#ፈጣሪ_ብሔሩ_ምንድን_ነው... ?
ህመሜን ፍለጋ
ትኩሳት ነው ብለው
ሰዎች ይነግሩኛል፣
ራስ ምታት ነው ብለው
ይገምቱልኛል፣
:
ግማሹ እየመጣ
ጨጓራ ይዞሃል
ብሎ እየነገረኝ፤
ግማሹ ሰው ደግሞ
ኩላሊት አለብህ
ብሎ እየነገረኝ፤
ህመሜን ሰው ሁሉ
ስም እያወጣለት፤
ለየትኛው ህመም ክኒን ልዋጥለት፤
ለየትኛው ህመም መርፌ ልወጋለት።
:
ብቻ ይሄው ምልክቱ፣
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን ደፍሬ
እንዲህ ያስብለኛል፤
ለንፁሀኑ በደል
ለንፁሀኑ ደም ወርደህ እንድትፈርድ
በምነኛ እንፁም በምነኛ እንስገድ፤
በትግርኛ እንስገድ?
በአማርኛ እንስገድ?
በኦሮምኛ እንስገድ?
የቱ ነው ሚቀርብህ
የትኛው ነው ያንተ ብሔር ያሰኘኛል፤
ስሙ ጠፋኝ እንጂ እውነት ነው አሞኛል፤
:
ግን ግን ይህ ህመም ምንድን ነው?
እንደምን ልወቀው?
ህመሜን እንዳልውጥ
ስቃዩ በዛብኝ እንዴት ልደብቀው፤
:
ቸገረኝ!
:
እስኪ ታውቁ እንደሆን
የበሽታዬን ስም
ንገሩኝ ልለየው፤
ፍለጋው ነው እንጂ
ህመም ስቃዩ አይደል
ነፍሴን የሚለየው፤
:
ብቻ ይሄው ምልክቱ
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን
ደፍሬ እንዲህ ያስብለኛል፤
ጥበብ ያልከኝን ቃል
በቃሌ መዝገብ ላይ እየተረጎምኩኝ
ጠብቤ ጠብቤ ጎሳህን ዘረክን ብሄርክን ጠየኩኝ
ጌታ ግን ምንድን ነህ ?
ኦሮሞ
ጉራጌ
ሱማሌ
ሀረርጌ
ትግሬ ነህ አማራ፤
ቤተስኪያን አልሄድም
መስጊድም አልሄድም ዘርክን እስካጣራ
ማለትም ያምረኛል
ስሙ ጠፋኝ እንጂ እውነት ነው አሞኛል፤
ግን ግን ይህ ህመም ምንድን ነው?
እንደምን ልወቀው?
ህመሜን እንዳልውጥ
ስቃዩ በዛብኝ እንዴት ልደብቀው፤
:
ሞትማ ክብር ነው
ሞትማ 'ረፍት ነው
ቅር ቢሉት የማይቀር፤
ከነጥያቄዬ ወደ ሌላኛው ዓለም
መሄድ መጓዜ ግን
ሰላም እንዳይነሳኝ
ከነፍሴ ጋር ሄዶ እንዳይሰነቀር።
:
ብቻ ይሄው ምልክቱ
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን
ደፍሬ እንዲህ ያስብለኛል፤
:
በፈጠርካት ምድር ድንበር አበጅተን
የኔ ነው የኔ ነው ተባብለን አድረናል
ሁሉ ያንተ መሆኑን ዘንግተን ከኖርን
ብዙ አመት ሆኖናል፤
:
ይሄው ስማኝማ በባቢሎን
ምክንያት ሀጥያታችን በዝቶ፤
:
ቋንቋ ልሳናችን ለይተህ ቃኝተካል
ግድ የለም አሁን ግን ቋንቋችንን ቀማን
እንዳደርስብህ ግንቡ ይሻልካል፤
:
ይሄው ስማኝማ አንተን ልናከብር
የፈጠርክልን አንደበት ተዘጋ፤
:
አንተን ዘንግተናል ውዳሲያችን ሁሉ
ዘሬ ዘሬ ሆኖል በነጋ በጠባ
:
ግን ግን ይህ ህመም ምንድን ነው?
እንደምን ልወቀው?
ህመሜን እንዳልውጥ
ስቃዩ በዛብኝ እንዴት ልደብቀው
:
:
ግድ የለም ንገሩኝ
ህመሜ ምንድነው?
:
ጠሃይዋን እያየው ብርድ ብርድ የሚለኝ
በረዶ እየጣለ ሙቀት የሚገለኝ
ከቶ ምን ሆኜ ነው?
:
ወባ ነው እንዳልል
አጎበር ዘርግቼ፤
ብርድ ነው እንዳልል
ልብስ ደራርቤ
እሳትም አንድጄ ቤቴንም ዘግቼ፤
:
ለምን ይበርደኛል?
:
ለምን ይሞቀኛል?
