አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
568 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የፈሪ_ሰው_ጸሎት

አምላክ ሆይ .
ይግባኝ ዐለኝና አቤት የምልበት
በአርባ አራት ጾሜ ሕግን 'ምሽርበት።
ለምን? የሚል ሐሳብ . . .
በመሸነፍ ብእር ልብ ወለድ ተደርሶ
ይጠይቃል ልቤ ከዙፋንኽ ደርሶ።

እዚኽ . . .
ሕግን እያወጣ ደንብ እያረቀቀ
ሕዝብ እያስከበረ እራሱ እየናቀ፣
ይበይንብኻል . . .!
አያድን ከቅጣት ሕግን ያላወቀ።
( . . . እያለ. . .)

( ፈተና ፩ )
ሠፊው የ'ኔ ዓለም . . .
ስልቻ ላይሞላ ሠርክ ፍዳ ኾነ
ሆድ የሚሉት ዋሻ ለግብሩ ታመነ ፣
ድንጋይን ከዳቦ እያፎካከረ
ኅሊናን ረስቶ ተገዛ ፣ታሰረ።

( ፈተና ፪ )
መከራዬ ኹሉ ዕንገት እያስደፋኝ
መንገዴ በሙሉ 0ጉኖ እያፋፋኝ ፣
ጠረጠርኩኝና ...
በኾነው በቀኑ መድረስኽን ረሳኹ ፤
በማወቅ ጉጉቴ . . .
ከመቅደስ ከፍታ ለመውደቅ ተነሣኹ።

( ፈተና ፫ )
ነባዊ . . .
ልባዊ . .
ሕያዊ . . .
መገመት ጀመሩ ፤ አንሰው ኮሰሱና
እሩጫው ዐየለ ፤ መስገድ እረሱና ፣
ሙዳይ መስፈራዬ አስገምቶኝ ከ'ኔ
ገዛኹ ፣ተገዛኹኝ ፤ በምድራዊው ቅኔ።

እናም . .
ልቤ ቃልን ስቶ
ለሥጋ ተገዝቶ
በዓለም ተመርቶ።
በሰው መኾን ግብር
አልችል ካለች ነፍሴ ፈተናውን ማለፍ፤
ይግባኝ ባሉት ብሂል ይቺ ጽዋ ትለፍ።

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