#እኔ_አንዳንዴ_ስሰጥ
ኑሮ ለገረፈው ፤ በችግር አለንጋ
በረሃብ ጠውልጎ፤ እጁን ለዘረጋ
በመከራ ስለት፤ ጎኑን ለተወጋ
ለዚህ ብሶተኛ፤
ለዚህ ጉዳተኛ፤
ጥቂት ልመፀውት፤ ከኪሴ እገባለሁ
ከብሮች መካከል፤ብሮች አወጣለሁ
አምስት ብርአውጥቼ፤ልሰጠው እልና
እኒህ አምስት ብሮች፤ ይበዙብኝና
አራቱን ለመስጠት፤ጥቂት ሳሰላስል
'ለእኔ አይበዛብኝም ለእሱ ይበዛል' ስል
ሶሥት ብር ለመስጠት፤ውሳኔ ደርሼ
'ጎዶሎ አይሰጥም፤ እልና መልሼ
በሁለት ብሮች ላይ፤ፍርዴን እሰጣለሁ
ፍርዴን ግን መልሼ፤ እከልሰዋለሁ
ሁለት ብር ከምሰጥ፤ ለመንገድ ልመና፤
አንዳንድ እንካፈል፤ ብዬ እወስንና
'አንድ ብር ብሰጠው፤ለዚህ ብሶኛ
ሆላ ቢጠጣበቸፈት፤ እያልኩ አስብና
ያችን አንድ ብርም፤ ኪሴ እከታታለሁ እግዚአብሔር ይስጥልኝ!" ብዬው እሄዳለው
ኑሮ ለገረፈው ፤ በችግር አለንጋ
በረሃብ ጠውልጎ፤ እጁን ለዘረጋ
በመከራ ስለት፤ ጎኑን ለተወጋ
ለዚህ ብሶተኛ፤
ለዚህ ጉዳተኛ፤
ጥቂት ልመፀውት፤ ከኪሴ እገባለሁ
ከብሮች መካከል፤ብሮች አወጣለሁ
አምስት ብርአውጥቼ፤ልሰጠው እልና
እኒህ አምስት ብሮች፤ ይበዙብኝና
አራቱን ለመስጠት፤ጥቂት ሳሰላስል
'ለእኔ አይበዛብኝም ለእሱ ይበዛል' ስል
ሶሥት ብር ለመስጠት፤ውሳኔ ደርሼ
'ጎዶሎ አይሰጥም፤ እልና መልሼ
በሁለት ብሮች ላይ፤ፍርዴን እሰጣለሁ
ፍርዴን ግን መልሼ፤ እከልሰዋለሁ
ሁለት ብር ከምሰጥ፤ ለመንገድ ልመና፤
አንዳንድ እንካፈል፤ ብዬ እወስንና
'አንድ ብር ብሰጠው፤ለዚህ ብሶኛ
ሆላ ቢጠጣበቸፈት፤ እያልኩ አስብና
ያችን አንድ ብርም፤ ኪሴ እከታታለሁ እግዚአብሔር ይስጥልኝ!" ብዬው እሄዳለው