቧ፡፡ በኋላ ላይ ግን ይህንን ሃሳቧን የሚፈታተን ድርጊት ስትመለከት ልቧ አዘነ፡፡ እንባ ከፊቱ ኮለል እያለ ሲወርድ ተመልክታ፤ የሆነ ስሜት፤ የመጸጸት ስሜት፤ ተሰማት :: ከዚያም ተከሳሿ በተከሳሽ መቆሚያ ሳጥን ውስጥ ሆና የፍርድ
ውሳኔው መሰማት ጀመረ፡፡
ረዘም ቀላ ያሉትና ፀጉራቸውን ሽበት ጣል ጣል ያደረገበት የመሐል ዳኛ የዳጎሰ አረንጓዴ ፋይል አወጡ፡፡ በዛሬው ችሎት ላይ እንደሻው በቀለ ተገኝቷል በወላጆቹ ታጅቦ ከወዲያ ማዶ ሆኖ ከወዲህ ማዶ
የተቀመጡት እነ ሻምበል ብሩክን በቀሉት ዐይኖቹ ይገረምማቸዋል።
ከዚያም ዳኛው መነጽራቸውን አውልቀው ወለወሉና ፋይሉን ገለጡ፡፡
ከሳሽ፣ ዐቃቤ ህግ
ተከሳሽ፣ ወይዘሪት ትህትና ድንበሩ
የክሱ ምክንያት ሰው የመግደል ሙከራ ወንጀል
ተከሳሽ ትህትና ድንበሩ፤ የጦር መሣሪያ በመያዝ፤ ወጣት እንደሻው በቀለ ከሚሰራበት የግል የንግድ ሱቅ ድረስ በመሄድ፤ በአራት ጥይቶች ተኩሳ በማቁሰል፤ የመግደል ሙከራ በማድረጓ የተመሰረተ ክስ ሲሆን፤ ለክሱ መልስና የመልስ መልስ ተሰጥቶበታል፡፡ ከሳሽ የሆስፒታል ማስረጃ፣ የፓሊስ ሪፓርትና፤ ወንጀሉ የተፈጸመበትን የጦር መሣሪያ፧
በኤግዚቢትነት ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል፡፡ ምስክሮች ቀርበው ተሰምተዋል።
ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ፤ ተከሳሽ ጥፋተኛ ሆና በማግኘቷ
የጥፋተኛነት ውሣኔ ሰጥቷል፡፡
ተከሳሽ በተመሰረተባት ክስ መሠረት የቅጣት ውሣኔ ለመስጠት እንዲያስችል፤ ዐቃቤ ህግና የተከሳሽ ጠበቃ፤ የቅጣት ማቅለያ፤ ወይንም የቅጣት ማክበጃ፤ ሃሣባቸውን እንዲያቀርቡ ተደርጐ፤ በሁሉቱም ወገን የቀረበው የመፋረጃ ሃሣብ በፍርድ ቤቱ ተመዝግቧል፡፡ ስለሆነም ፍርድ ቤቱ የቀረበውን የግራ ቀኙን የመፋረጃ ሃሣብ በመመርመርና፤ የወንጀለኛ መቅጫ ህጐችን መሠረት በማድረግ፤ ከዚህ የሚከተለውን የፍርድ ውሣኔ ሰጥቷል፡፡
#ፍርድ
ተከሳሽ በፈጸመችው ወንጀል ጥፋተኛ ሆና ብትገኝም፤ ወንጀሉን ለመፈጸም የተነሳሳችበትን የሞራል ተቃራኒ ድርጊት፤ የተከሳሽን የቀድሞ ስነምግባር ሁኔታ፤ የቤተሰብ ሃላፊነት ደረጃን፤ የተከሳሿን የዕድሜ ሁኔታ፤ ከግምት ውስጥ በማስገባት፤ እንደዚሁም፧ ተከሳሽ ከዚህ በፊት በማንኛውም የወንጀል ድርጊት ውስጥ ተሳትፋ ያልተቀጣችና፤ ለወደፊቱ
ከዚህ ጥፋት ተምራ መልካም ዜጋ ልትሆን የምትችል ታዳጊ ወጣት መሆኗን በማገናዘብ፤ እጇ ከተያዘበት ዕለት ጀምሮ ለሶስት ዓመት በማረሚያ ቤቱ ውስጥ ቆይታ እንድትታረም ወስነን፤ ፋይሉን ዘግተን፤ ወደ መዝገብ ቤት መልሰናል፡፡
ፊርማ
የመሀል ዳኛ
ጸጥ አርጋቸው ተፈራ
በውሣኔው ቅር የተሰኘ ወገን ይግባኝ የመጠየቅ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ውሣኔውን ለመስማት ሁሉም ፀጥ ብሏል፡፡ እያንዳንዷ እንቅስቃሴና
