#ቀጥረሽኝ_ፈላስፋ_አደረግሽኝ
“ላገኝህ” ስትዪኝ...
በፊትሽ ለማመር ፥ በፊትሽ ልነጣ
ልብሴን አጣጥቤ ፥ ገመድ ላይ ሳሰጣ
ደመናው ኬ'ት መጣ?
አርፍጄ እንዳላጣሽ ፡ ስፈራ ስሳቀቅ
ልብሴን በ'ላዬ ላይ
በእግር መንገድ ላደርቅ
ስራመድ እየሮጥኩ
መንገዱ አጠረ ፥ ካልሽኝ ቦታ ደረስኩ፡፡
ሰዓቱ እስኪደርስ ፥ ሰዓት እየፈጀሁ
በምናብ ገፄ ላይ
ስትመጭ የምልሽን ፥ ቃል እያዘጋጀሁ
ካንቺ ጋራ ስሆን
እንዴት እንደምሔድ ፥ አካሔድ ሳጠና
አንዴ አንገት ስሰብር ፥ አንዴ አንገት ሳቀና
አንዱ እግሬን ስጎትት ፥ አንዱ እግሬን ሳነጥር
ቀፈቴን ስደብቅ ፥ ደረቴን ስወጥር
እንደድሮ ለኪ ፥ እርምጃ ስቆጥር
ጫማዬን ነደለው ፥ አገኘኝ እንቅፋት
ሰአቱ ገና ነው!
ሊስትሮ ጋር ሔድኩኝ ፥ ጫማ ለማሰፋት፡፡
ሊስትሮው ...
በወስፌ መንጠቆው ፥ ጅማቱን ይጠልፋል
ቀዳዳ እያበጀ ፥ ቀዳዳ ይሰፋል
ይለኛል ጫማዬ !
“የህይወት ትንሽ ሽንቁር
ጊዜና ግመልን ፥ እኩል ያሳልፋል፡፡
ሰአቴን አየሁት
ከቀጠርሽኝ ሰአት ፥ ጥቂት ደቂቃ አልፏል፡፡
እየተጣደፍኩኝ….
ያልሽኝ ቦታ እስክደርስ
እስካገኝሽ ድረስ
ቅድም ያጠረብኝ...
እዛው በዛው ሆኖ ፥ ራቀኝ መንገዱ
መድረስ ተረት ሆነ ፥ “ሲሔዱ ሲሔዱ
ሲሔዱ ሲሔዱ
ሲሔዱ ሲሔዱ ፥ መንገዱ አያልቅም
ሳጣሽ ተፈላሰፍኩ…
“መፈለግ ነው” ብዬ ፥ የፍልስፍና አቅም፡፡
እፈላሰፋለሁ!
ልብሴን ስዳብሰው ፥ እላዬ ላይ ደርቋል
ሰማዩን አየሁት ፥ ደመናው ተፍቋል
መንገዱ ቅድም ላይ ፥ ልሔደው ስል ያልቃል
አሁን ላይ ስሔደው...
ስሔደው ስሔደው ፥ ስሔደው ይርቃል፡፡
ወደ ጫማዬ ሳይ ፥ አንድ እግሬ ነው ባዶ
ሊስትሮው እጅ ላይ
ትቼው መጥቻለሁ ፥ ያልሽኝ ሰአት ሔዶ
የህይወትን ሽንቁር
ላይጠግን ይሰፋል ፥ በወስፌ ተቀዶ።
እፈላሰፋለሁ !
ቀድሜ መጥቼ ፥ በማርፈዴ ሳጣ
በጣም ከቀደመ
እጅጉን ይሻላል ፥ አርፍዶ የመጣ፡፡
እፈላሰፋለሁ!
ሰው የሚሉት ፍጡር..
ነፍስ ከስጋ ጋር ፥ እኩል ሲሞግተው
ፍፁም ልሁን ሲል ነው ፥ ፍፁም የሚስተው፡፡
እፈላሰፋለሁ !
ቀድሜሽ መጥቼ ፥ አርፍጃለሁ ሳውቀው
እፈላሰፋለሁ!
ቀድመው ሲያረፍዱ ነው መንገድ የሚርቀው
እፈላሰፋለሁ!!!
የሚጠነቀቅ ነው ፥ ማይጠነቀቀው!!
