#ከብጽእና_ጸብ.
‹‹ብጹእ ናቸው›› ሲል ወንጌሉ ፤
ሳያይ ያመነውን ሁሉ ፤
ሳያዩ አምኖ መገኘት ፤
ሳይሰፈሩ መመላት፣
ሳይፈተኑ ማለፍ አይነት፤
...........................ቢመስልም፤
የሚታየውን፣
ዶፍ
ጎርፍ፣ . , ከማመን፤
ለወና ሰማይ መመነን፤
. ........................ አይቀልም?
ግና
ሁለቱን ምን ለየው?!
አንደኛው መጸየፍ፣
ሌላው ግብዝነት፤
ዞሮ ዞሮ ሽንፈት!
🔘በድሉ ዋቅጅራ
🔘ሰኔ፣ 2012