ኮሽታዋ ሁሉ፤ ጎልታ ትሰማ ነበር፡፡ ልብ ድው፤ ድው! ሲል ይደመጣል፡፡ ትንፋሽ በአጭር በአጭሩ....ይሮጣል፡፡ ዶክተር ባይከዳኝም የፍርዱ ውሳኔ እስከሚነበብ ድረስ የልቡ ምት ፍጥነቱን ጨምሮ ነበር፡፡
በዚያች ሰዓት ለትህትና እና ከጉኗ ለተሰለፉት ወገኖቿ የዓለም እንቅስቃሴ የቆመ መስሏቸው ነበር። እንደ እውነቱ ከሆነ ውሣኔው ከገመቱት በጣም ያነሰ ነበር የፍርድ ውሳኔዋን ሰምታ ከተከሳሽ
መቆሚያ ሣጥን እንደወረደች፣ ፓሊሱ ከፊት አስቀድሟት ወጣ፡፡ አዜብ
ሻምበል ብሩክና ወንድሟ ፓሊሱን ተከትለው አጀቧት፡፡ ከዚያም ሄደው
አቀፏትና......
“አይዞሽ አንዱን ጨርስሻል፡፡ የቀረችሽ ሁለት ዓመት ብቻ ናት፡፡
ሁለት ዓመት ማለት ሁለት ቀን ነች” በማለት ሞራል ሰጧት፡፡
እዚያ የተሰበሰበው ህዝብ የእነሱን ሁኔታ እያየ... አይዞሽ? አይዞሽ! አይዞሽ!” በማለት የማያቋርጥ የማበረታቻ ድጋፍ እየሰጣት ነበር፡፡ ተደጋጋሚ በደል የተፈጸመባት ወጣት በመሆኗ፤ አብዛኞቹ እንደ ወንጀለኛ በክፉ አይናቸው ሊያይዋት አልፈለጉም፡፡ዶክተር ባይከዳኝም
ከፍርድ ውሳኔው ዝርዝር በተጨማሪ አጠገቡ ተቀምጦ ከነበረው ታዳሚ
አንደበት፧ ልክ አዜብ በነገረችው መሰረት፤ የወንጀሉን ታሪክ ሰምቷል፡፡ በጉልበቱ ድንግልናዋን በወሰደው ሰው ላይ አደጋ አድርሳ በራሷም ላይ ጉዳት ማድረሷን፤ እንደሻውን ጠቁሞ በማሳየት ጭምር
አረጋግጦለታል፡፡
ዶክተር ባይከዳኝ ይህንን ሁሉ ካረጋገጠ በኋላ፤ እንደፈራው አልቀረም፡፡ ከባድ ጸጸት አደረበት፡፡ በዚያን ዕለት መጥፎ ስድብ በሰደባት ዕለት የነበረችው ትህትና ታወሰችውና ራሱን ወቀሰ፡፡ ትህትና በአጃቢ ፖሊሱ ታጅባ ከችሎቱ እንደወጣች፤ ፖሊሱ ከፊትዋ ቀደመና፤ ፈጠን ፈጠን፤ እያለ አስከተላት፡፡ ከሁዋላ፤ ከሁዋላው፤ ተከተለችው :: ከዚያም
እዚያ በጣም ትልቅና በጥላው ምክንያት ቀዝቃዛ አየር ከሚነፍስበት የግራር ዛፍ አጠገብ ሲደርስ ቆም አለ ፡፡ ሻምበልም ወደ አጃቢ ፖሊሱ ጠጋ አለና ጀርባውን ቸብ፤ ቸብ፤ በማድረግ ፈገግ አለ፡፡ ፖሊሱም ሰፊ ፈገግታውን ለገሰው፡፡ መልካም... ይሁንልህ ማለቱ ይሆን? :: ከዚያም ሻምበል ብሩክ ለዚህች ለዛሬዋ አስገራሚ እለት የተዘጋጀበትን፡ አስቀድሞ
ፍቃድ ያገኘበትን፡ እቅዱን ሊያጠናቅቅ፤ ወደ ትህትና ተጠጋ፡፡ ፖሊሱም በአክብሮት ፈንጠር ብሎ ቆመና ቦታውን ለሻምበል
በዚያን የፍርድ ውሳኔው በሚሰማበት ዕለት ሻምበል ብሩክ አዜብና አንዱአለም ፀአዳ ለብሰው አምረውና ደምቀው ውሣኔውን ሊሰሙ ወደ ፍርድ ቤት ሄዱ፡፡ እናቷ ወይዘሮ አመልማል በአካል አብራቸው መሄዱ ቢያቅታትም ልቧ ተከትሏቸዋል፡፡ በተለይ ሻምበል ብሩክ ሙሉ ጥቁር ሱፍ፣ ነጭ ሸሚዝና ፍንጥቅጥቅ ውሃ ሰማያዊ ክራቫት አስሮ
ሙሽራ መስሏል፡፡ ምን አስቦ ይሆን?.....