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
“ላገኝህ” ስትዪኝ...
በፊትሽ ለማመር ፥ በፊትሽ ልነጣ
ልብሴን አጣጥቤ ፥ ገመድ ላይ ሳሰጣ
ደመናው ኬ'ት መጣ?
አርፍጄ እንዳላጣሽ ፡ ስፈራ ስሳቀቅ
ልብሴን በ'ላዬ ላይ
በእግር መንገድ ላደርቅ
ስራመድ እየሮጥኩ
መንገዱ አጠረ ፥ ካልሽኝ ቦታ ደረስኩ፡፡
ሰዓቱ እስኪደርስ ፥ ሰዓት እየፈጀሁ
በምናብ ገፄ ላይ
ስትመጭ የምልሽን ፥ ቃል እያዘጋጀሁ
ካንቺ ጋራ ስሆን
እንዴት እንደምሔድ ፥ አካሔድ ሳጠና
አንዴ አንገት ስሰብር ፥ አንዴ አንገት ሳቀና
አንዱ እግሬን ስጎትት ፥ አንዱ እግሬን ሳነጥር
ቀፈቴን ስደብቅ ፥ ደረቴን ስወጥር
እንደድሮ ለኪ ፥ እርምጃ ስቆጥር
ጫማዬን ነደለው ፥ አገኘኝ እንቅፋት
ሰአቱ ገና ነው!
ሊስትሮ ጋር ሔድኩኝ ፥ ጫማ ለማሰፋት፡፡
ሊስትሮው ...
በወስፌ መንጠቆው ፥ ጅማቱን ይጠልፋል
ቀዳዳ እያበጀ ፥ ቀዳዳ ይሰፋል
ይለኛል ጫማዬ !
“የህይወት ትንሽ ሽንቁር
ጊዜና ግመልን ፥ እኩል ያሳልፋል፡፡
ሰአቴን አየሁት
ከቀጠርሽኝ ሰአት ፥ ጥቂት ደቂቃ አልፏል፡፡
እየተጣደፍኩኝ….
ያልሽኝ ቦታ እስክደርስ
እስካገኝሽ ድረስ
ቅድም ያጠረብኝ...
እዛው በዛው ሆኖ ፥ ራቀኝ መንገዱ
መድረስ ተረት ሆነ ፥ “ሲሔዱ ሲሔዱ
ሲሔዱ ሲሔዱ
ሲሔዱ ሲሔዱ ፥ መንገዱ አያልቅም
ሳጣሽ ተፈላሰፍኩ…
“መፈለግ ነው” ብዬ ፥ የፍልስፍና አቅም፡፡
እፈላሰፋለሁ!
ልብሴን ስዳብሰው ፥ እላዬ ላይ ደርቋል
ሰማዩን አየሁት ፥ ደመናው ተፍቋል
መንገዱ ቅድም ላይ ፥ ልሔደው ስል ያልቃል
አሁን ላይ ስሔደው...
ስሔደው ስሔደው ፥ ስሔደው ይርቃል፡፡
ወደ ጫማዬ ሳይ ፥ አንድ እግሬ ነው ባዶ
ሊስትሮው እጅ ላይ
ትቼው መጥቻለሁ ፥ ያልሽኝ ሰአት ሔዶ
የህይወትን ሽንቁር
ላይጠግን ይሰፋል ፥ በወስፌ ተቀዶ።
እፈላሰፋለሁ !
ቀድሜ መጥቼ ፥ በማርፈዴ ሳጣ
በጣም ከቀደመ
እጅጉን ይሻላል ፥ አርፍዶ የመጣ፡፡
እፈላሰፋለሁ!
ሰው የሚሉት ፍጡር..
ነፍስ ከስጋ ጋር ፥ እኩል ሲሞግተው
ፍፁም ልሁን ሲል ነው ፥ ፍፁም የሚስተው፡፡
እፈላሰፋለሁ !
ቀድሜሽ መጥቼ ፥ አርፍጃለሁ ሳውቀው
እፈላሰፋለሁ!
ቀድመው ሲያረፍዱ ነው መንገድ የሚርቀው
እፈላሰፋለሁ!!!
የሚጠነቀቅ ነው ፥ ማይጠነቀቀው!!
