#ጸሎተ #ደቂቃን
አባ ያለህ በሰማይ
አባ አንተ ትልቁ
ከጡቶች ብቻ ሳይሆን
ወተቶች ካ'የር ይፍለቁ...
እንጠጣ ያለ አንዳች እቅፍ
ተይዞ መጥባት ይቅርልን
እየሮጥን የምንጠጣው
እየዳህን የምንረካው
ያ'የር ላይ ጡት ፍጠርልን።
እነኾም አደራ ጌታ
ይቅርልን የቀን መኝታ
ይቅርልን የሌሊት እንቅልፍ
እናቶቻችን አይተኙ
አባቶቻችንም ይንቁ
ደቂቅ ናቸው አይበሉን
ጮርቃነታችን አይናቁ
በገዛ ሕልሞቻችን ላይ
ፍቃድ እንዳለን ይወቁ።
በዛውም አደራ አባ
አባ የሰማያቱ
አልበላችሁም ብለው
አልተኛችሁም ብለው
ቁጠርባቸው ሲማቱ...
በደፋን በገፋን
በሰበርን ቁጥር
የሚዘረጋውን
እጃቸውን ቁጠር።
አባ እንደምታውቀው
ለራስ ልጅ ሲቆርሱ፥ ከቶ አያሳንሱም
ያንተ አባትነት፥ ነውና ለእነሱም
ይቀጡናልና፥ ስናጠፋባቸው
እንዳባትነትህ፥
ጥፋቶቻቸውን፥ አትለፍባቸው።
ረድኤት አ
አባ ያለህ በሰማይ
አባ አንተ ትልቁ
ከጡቶች ብቻ ሳይሆን
ወተቶች ካ'የር ይፍለቁ...
እንጠጣ ያለ አንዳች እቅፍ
ተይዞ መጥባት ይቅርልን
እየሮጥን የምንጠጣው
እየዳህን የምንረካው
ያ'የር ላይ ጡት ፍጠርልን።
እነኾም አደራ ጌታ
ይቅርልን የቀን መኝታ
ይቅርልን የሌሊት እንቅልፍ
እናቶቻችን አይተኙ
አባቶቻችንም ይንቁ
ደቂቅ ናቸው አይበሉን
ጮርቃነታችን አይናቁ
በገዛ ሕልሞቻችን ላይ
ፍቃድ እንዳለን ይወቁ።
በዛውም አደራ አባ
አባ የሰማያቱ
አልበላችሁም ብለው
አልተኛችሁም ብለው
ቁጠርባቸው ሲማቱ...
በደፋን በገፋን
በሰበርን ቁጥር
የሚዘረጋውን
እጃቸውን ቁጠር።
አባ እንደምታውቀው
ለራስ ልጅ ሲቆርሱ፥ ከቶ አያሳንሱም
ያንተ አባትነት፥ ነውና ለእነሱም
ይቀጡናልና፥ ስናጠፋባቸው
እንዳባትነትህ፥
ጥፋቶቻቸውን፥ አትለፍባቸው።
ረድኤት አ