#ላባቴ
ስው ብቻ እይደለህም፥ ካፈር ወጥተህ ላፈር
መላክ ነህ፥ ሉሲፈር
ክብርህ ማንነትህ፥ ባመጽ የሚታፈር
የማትንበረከክ
የማትርመጠመጥ
ከባለጌ ዙፋን፥ በርጩማ የምትመርጥ፤
ያለ ባሕር ሰርጓጅ፥ ያለ ሙሴ በትር
በመታገሰ ብቻ፥ ባሕር የምትመትር
ካዘልከኝ ጀምሮ፥ እንኮኮ ጫንቃህ ላይ
ከፍታውን እንጅ፥ ዝቅታውን ሳላይ
እንደንስር መጠቅሁ፥ እንደ ምሥራቅ በራሁ
የገዛ ክንፎቼን፥ እንደ ዳንቴል ሠራሁ፤
በርግጥ ድሀ ነበርክ
ከሰላምታ በቀር፥ የማታበረክት
ነጠላህ መናኛ፥ ሰውነትህ የክት፤
በርግጥ ድሀ ነበርክ፥ የነጣህ የጠራህ
ከጦር ሜዳ ይልቅ፥ ገበያ ሚያስፈራህ
ቤሳ ባታወርሰኝ፥ አወረስከኝ ትግል
የትም እንዳይጥለኝ፥ ሕይወት እንደ ፈንግል፤
አባዬ ብርሃን
አባ የምሥራቅ በር
ገመና ሸሻጊ፥ እንደ ካባ ጎበር
አባቴ ባትሆን፥ ምን ይውጠኝ ነበር።
ስው ብቻ እይደለህም፥ ካፈር ወጥተህ ላፈር
መላክ ነህ፥ ሉሲፈር
ክብርህ ማንነትህ፥ ባመጽ የሚታፈር
የማትንበረከክ
የማትርመጠመጥ
ከባለጌ ዙፋን፥ በርጩማ የምትመርጥ፤
ያለ ባሕር ሰርጓጅ፥ ያለ ሙሴ በትር
በመታገሰ ብቻ፥ ባሕር የምትመትር
ካዘልከኝ ጀምሮ፥ እንኮኮ ጫንቃህ ላይ
ከፍታውን እንጅ፥ ዝቅታውን ሳላይ
እንደንስር መጠቅሁ፥ እንደ ምሥራቅ በራሁ
የገዛ ክንፎቼን፥ እንደ ዳንቴል ሠራሁ፤
በርግጥ ድሀ ነበርክ
ከሰላምታ በቀር፥ የማታበረክት
ነጠላህ መናኛ፥ ሰውነትህ የክት፤
በርግጥ ድሀ ነበርክ፥ የነጣህ የጠራህ
ከጦር ሜዳ ይልቅ፥ ገበያ ሚያስፈራህ
ቤሳ ባታወርሰኝ፥ አወረስከኝ ትግል
የትም እንዳይጥለኝ፥ ሕይወት እንደ ፈንግል፤
አባዬ ብርሃን
አባ የምሥራቅ በር
ገመና ሸሻጊ፥ እንደ ካባ ጎበር
አባቴ ባትሆን፥ ምን ይውጠኝ ነበር።
#ላባቴ
የማትንበረከክ
የማትርመጠመጥ
ከባለጌ ዙፋን
በርጩማ የማትመርጥ፡፡
ያለ ባህር ሰርጓጅ ያለ ሙሴ በትር
በመታገስ ብቻ ፣ባህር የምትመትር፡፡
ካዘልከኝ ጀምሮ ፣እንኮኮ ጫንቃህ ላይ
ከፍታውን እንጅ፣ ዝቅታውን እንዳላይ
እንደ ንሥር መጠቅሁ፣ እንደ ምስራቅ በራሁ
የገዛ ክንፎቼን ፣እንደ ዳንቴል ሠራሁ፡፡
በርግጥ ደሀ ነበርህ…
ከሰላምታ በቀር የማታበረክት
ነጠላህ መናኛ፣ሰውነትህ የክት
በርግጥ ድሀ ነበርህ
የነጣህ፣ የጠራህ
ከጦርሜዳ ይልቅ ገበያ ሚያስፈራህ፡፡
ቤሳ ባታወርሰኝ አወረስከኝ ትግል
የትም እንዳይጥለኝ ፣ሕይወት እንደ ፈንግል፡፡
አባየ ብርሀን
አባ የምስራቅ በር
ገመና ሸሻጊ፣እንደ ካባ ገበር
አባቴ ባትሆን ይጸጽተኝ ነበር፡፡
🔘በእውቀቱ ስዩም🔘
የማትንበረከክ
የማትርመጠመጥ
ከባለጌ ዙፋን
በርጩማ የማትመርጥ፡፡
ያለ ባህር ሰርጓጅ ያለ ሙሴ በትር
በመታገስ ብቻ ፣ባህር የምትመትር፡፡
ካዘልከኝ ጀምሮ ፣እንኮኮ ጫንቃህ ላይ
ከፍታውን እንጅ፣ ዝቅታውን እንዳላይ
እንደ ንሥር መጠቅሁ፣ እንደ ምስራቅ በራሁ
የገዛ ክንፎቼን ፣እንደ ዳንቴል ሠራሁ፡፡
በርግጥ ደሀ ነበርህ…
ከሰላምታ በቀር የማታበረክት
ነጠላህ መናኛ፣ሰውነትህ የክት
በርግጥ ድሀ ነበርህ
የነጣህ፣ የጠራህ
ከጦርሜዳ ይልቅ ገበያ ሚያስፈራህ፡፡
ቤሳ ባታወርሰኝ አወረስከኝ ትግል
የትም እንዳይጥለኝ ፣ሕይወት እንደ ፈንግል፡፡
አባየ ብርሀን
አባ የምስራቅ በር
ገመና ሸሻጊ፣እንደ ካባ ገበር
አባቴ ባትሆን ይጸጽተኝ ነበር፡፡
🔘በእውቀቱ ስዩም🔘
❤34👍18