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
👍1
#ቀጥረሽኝ....ፈላስፋ አደረግሽኝ
ላገኝህ ስትዪኝ...
በፊትሽ ለማመር ፣ በፊትሽ ልነጣ
ልብሴን አጣጥቤ ፣ ገመድ ላይ ሳሰጣ
ደመናው ኬት መጣ?
አርፍጄ እንዳላጣሽ ፣ ስፈራ ስሳቀቅ
ልብሴን በላዬ ላይ
በእግር መንገድ ላደርቅ
ስራመድ እየሮጥኩ
መንገዱ አጠረ ፣ ካልሽኝ ቦታ ደረስኩ፡፡
ሰአቱ እስኪደርስ ፤ ሰአት እየፈጀሁ
በምናብ ገፄ ላይ
ስትመጭ የምልሽን ፣ ቃል እያዘጋጀሁ
ካንቺ ጋራ ስሆን...
እንዴት እንደምሔድ ፣ አካሔድ ሳጠና
አንዴ አንገት ስሰብር ፣ አንዴ አንገት ሳቀና
አንዴ እግሬን ስጎትት፣ አንዴ እግሬን ሳነጥር
ቀፈቴን ስደብቅ ፣ ደረቴን ስወጥር
እንደድሮ ለኪ ፣ እርምጃ ስቆጥር
ጫማዬን ነደለው ፣ አገኘኝ እንቅፋት
ሰአቱ ገና ነው...
ሊስትሮ ጋ ሔድኩኝ ፣ ጫማ ለማሰፋት፡፡
ሊስትሮው...
በወስፌ መንጠቆው ፣ ጅማቱን ይጠልፋል
ቀዳዳ እያበጀ ፣ ቀዳዳ ይሰፋል
ይለኛል ጫማዬ...
የህይወት ትንሽ ሽንቁር...
ጊዜና ግመልን ፣ እኩል ያሳልፋል፡፡
ሰአቴን አየሁት ፣
ከቀጠርሽኝ ሰአት ፣ ጥቂት ደቂቃ አልፏል፡፡
እየተጣደፍኩኝ...
ያልሽኝ ቦታ እስክደርስ
እስካገኝሽ ድረስ
ቅድም ያጠረብኝ...
እዛው በዛው ሆኖ ፣ ራቀኝ መንገዱ
መድረስ ተረት ሆነ ፣ ሲሔዱ ሲሔዱ
ሲሔዲ ሲሔዱ
ሲሔዱ ሲሔዱ ፣ መንገዱ አያልቅም
ሳጣሽ ተፈላሰፍኩ...
መፈለግ ነው ብዬ ፣ የፍልስፍና አቅም፡፡
እፈላሰፋለሁ!
ልብሴን ስዳብሰው ፣ እላዬ ላይ ደርቋል
ሰማዩን አየሁት ፣ ደመናው ተፍቋል
መንገዱ ቅድም ላይ ፣ ልሔደው ስል ያልቃል
አሁን ላይ ስሔደው...
ስሔደው ስሔደው ፣ ስሔደው ይርቃል፡፡
ወደ ጫማዬ ሳይ ፣ አንድ እግሬ ነው ባዶ
ሊስትሮው እጅ ላይ....
ትቼው መጥቻለሁ ፣ ያልሽኝ ሰአት ሔዶ
የህይወትን ሽንቁር...
ላይጠግን ይሰፋል ፣ በወስፌ ተቀዶ፡፡
እፈላሰፋለሁ...
ቀድሜ መጥቼ ፣ በማርፈዴ ሳጣ
በጣም ከቀደመ....
እጅጉን ይሻላል ፣ አርፍዶ የመጣ፡፡
ሰው የሚሉት ፍጡር...
ነፍስ ከስጋ ጋር ፣ እኩል ሲሞግተው
ፍፁም ልሁን ሲል ነው ፣ ፍፁም የሚስተው፡፡
እፈላሰፋለሁ...
ቀድሜሽ መጥቼ ፣ አርፍጃለሁ ሳውቀው
እፈላሰፋለሁ!
ቀድመው ሲያረፍዱ ነው ፣ መንገድ የሚርቀው
እፈላሰፋለሁ!!!
የሚጠነቀቅ ነው ፣ ማይጠነቀቀው!!!