የወንጀል ችሎት... የፍትሐብሔር ችሎት... የሥራ ክርክር ልዩ ልዩ ችሎቶች በሚመረመሩበት በህግ የሚፈተሽበት
በአንቀጽ በሚተነተንበት ጠበቆች ወገባቸውን ጠበቅ አድርገው በሚሟገቱበት፡ ዳኞች በጥቁር ካባቸውን
ተጐናጽፈው፤ በግርማ ሞገስ ተሰይመው ፍርድ ወደ ሚሰጡበት አምባ.....ግማሹ ሲስቅ፣ ግማሹ ወደሚያለቅስበት፡
የፍትህ አደባባይ፤የተፈረደለት ሲፈነድቅ፤ የተፈረደበት አንገቱን ወደሚያቀረቅርበት፤ ወደ ፍርድ ቤት ሄዱ፡፡
ሶስቱ ዳኞች ካባቸውን ደርበው ከፍ ብሎ በተዘጋጀው መድረክ ላይ በግርማ ሞገስ ተሰይመዋል፡፡
በችሎቱ ውስጥ ታዳሚው ግጥም ብሎ ሞልቷል፡፡ ሞልቶ ተርፎም ከደጅ ድረስ ቆሟል። አንዳንዱ ልማድ ያለው እንጂ ጉዳይ ያለው ሆኖ አይደለም፡፡ እዚያ ፍርድ ቤት ሆነው የፍርድ ቤቱን ስርዓትና ደንብ
መመልከት፣ የህግ አንቀጾችን ማጥናት፣ የጠበቆችን የክርክር ስልት መከታተል፡ አንደሱስ የሆነባቸው ጥቂቶች አይደሉም፡፡ ከእነዚህ መካከል አንድ ታዳሚ ግን የፍርድ ቤቱን ደጃፍ የረገጠው ገና ዛሬ ነው፡፡
ሁለመናው አቆብቁቦ፤ በሰው መግደል ሙከራ ወንጀል ተከሳ የታሰረች ወጣት
ወደ ፍርድ ቤቱ አዳራሽ የምትገባበትን ጊዜ በናፍቆት እየተጠበባበቀ ይገኛል፡፡ ደጅ ደጁን አስር ጊዜ ያያል ።ከዚያም ያ
በናፍቆት ሲጠባበቀው የቆየው ስም ተጠራ :፡ልቡ ድው፧ ድው፤ አለችበት፡፡ አይኖቹ ወደ በሩ ተወረወሩ፡፡ ከዚያም ያቺ ወጣት በአጃቢ ፖሊስ አማካኝነት ታጅባ ወደ ፍርድ ቤቱ አዳራሽ ስትዘልቅ ተመለከተ ::
አይኖቹን ማመን አቃተው፡፡ ልክ ነው፡፡ ራሷ ናት፡፡ በግራ ጆሮዋ ላይ ጠባሳ
ተጋድሞባታል፡፡ መልኳም ትንሽ ተጐሳቁሏል፡፡ አንጀቱ ተርገፈገፈ፡፡
እንባው አመለጠው፡፡ እሱ እንደዚያ
በጉጉት ተውጦ ሁኔታዎችን ሲከታተል፤ አዜብ ደግሞ ተደብቃ የሱን ሁኔታ ትከታተል ነበር :: ተንኮሏ ስለሰራላት በጣም ተደስታ ነበር፡፡ የት አባቱ! ለሰራው
ግፍ አያንሰውም እያለች ነበር፡፡ በልቧ፡፡ በኋላ ላይ ግን ይህንን ሃሳቧን የሚፈታተን ድርጊት ስትመለከት ልቧ አዘነ፡፡ እንባ ከፊቱ ኮለል እያለ ሲወርድ ተመልክታ፤ የሆነ ስሜት፤ የመጸጸት ስሜት፤ ተሰማት :: ከዚያም ተከሳሿ በተከሳሽ መቆሚያ ሳጥን ውስጥ ሆና የፍርድ
ውሳኔው መሰማት ጀመረ፡፡
ረዘም ቀላ ያሉትና ፀጉራቸውን ሽበት ጣል ጣል ያደረገበት የመሐል ዳኛ የዳጎሰ አረንጓዴ ፋይል አወጡ፡፡ በዛሬው ችሎት ላይ እንደሻው በቀለ ተገኝቷል በወላጆቹ ታጅቦ ከወዲያ ማዶ ሆኖ ከወዲህ ማዶ
