አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#እገዛላታለሁ ... !!


#በአሌክስ_አብርሃም


ቆንጆ ማለት ለዓይን የሚማርክ፣ ለጆሮ የሚጥም፣ የሚያምር፣ የሚያስደስት፣ የሚያማልል፣ ሰው፣እንስሳ፣ ሳር፣ ቅጠል፣ አየር፣ ውሃ፣ ቃል፣ ሁኔታ፣ ድርጊት ሌላም መዓት ትርጉም ይኖረዋል፡፡
አሻሚ ነው ቃሉ፡፡ ውብ የሚለው ቃል ግን አያሻማም አያደናግርም፣ “ውብ” ማለት “እናቴ” ማለት ናት ! የእኔ እማማ ብቻ !!

አዎ እናቴ ውብ ናት !! በችግር የማይፈታ ውበት፡፡ ማንም በአድናቆት ቃል በእንቶፈንቶ ድለላ
ውሉን እጁ አስገብቶ የማይተረተረው ነጭ ቱባ ናት እማማ ፤ ፈገግ ስትል ከጥርሶቿ ድል ማድረግ በአካቤቢው ይነዛል፡፡ እንደ እናቴ ፈገግታ ልብ የሚሰነጥቅ ሳቅ አላየሁም፤ የእናቴ ፈገግታ ብርታቴ ነው፡፡ ሰውነቴ በፈገግታዋ ይታደሳል፡፡ የተፈጥሮ ፍልውሃ ነው ፈገግታዋ !!

ሕይወት ወገቧን አስራ ልታስለቅሳት ድንጋይ ስትፈነቅል እናቴ እማምዬ.የኔ ፀሐይ...በአንዲት
የአሽሙር ፈገግታ ትደቁሳታለች ፤ ሕይወት የጨለማ አረሟን በቤታችን ላይ ስትዘራ እናቴ
በፈገግታዋ ትመነጋግለውና የደስታ እና የሐሴት አዝመራ ቤታችን ይዘናፈላል፡፡እዛ ማሳ ውስጥ እኔ እቦርቃለሁ፡፡አውቆም ይሁን ሳያውቅ አባቴ ቤታችንን የምድር ዋልታ ላይ በበረዶ ገነባው፤ እናቴ በፈገግታ ገመድ ጎትታ መሃል አዲስ አበባ፣ አራት ኪሎ፣ ፀሐይ የሞላበት አመጣችው ቤቱን ከነግቢው ከነዛፉ !! እንደዛ ነው የሚሰማኝ፡፡

አባቴ በውትድርና ኤርትራ ሄደ፡፡
“እነከሌ አገር ሊገነጥሉ፣ መሬት ሊሸርፉ ነውና ሄደህ ልክ
አግባቸው!” በሚል ትዕዛዝ ከእኔ ከአንድ ልጁና ከሚወዳት ሚስቱ ተነጥሎ ሄደ :: “.…አቤት
ቁመና ! አቤት የትጥቅ ማማር !” እያለ ጎረቤቱ ሸኘው፡፡ አምሮ ሊገድል፣ አምሮ ሊሞት አባቴ፡፡
ሕፃን ነበርኩ፤ ብዥ ያለ ነው ትዝታዬ፡፡ አባቴ ሄደ፤ (ዘመተ ይሉታል)፡፡ ስልክ የለም፤ ደብዳቤ
የለም፤ ሄደና ጠፋ፡፡