በላይ በቀለ ወያ
ላገኝህ ስትዪኝ...
በፊትሽ ለማመር ፣ በፊትሽ ልነጣ
ልብሴን አጣጥቤ ፣ ገመድ ላይ ሳሰጣ
ደመናው ኬት መጣ?
አርፍጄ እንዳላጣሽ ፣ ስፈራ ስሳቀቅ
ልብሴን በላዬ ላይ
በእግር መንገድ ላደርቅ
ስራመድ እየሮጥኩ
መንገዱ አጠረ ፣ ካልሽኝ ቦታ ደረስኩ፡፡
ሰአቱ እስኪደርስ ፤ ሰአት እየፈጀሁ
በምናብ ገፄ ላይ
ስትመጭ የምልሽን ፣ ቃል እያዘጋጀሁ
ካንቺ ጋራ ስሆን...
እንዴት እንደምሔድ ፣ አካሔድ ሳጠና
አንዴ አንገት ስሰብር ፣ አንዴ አንገት ሳቀና
አንዴ እግሬን ስጎትት፣ አንዴ እግሬን ሳነጥር
ቀፈቴን ስደብቅ ፣ ደረቴን ስወጥር
እንደድሮ ለኪ ፣ እርምጃ ስቆጥር
ጫማዬን ነደለው ፣ አገኘኝ እንቅፋት
ሰአቱ ገና ነው...
ሊስትሮ ጋ ሔድኩኝ ፣ ጫማ ለማሰፋት፡፡
ሊስትሮው...
በወስፌ መንጠቆው ፣ ጅማቱን ይጠልፋል
ቀዳዳ እያበጀ ፣ ቀዳዳ ይሰፋል
ይለኛል ጫማዬ...
የህይወት ትንሽ ሽንቁር...
ጊዜና ግመልን ፣ እኩል ያሳልፋል፡፡
ሰአቴን አየሁት ፣
ከቀጠርሽኝ ሰአት ፣ ጥቂት ደቂቃ አልፏል፡፡
እየተጣደፍኩኝ...
ያልሽኝ ቦታ እስክደርስ
እስካገኝሽ ድረስ
ቅድም ያጠረብኝ...
እዛው በዛው ሆኖ ፣ ራቀኝ መንገዱ
መድረስ ተረት ሆነ ፣ ሲሔዱ ሲሔዱ
ሲሔዲ ሲሔዱ
ሲሔዱ ሲሔዱ ፣ መንገዱ አያልቅም
ሳጣሽ ተፈላሰፍኩ...
መፈለግ ነው ብዬ ፣ የፍልስፍና አቅም፡፡
እፈላሰፋለሁ!
ልብሴን ስዳብሰው ፣ እላዬ ላይ ደርቋል
ሰማዩን አየሁት ፣ ደመናው ተፍቋል
መንገዱ ቅድም ላይ ፣ ልሔደው ስል ያልቃል
አሁን ላይ ስሔደው...
ስሔደው ስሔደው ፣ ስሔደው ይርቃል፡፡
ወደ ጫማዬ ሳይ ፣ አንድ እግሬ ነው ባዶ
ሊስትሮው እጅ ላይ....
ትቼው መጥቻለሁ ፣ ያልሽኝ ሰአት ሔዶ
የህይወትን ሽንቁር...
ላይጠግን ይሰፋል ፣ በወስፌ ተቀዶ፡፡
እፈላሰፋለሁ...
ቀድሜ መጥቼ ፣ በማርፈዴ ሳጣ
በጣም ከቀደመ....
እጅጉን ይሻላል ፣ አርፍዶ የመጣ፡፡
ሰው የሚሉት ፍጡር...
ነፍስ ከስጋ ጋር ፣ እኩል ሲሞግተው
ፍፁም ልሁን ሲል ነው ፣ ፍፁም የሚስተው፡፡
እፈላሰፋለሁ...
ቀድሜሽ መጥቼ ፣ አርፍጃለሁ ሳውቀው
እፈላሰፋለሁ!
ቀድመው ሲያረፍዱ ነው ፣ መንገድ የሚርቀው
እፈላሰፋለሁ!!!
የሚጠነቀቅ ነው ፣ ማይጠነቀቀው!!!
በላይ በቀለ ወያ
👍1