የተቀመጡት እነ ሻምበል ብሩክን በቀሉት ዐይኖቹ ይገረምማቸዋል።
ከዚያም ዳኛው መነጽራቸውን አውልቀው ወለወሉና ፋይሉን ገለጡ፡፡
ከሳሽ፣ ዐቃቤ ህግ
ተከሳሽ፣ ወይዘሪት ትህትና ድንበሩ
የክሱ ምክንያት ሰው የመግደል ሙከራ ወንጀል
ተከሳሽ ትህትና ድንበሩ፤ የጦር መሣሪያ በመያዝ፤ ወጣት እንደሻው በቀለ ከሚሰራበት የግል የንግድ ሱቅ ድረስ በመሄድ፤ በአራት ጥይቶች ተኩሳ በማቁሰል፤ የመግደል ሙከራ በማድረጓ የተመሰረተ ክስ ሲሆን፤ ለክሱ መልስና የመልስ መልስ ተሰጥቶበታል፡፡ ከሳሽ የሆስፒታል ማስረጃ፣ የፓሊስ ሪፓርትና፤ ወንጀሉ የተፈጸመበትን የጦር መሣሪያ፧
በኤግዚቢትነት ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል፡፡ ምስክሮች ቀርበው ተሰምተዋል።
ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ፤ ተከሳሽ ጥፋተኛ ሆና በማግኘቷ
የጥፋተኛነት ውሣኔ ሰጥቷል፡፡
ተከሳሽ በተመሰረተባት ክስ መሠረት የቅጣት ውሣኔ ለመስጠት እንዲያስችል፤ ዐቃቤ ህግና የተከሳሽ ጠበቃ፤ የቅጣት ማቅለያ፤ ወይንም የቅጣት ማክበጃ፤ ሃሣባቸውን እንዲያቀርቡ ተደርጐ፤ በሁሉቱም ወገን የቀረበው የመፋረጃ ሃሣብ በፍርድ ቤቱ ተመዝግቧል፡፡ ስለሆነም ፍርድ ቤቱ የቀረበውን የግራ ቀኙን የመፋረጃ ሃሣብ በመመርመርና፤ የወንጀለኛ መቅጫ ህጐችን መሠረት በማድረግ፤ ከዚህ የሚከተለውን የፍርድ ውሣኔ ሰጥቷል፡፡
#ፍርድ
ተከሳሽ በፈጸመችው ወንጀል ጥፋተኛ ሆና ብትገኝም፤ ወንጀሉን ለመፈጸም የተነሳሳችበትን የሞራል ተቃራኒ ድርጊት፤ የተከሳሽን የቀድሞ ስነምግባር ሁኔታ፤ የቤተሰብ ሃላፊነት ደረጃን፤ የተከሳሿን የዕድሜ ሁኔታ፤ ከግምት ውስጥ በማስገባት፤ እንደዚሁም፧ ተከሳሽ ከዚህ በፊት በማንኛውም የወንጀል ድርጊት ውስጥ ተሳትፋ ያልተቀጣችና፤ ለወደፊቱ
ከዚህ ጥፋት ተምራ መልካም ዜጋ ልትሆን የምትችል ታዳጊ ወጣት መሆኗን በማገናዘብ፤ እጇ ከተያዘበት ዕለት ጀምሮ ለሶስት ዓመት በማረሚያ ቤቱ ውስጥ ቆይታ እንድትታረም ወስነን፤ ፋይሉን ዘግተን፤ ወደ መዝገብ ቤት መልሰናል፡፡
ፊርማ
የመሀል ዳኛ
ጸጥ አርጋቸው ተፈራ
በውሣኔው ቅር የተሰኘ ወገን ይግባኝ የመጠየቅ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ውሣኔውን ለመስማት ሁሉም ፀጥ ብሏል፡፡ እያንዳንዷ እንቅስቃሴና