እናቴ ታዲያ በፍፁም ንፅህና
ስድስት ዓመት ጠበቀችው:: ያውም በደጃችን፡ በእናቴ ውበት
መቶ ጀኔራል እየሸለለ፣ ሺ ካድሬ እየቋመጠ፣ ሚሊዩን አብዮት ጠባቂ ምራቁን እየዋጠ !!
"ንፅህናዋን በምን አወቅክ ?” ስድስት ዓመት ሙሉ ማታ ማታ አንዲት ቀን ሳታቋርጥ ፎቶው
ፊት ተንበርክካ ምን እያለች ትፀልይ እንደነበር እናንተ ታውቃላችሁ ? የአባቴን ፎቶ አቧራ ዝር እንዳይልበት በቀን ስንት ጊዜ ትወለውለው እንደነበርስ…?
ከቤታችን ዕቃዎች ውድ የተባለው መደርደሪያ ላይ ምን ይቀመጥ እንደነበርስ ? የአባቴ ፎቶ !! በዛ ናፍቆት በረበበት፣ ምስኪን እናትና ልጅ ምዕመን በሆኑበት፣ የብቸኝነት ቤተ መቅደስ ውስጥ የአባቴ ፎቶ ፅላት ነበር፡፡
አባቴ ፎቶ ጎን ተሳስቼ ደብተሬን ሳስቀምጥ ሳታስደነግጠኝ ቀስ ብላ ታነሳዋለች ፡፡ ቤት ለማዘጋጀት
እንዳይመስላችሁ፣ አባቴ ፎቶ አጠገብ ምንም እንዳይቀመጥ እንጂ !! እማማ የቃል ኪዳን
ቀለበቷን ሽጣ ምን ገዛች? ለኔ ቆንጆ ጫማና ልብስ ፣ ምድረ የትምህርት ቤት ማቲ የቀናበት
የደብተር መያዣ ቦርሳ ፣ ለአባቴ ፎቶ ወርቃማ የብረት ከፈፍ ያለው ባለመስታዋት የፎቶ ማስቀመጫ፤ በተረፈችው የቃል ኪዳን ቀለበቷን የምትመስል አርቴፊሻል ቀለበት ፡፡ በእንቁ ልብና በአርቴፊሻል ቀለበት ቃል ኪዳኗን አጠረች፤ ከእኔ በስተቀር ይሄንን ማንም አያውቅም::ለራሷስ ምን ገዛች?…ምንም !! እች ናት እናቴ!!

ስድስት ዓመት አባቴን ጠበቀችው ይሄ ሊመጣ ይችላል ተብሎ እዛም እዚህም እየተባለ የሚጠበቀው ዓይነት ጥበቃ ሳይሆን 'መቼ ሄደና' ብሎ ክችች የሚሉት አይነት የመንፈስ አብሮነት
በሌሉበት ማከበር !! ..ይሄ የመጀመሪያው ዓመት ላይ “ሄደብኝ የኔ ጌታ የልቤ ቁራሽ የደሜ ጭላፊ…" እያሉ ጎረቤት እንዲያባብል ድራማ መስራት፣ ዓመት በጨመረ ቁጥር 'አሁን ተፅናናች ሰው መቅረብ ጀመረች የሚባለው አይነት መጠበቅ ሳይሆን፣ ትላንትም ዛሬም ዓመታት ጉልበቱን በማይሰልቡት ጥልቅ መሻት ጠበቀችው:: ይህች ናት እናቴ!!

ስለ ኤርትራ በተወራ ቁጥር ኪሎ ስጋ ከአካሏ እየተገነጠለ ጠበቀች :: “ከኤርትራ የመጣ ሰው
በኮተቤ አለፈ" ሲሏት ነጠላዋን አንጠልጥላ ኮተቤ ትገኛለች፡፡” እንዲት ኤርትራዊት ተፈናቃይ
አቃቂ ኪዬስክ ከፈተች” ሲባል ከአራት ኪሎ እየተመላለሰች የስሙኒ ሻይ ቅጠል ለመግዛት
ደንበኛ የምትሆን ሴት ካለች እናቴ ብቻ ነበረች፡፡ እች ናት እማማ!!

እርጋታዋ የእኔ እማማ በእልፍ ሲሉ እልፍ ይገኛል” ተረት እልፍኛቸው ውስጥ ተሳላፊ እንደሚያበዙ ሴቶች አይደለችም ፤ ማንም የቃል ኪዳን መስመሯን አያልፍም፤ አገር ያውቃል፡ቤታችን ቤተ መቅደስ ነው፡፡ የፍቅር ፅላት በቅዱሰ ቅዱሳን እማማ ልብ ውስጥ አለ፡፡ እርጋታዋ ታማኝነቷን ይነግረኛል፡፡ ዓይኗ ከአባቴ ፎቶ ላይ ከተነቀለ ቀጥሎ ማረፊያው እኔ ላይ ነው፡፡
ጆሮዋ ወደ ውጭ አይቀሰርም፡፡ የኔን አርቲ ቡርቲ ወሬ እንደወንጌል በጥሞና መስማት የነፍሷ
እርካታ ነው፡፡ አባባ መጽሐፍ ቅዱስ፣ እኔ ዮሐንስ ራዕይዋ ታነበኛለች፣ ሰባት ቀንድ፣ እስራ
ስድስት ምላስ፣ ምንም ጆሮ የሌላቸው ልዩ ፍጥረቶች መሐል እናቴ ጆሮ ብቻ ሆና ትሰማኛለች ...!!

