#የነፍስ_ክረምት!
ከርስ የጎደለ እንደው ይሞሉታል በህል፤
የበረደም ዕለት..ኮት ያኮቱበታል የቁሩን ልክ ያህል።
ጤዛውን በጫማ ፤
ውርጩን በስብ ሸማ፤
ሌቱን በትኩስ ራት ፤
ደመናውን በሣት፤
አጉል የሰፈረን ወዲያልኝ ይሉታል፤
አልባሌን አየር ፤ ጢስ ይከልሉታል፡፡
ሙቀት ስጡኝ ለሚል..
ለበረደው ገላ ፤ መጋጋል ላነሰው፤
መድኃኒቱን አውቋል ፥ የተቃቀፈ ሰው ።
ግና!
ነፍስ የበረደ ዕለት፥ ምን ቤት ይጠልላል??
ለቀዘቀዘስ ልብ ፥ ማን ኮት ልሁን ይላል??
🔘ፓፒረስ🔘
ከርስ የጎደለ እንደው ይሞሉታል በህል፤
የበረደም ዕለት..ኮት ያኮቱበታል የቁሩን ልክ ያህል።
ጤዛውን በጫማ ፤
ውርጩን በስብ ሸማ፤
ሌቱን በትኩስ ራት ፤
ደመናውን በሣት፤
አጉል የሰፈረን ወዲያልኝ ይሉታል፤
አልባሌን አየር ፤ ጢስ ይከልሉታል፡፡
ሙቀት ስጡኝ ለሚል..
ለበረደው ገላ ፤ መጋጋል ላነሰው፤
መድኃኒቱን አውቋል ፥ የተቃቀፈ ሰው ።
ግና!
ነፍስ የበረደ ዕለት፥ ምን ቤት ይጠልላል??
ለቀዘቀዘስ ልብ ፥ ማን ኮት ልሁን ይላል??
🔘ፓፒረስ🔘
❤9👍7