:
እጅ እግሬ ጉልበቴስ
ምን ሆንኩኝ ብሎ ነው
'ሚቆረጣጥመኝ?
ምን ሆንኩኝ ብዬ ነው
ስኳር የሚመረኝ እሬት የሚጥመኝ?
:
ምን እንደሆንኩ እንጃ
:
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን ደፍሬ
እንዲህ ያስብለኛል፤
:
በልሙጥ ሰማይ ላይ ሰንደቄን ስላየው
ኮከቡን አጥፋልኝ ብዬ እጠይቃለው
ስሙን ባላውቀውም እውነት ታምሚያለው፤
:
ካስርቱ ትዛዛት አንድ የጨመርክበት
አልያም ያጎደልከው ሆኖ እየተሰማኝ
ህግ ሻርክ ብዬ መበታተን ጠማኝ፤
እንዲህም አስባለው
ስሙን ባላውቀውም እውነት ታምሜአለሁ
፡
ምን እንደሆንኩ እንጃ!
:
ህመሜን መለየት
ማወቁን አላውቀው፤
እንዳው ዝም ብዬ ነው
ቁስሌን እያየሁ
ትናንት ዛሬም ነገም
ሁሌም ምጠይቀው፤
:
ኬት መጣ ይህ ቁስል?
የት ነው የተጋጋጥሁ?
ወዴት ልዘል ይሆን
እግሬን ተሰብሬ
የስቃይ ምጥ ያማጥሁ
:
ምን እንደሆንኩ እንጃ!
:
እየጠዘጠዘኝ
እየቀዘቀዘኝ
እየገዘገዘኝ
:
የኔ ሰው እርቆኝ
ነው ጠላት የገነዘኝ፤
እያልኩ አስባለው
:
ከወዳጄም ጥል ነኝ
ከጠሌቴም ጥል ነኝ
ከራሴም ጋር ጥል ነኝ
:
እውነት ታምሜአለሁ
:
እንዲያው ዝም ብዬ እንጂ
:
እንደታመምኩኝስ
እንዳልታመምኩኝስ
ከወዴት አውቄው፤
እንዳው ላመል እንጂ
ጠይቅ ስለተባልኩ
እንዲህ ምጠይቀው፤
:
እንደዚህ እያልኩኝ!
:
ህመሜን ሰው ሁሉ
ስም እያወጣለት፤
ለየትኛው ህመም ክኒን ልዋጥለት፤
ለየትኛው ህመም መርፌ ልወጋለት።
እንጃ!
ህመሜን ፍለጋ
ትኩሳት ነው ብለው
ሰዎች ይነግሩኛል፣
ራስ ምታት ነው ብለው
ይገምቱልኛል፣
:
ግማሹ እየመጣ
ጨጓራ ይዞሃል
ብሎ እየነገረኝ፤
ግማሹ ሰው ደግሞ
ኩላሊት አለብህ
ብሎ እየነገረኝ፤
ህመሜን ሰው ሁሉ
ስም እያወጣለት፤
ለየትኛው ህመም ክኒን ልዋጥለት፤
ለየትኛው ህመም መርፌ ልወጋለት።
:
ብቻ ይሄው ምልክቱ፣
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን ደፍሬ
እንዲህ ያስብለኛል፤
ለንፁሀኑ በደል
ለንፁሀኑ ደም ወርደህ እንድትፈርድ
በምነኛ እንፁም በምነኛ እንስገድ፤
በትግርኛ እንስገድ?
በአማርኛ እንስገድ?
በኦሮምኛ እንስገድ?
የቱ ነው ሚቀርብህ
የትኛው ነው ያንተ ብሔር ያሰኘኛል፤
ስሙ ጠፋኝ እንጂ እውነት ነው አሞኛል፤
:
ግን ግን ይህ ህመም ምንድን ነው?
እንደምን ልወቀው?
ህመሜን እንዳልውጥ
ስቃዩ በዛብኝ እንዴት ልደብቀው፤
:
ቸገረኝ!
:
እስኪ ታውቁ እንደሆን
የበሽታዬን ስም
ንገሩኝ ልለየው፤
ፍለጋው ነው እንጂ
ህመም ስቃዩ አይደል
ነፍሴን የሚለየው፤
:
ብቻ ይሄው ምልክቱ
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን
ደፍሬ እንዲህ ያስብለኛል፤
ጥበብ ያልከኝን ቃል
በቃሌ መዝገብ ላይ እየተረጎምኩኝ
ጠብቤ ጠብቤ ጎሳህን ዘረክን ብሄርክን ጠየኩኝ
ጌታ ግን ምንድን ነህ ?
ኦሮሞ
ጉራጌ
ሱማሌ
ሀረርጌ
ትግሬ ነህ አማራ፤
ቤተስኪያን አልሄድም
መስጊድም አልሄድም ዘርክን እስካጣራ
ማለትም ያምረኛል
ስሙ ጠፋኝ እንጂ እውነት ነው አሞኛል፤
ግን ግን ይህ ህመም ምንድን ነው?