ጥቁር ፀጉሯ ሲዘናፈል፣ እንደማር የለሰለሰ ቆዳዋ አላፊ አግዳሚ ሲጠራ፣ ረጋ ባለ እርምጃ እንደ
ደመና ስትንሳፈፍ፣ “ፈዛዛ ውበቷን አቀለጠችው” ይሏታል፡፡ “ጎታታ እንደ ኤሊ ስትንቀረፈፍ
እድሜዋን ፈጀች” ይሏታል፡፡ በሌጣ ልባቸው ሮጠው ምናምን ስለቃረሙ የፈጠኑ የመስላቸው
የመንደራችን ከንቱ ሐሜተኞች፡፡ የፍቅር መስቀል ተሸክማ ዳገት የምትወጣ እናቴን ኤሊ ይሏታል፤
አፍ አውጥተው ኤሊ ይሏታል፡፡ የድንጋይ ልባሷ አንደነሱ ቀሚስ የትም ለማንም አለመገለቡ
እያበገናቸው፣ ተኳኩለው የሚጠብቋቸው ወታደር ውሽሞቻቸው ያልተኳኳለች እናቴን እያዩ
«ማናት ይህች ቆንጆ ?” ሲሏቸው እየበሸቁ…::

እማማዬ ስድስት ዓመት ጠበቀችው አባቴን፡፡ “ይኼኔ ባሏ ከአስመራ ቆንጆዎች ጋር አሸሼ ገዳሜ እያለ ነው፣ እሷ እዚህ ጉልበቷን አቅፋ ትጠራሞታለች” እያሏት ጎረቤቶቻችን፤ አስመራ አድረው ጧት አዲስ አበባ የገቡ ይመስል፡፡ “ለታመነልህ ታመን” የቆሸሸ ዲስኩራቸው “በአልታመኑልንም” ሰበብ ባሎቻቸውን እንዲክዱ፣ ፍቅረኞቻቸውን እንዲቀጥፉ መንገድ እየጠረገላቸው፣ ለውስጣቸው ግልሙትና ጥቅስ እየሆነላቸው፣ “የአስመራን ግልሙትና በአዲስ አበባ ግልሙትና መበቀል ፅድቅ
ነው" የተባለ ይመስል እማምዬን “ባልሽ ወንድ ነው አትመኝው” ይሏታል፡፡

እንድ ማለዳ በራችን ተንኳኳ፡፡ እማማ ከፈተች፡፡ ጎረቤቶቻችን አንድ የተጎሳቆለ ወታደር
አስከትለው መጡና “ባልሽ ሞቷል” አሏት :: “በዚህ ወርዶ በዚያ ሂዶ፣ መድፍ ተኩሶ፣ ታንክ
ማርኮ፣ በጀግንነት ሞተ !” አሏት፡፡ ዝም ብላ ሰማቻቸው፡፡ “ሰው ቀጥ ብሎ የማያይ ጨዋ፣ለትዳሩ ታማኝ፣ ወታደሩ ሁሉ እዛና እዚህ ሲል ባልሽ ግን የአንቺን ፎቶ ከደረት ኪሱ ሳይለይ
በየበረሃው ለእዝ ሲፋለም ኖሮ ሞተ” አሏት፡፡ ዝም ብላ ሰማቻቸው፡፡

አባቴ ሲሞት “ከጎኑ ነበርኩ” ያለው ጎስቋላ ወታደር ከአባቴ ሬሳ ኪስ ውስጥ አገኘሁት ያለውን
ፎቶ ሰጣት፡፡ እናቴና አባቴ ጎን ለጎን ሆነው የተነሱት ጉርድ ፎቶ ግራፍ ነበር፡፡ ልክ መሀላቸው
👍30🔥1👏1