#የማያልቅ_ስጦታ
የካብኩት እየተናደ
የገመድኩትም ሲበጠስ
ያደመቅኩት እየፈዘዘ
ያነጽኩት ሁሉ ሲፈርስ
ደመናው ፀሐይ ሆኖብኝ
በመንገዴ እየተሰጣሁ
ከእንስራው ውሃ ጠፍቶ
ላቤን ከጉንጬ እየጠጣሁ
የበደሉኝን ይቅር ለማለት
ራሴን በራስ እየቀጣሁ
“ማነው?” ስባል “እኔ” የምል
የሰው ጥፋት የምሸከም
በኔ ይለፍ የምዘምር
እስክጠፋ የማልደክም
ሳይታሰብ እንደ መና
ከላይ ወርዶ የሚያወፍር
ስላለኝ ነው ታላቅ እውነት
ስላለኝ ነው አንዳች ክብር
ያንቺ ፍቅር...!
🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
የካብኩት እየተናደ
የገመድኩትም ሲበጠስ
ያደመቅኩት እየፈዘዘ
ያነጽኩት ሁሉ ሲፈርስ
ደመናው ፀሐይ ሆኖብኝ
በመንገዴ እየተሰጣሁ
ከእንስራው ውሃ ጠፍቶ
ላቤን ከጉንጬ እየጠጣሁ
የበደሉኝን ይቅር ለማለት
ራሴን በራስ እየቀጣሁ
“ማነው?” ስባል “እኔ” የምል
የሰው ጥፋት የምሸከም
በኔ ይለፍ የምዘምር
እስክጠፋ የማልደክም
ሳይታሰብ እንደ መና
ከላይ ወርዶ የሚያወፍር
ስላለኝ ነው ታላቅ እውነት
ስላለኝ ነው አንዳች ክብር
ያንቺ ፍቅር...!
🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
👍10❤5🔥1