እንደምን ልወቀው?
ህመሜን እንዳልውጥ
ስቃዩ በዛብኝ እንዴት ልደብቀው፤
:
ሞትማ ክብር ነው
ሞትማ 'ረፍት ነው
ቅር ቢሉት የማይቀር፤
ከነጥያቄዬ ወደ ሌላኛው ዓለም
መሄድ መጓዜ ግን
ሰላም እንዳይነሳኝ
ከነፍሴ ጋር ሄዶ እንዳይሰነቀር።
:
ብቻ ይሄው ምልክቱ
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን
ደፍሬ እንዲህ ያስብለኛል፤
:
በፈጠርካት ምድር ድንበር አበጅተን
የኔ ነው የኔ ነው ተባብለን አድረናል
ሁሉ ያንተ መሆኑን ዘንግተን ከኖርን
ብዙ አመት ሆኖናል፤
:
ይሄው ስማኝማ በባቢሎን
ምክንያት ሀጥያታችን በዝቶ፤
:
ቋንቋ ልሳናችን ለይተህ ቃኝተካል
ግድ የለም አሁን ግን ቋንቋችንን ቀማን
እንዳደርስብህ ግንቡ ይሻልካል፤
:
ይሄው ስማኝማ አንተን ልናከብር
የፈጠርክልን አንደበት ተዘጋ፤
:
አንተን ዘንግተናል ውዳሲያችን ሁሉ
ዘሬ ዘሬ ሆኖል በነጋ በጠባ
:
ግን ግን ይህ ህመም ምንድን ነው?
እንደምን ልወቀው?
ህመሜን እንዳልውጥ
ስቃዩ በዛብኝ እንዴት ልደብቀው
:
:
ግድ የለም ንገሩኝ
ህመሜ ምንድነው?
:
ጠሃይዋን እያየው ብርድ ብርድ የሚለኝ
በረዶ እየጣለ ሙቀት የሚገለኝ
ከቶ ምን ሆኜ ነው?
:
ወባ ነው እንዳልል
አጎበር ዘርግቼ፤
ብርድ ነው እንዳልል
ልብስ ደራርቤ
እሳትም አንድጄ ቤቴንም ዘግቼ፤
:
ለምን ይበርደኛል?
:
ለምን ይሞቀኛል?
:
እጅ እግሬ ጉልበቴስ
ምን ሆንኩኝ ብሎ ነው
'ሚቆረጣጥመኝ?
ምን ሆንኩኝ ብዬ ነው
ስኳር የሚመረኝ እሬት የሚጥመኝ?
:
ምን እንደሆንኩ እንጃ
:
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን ደፍሬ
እንዲህ ያስብለኛል፤
:
በልሙጥ ሰማይ ላይ ሰንደቄን ስላየው
ኮከቡን አጥፋልኝ ብዬ እጠይቃለው
ስሙን ባላውቀውም እውነት ታምሚያለው፤
:
ካስርቱ ትዛዛት አንድ የጨመርክበት
አልያም ያጎደልከው ሆኖ እየተሰማኝ
ህግ ሻርክ ብዬ መበታተን ጠማኝ፤
እንዲህም አስባለው
ስሙን ባላውቀውም እውነት ታምሜአለሁ
፡
ምን እንደሆንኩ እንጃ!
:
ህመሜን መለየት
ማወቁን አላውቀው፤
እንዳው ዝም ብዬ ነው
ቁስሌን እያየሁ
ትናንት ዛሬም ነገም
ሁሌም ምጠይቀው፤
:
ኬት መጣ ይህ ቁስል?
የት ነው የተጋጋጥሁ?
ወዴት ልዘል ይሆን
እግሬን ተሰብሬ
የስቃይ ምጥ ያማጥሁ
:
ምን እንደሆንኩ እንጃ!
:
እየጠዘጠዘኝ
እየቀዘቀዘኝ
እየገዘገዘኝ
:
የኔ ሰው እርቆኝ
ነው ጠላት የገነዘኝ፤
እያልኩ አስባለው
:
ከወዳጄም ጥል ነኝ
ከጠሌቴም ጥል ነኝ
ከራሴም ጋር ጥል ነኝ
:
እውነት ታምሜአለሁ
:
እንዲያው ዝም ብዬ እንጂ
:
እንደታመምኩኝስ
እንዳልታመምኩኝስ
ከወዴት አውቄው፤
እንዳው ላመል እንጂ
ጠይቅ ስለተባልኩ
እንዲህ ምጠይቀው፤
:
እንደዚህ እያልኩኝ!
:
ህመሜን ሰው ሁሉ
ስም እያወጣለት፤
ለየትኛው ህመም ክኒን ልዋጥለት፤
ለየትኛው ህመም መርፌ ልወጋለት።
እንጃ!