#የትውልዱ_ድርሳን - 3
ቀረርቶው ጥላቻ ፣
ፉከራው ጭካኔ፣ ሽለላው ድንፋታ፤
መንፈሱ የታሰረ፣ አካሉ የተፈታ::
ልቦናን አስሮ፣ ለወስፋቱ ፈራጅ ፣
የገዛ ወንድሙን ፣ እንደሙክት አራጅ::
ፍቅሩ ያንዳፍታ፣
ህብረቱ ያንዳፍታ፣ የሳፋ ላይ ብቅል፤
መጽኛ ስር የነሳው ፣ መለምላሚያ ቅጠል፡፡
እድሩ የፈረሰ፣
አሟሟቱ ምጸት፣ መሾ ያነወረው ፤
በቁሙ የሞታ፣ ቀባሪ የቸገረው ፤
በጅምላ አሳቢ፣
በመንጋ ተዋጊ፣
የ'ራሱ ባላንጣ፣ ተስፋ የቆረጠ ፤
ሰብኣዊ ሚዛኑን፣ ለጎሳው የሸጠ፡፡
🔘በድሉ ዋቅጅራ🔘
የካቲት፣ 2011፣ አዲስ አበባ፡፡
ቀረርቶው ጥላቻ ፣
ፉከራው ጭካኔ፣ ሽለላው ድንፋታ፤
መንፈሱ የታሰረ፣ አካሉ የተፈታ::
ልቦናን አስሮ፣ ለወስፋቱ ፈራጅ ፣
የገዛ ወንድሙን ፣ እንደሙክት አራጅ::
ፍቅሩ ያንዳፍታ፣
ህብረቱ ያንዳፍታ፣ የሳፋ ላይ ብቅል፤
መጽኛ ስር የነሳው ፣ መለምላሚያ ቅጠል፡፡
እድሩ የፈረሰ፣
አሟሟቱ ምጸት፣ መሾ ያነወረው ፤
በቁሙ የሞታ፣ ቀባሪ የቸገረው ፤
በጅምላ አሳቢ፣
በመንጋ ተዋጊ፣
የ'ራሱ ባላንጣ፣ ተስፋ የቆረጠ ፤
ሰብኣዊ ሚዛኑን፣ ለጎሳው የሸጠ፡፡
🔘በድሉ ዋቅጅራ🔘
የካቲት፣ 2011፣ አዲስ አበባ፡፡