ኮሽታዋ ሁሉ፤ ጎልታ ትሰማ ነበር፡፡ ልብ ድው፤ ድው! ሲል ይደመጣል፡፡ ትንፋሽ በአጭር በአጭሩ....ይሮጣል፡፡ ዶክተር ባይከዳኝም የፍርዱ ውሳኔ እስከሚነበብ ድረስ የልቡ ምት ፍጥነቱን ጨምሮ ነበር፡፡
በዚያች ሰዓት ለትህትና እና ከጉኗ ለተሰለፉት ወገኖቿ የዓለም እንቅስቃሴ የቆመ መስሏቸው ነበር። እንደ እውነቱ ከሆነ ውሣኔው ከገመቱት በጣም ያነሰ ነበር የፍርድ ውሳኔዋን ሰምታ ከተከሳሽ
መቆሚያ ሣጥን እንደወረደች፣ ፓሊሱ ከፊት አስቀድሟት ወጣ፡፡ አዜብ
ሻምበል ብሩክና ወንድሟ ፓሊሱን ተከትለው አጀቧት፡፡ ከዚያም ሄደው
አቀፏትና......
“አይዞሽ አንዱን ጨርስሻል፡፡ የቀረችሽ ሁለት ዓመት ብቻ ናት፡፡
ሁለት ዓመት ማለት ሁለት ቀን ነች” በማለት ሞራል ሰጧት፡፡
እዚያ የተሰበሰበው ህዝብ የእነሱን ሁኔታ እያየ... አይዞሽ? አይዞሽ! አይዞሽ!” በማለት የማያቋርጥ የማበረታቻ ድጋፍ እየሰጣት ነበር፡፡ ተደጋጋሚ በደል የተፈጸመባት ወጣት በመሆኗ፤ አብዛኞቹ እንደ ወንጀለኛ በክፉ አይናቸው ሊያይዋት አልፈለጉም፡፡ዶክተር ባይከዳኝም
ከፍርድ ውሳኔው ዝርዝር በተጨማሪ አጠገቡ ተቀምጦ ከነበረው ታዳሚ
አንደበት፧ ልክ አዜብ በነገረችው መሰረት፤ የወንጀሉን ታሪክ ሰምቷል፡፡ በጉልበቱ ድንግልናዋን በወሰደው ሰው ላይ አደጋ አድርሳ በራሷም ላይ ጉዳት ማድረሷን፤ እንደሻውን ጠቁሞ በማሳየት ጭምር
አረጋግጦለታል፡፡
ዶክተር ባይከዳኝ ይህንን ሁሉ ካረጋገጠ በኋላ፤ እንደፈራው አልቀረም፡፡ ከባድ ጸጸት አደረበት፡፡ በዚያን ዕለት መጥፎ ስድብ በሰደባት ዕለት የነበረችው ትህትና ታወሰችውና ራሱን ወቀሰ፡፡ ትህትና በአጃቢ ፖሊሱ ታጅባ ከችሎቱ እንደወጣች፤ ፖሊሱ ከፊትዋ ቀደመና፤ ፈጠን ፈጠን፤ እያለ አስከተላት፡፡ ከሁዋላ፤ ከሁዋላው፤ ተከተለችው :: ከዚያም
እዚያ በጣም ትልቅና በጥላው ምክንያት ቀዝቃዛ አየር ከሚነፍስበት የግራር ዛፍ አጠገብ ሲደርስ ቆም አለ ፡፡ ሻምበልም ወደ አጃቢ ፖሊሱ ጠጋ አለና ጀርባውን ቸብ፤ ቸብ፤ በማድረግ ፈገግ አለ፡፡ ፖሊሱም ሰፊ ፈገግታውን ለገሰው፡፡ መልካም... ይሁንልህ ማለቱ ይሆን? :: ከዚያም ሻምበል ብሩክ ለዚህች ለዛሬዋ አስገራሚ እለት የተዘጋጀበትን፡ አስቀድሞ
ፍቃድ ያገኘበትን፡ እቅዱን ሊያጠናቅቅ፤ ወደ ትህትና ተጠጋ፡፡ ፖሊሱም በአክብሮት ፈንጠር ብሎ ቆመና ቦታውን ለሻምበል
👍1