#ሊሆን_ይችላል !!
:
:
#በአሌክስ_አብርሃም
ለሚስቴ ያለኝ ፍቅር ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረ ነው የሚሄደው። ችግሩ ፍቅሩ የሚጨምረው
ብቻውን አልነበረም፤ እግር እጅ ከሌለው ቅናት ጋር እንጂ። በእኔ ልብ ውስጥ ፍቅርና ቅናት
እንደመንትያ ልጆች እኩል ነበር የሚያድጉት። እየቆየ ግን የፍቅር አቅም እየኮሰመነ፣ የቅናቴ ጡንቻ
እየፈረጠመ ሄደና ቅናቴ እንደ ምርቃት ቆብ ከነመነሳንሱ በፍቅሬ አናት ላይ በኩራት ጉብ አለ።
አያድርስ ነው! ርኩሳዊ ቅናት የሰይጣን አንዱ ሥራ ሳይሆን ሰይጣን ራሱ ሳይሆን አይቀርም። ሚስቴ መዓዛ ጨዋነቷን አገር ይመሰክርላታል። ግን ምን ዋጋ አለው። የእኔ የባሏ ሆድ ግልፅ ባልሆነ ምከንያት ሻክሯል።
“ምን ስታደርግ አይተሀት ቀናህ?” ብባል መልስ የለኝም። ግን እቀናለሁ። ስቀና እስሳጭባታለሁ።
አንዳንዴ እንደውም ከመሬት ተነስቼ ሁለት-ሦስት ቀን አኮርፋታለሁ፤ ግራ ይገባታል። የምትይዝ የምትጨብጠውን ታጣለች። አንዲት ጠባብ ክፍል ውስጥ እየኖርን ስዘጋት የምታደርገውን ነገር ታጣለች። ..ደስ ይለኛል፡፡ ጭንቀቷ ነፍሴን ያረካታል፡፡ አንዳች የመበቀል እርካታ ይሰማኛል። ከንፈሯ እየተንቀጠቀጠና ቀይ ጉንጯ በርበሬ መስሎ ግራ ተጋብታ ስመለከታት በኩራት ኩፍስ ብዬ በስቃይዋ
እዝናናለሁ!
ብዙ ጊዜ፣ በተለይ ወንዶች በፍቅረኝነት እያሉ ቅናት ያጠቃቸዋል። ያፈቀሯትን ሲያገቡ ግን በቁጥጥራቸው የዋለች መስሎ ስለሚሰማቸው አይቀኑም ሲባል ነበር የሰማሁት። የእኔ ቅናት ግን የተገላቢጦሽ ነው። በፍቅረኝነት እንደነበርንም ይሁን የተጋባን ሰምን አልቀናም ነበር። ለዛም ሳይሆን አይቀርም መዓዛን ብዙም ትኩረት ሰጥቼ የት ገባች፣ የት ወጣች የማልለው። የኋላ ኋላ ግን ቅናት ከነ የልጅ ልጁ ሰፈረብኝ።
የቅናት ትልቁ ችግር የሚቀናበት ሰው እንደሚያስቡት መሆን አለቀመሆኑ ላይ አይደለም። የሚቀናውን ሰው ራሱን በበታችነት ስሜት አጥለቅልቆ ያልሆነውን ማድረጉ እንጂ። መዓዛ ፊልም እየተመለከተች አንዱን የፊልም ተዋናይ ካደነቀች የጨጓራ ሕመሜ ይነሳል። በቃ ስለምቀና፣ አገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀውን ጎበዝ የፊልም ተዋናይ ማጣጣል እጀምራለሁ። መዓዛ ከተከራከረችኝማ በቃ ሰውነቴ ሁሉ
በብስጭት ይንገበገባል፤ እቀናለሁ !
“ምናባቱ ይሄ ሴታሴት ካሜራ ፊት ጀግና ይመስላል፣ ልክስክስ፣ እዚህ ካዛንችስ መጠጥ ቤት በመጠጥ ቤት፣ ጫት ቤት ለጫት ቤት ሲዞር አይደል የሚውለው!? እሱ ያልተኛቸው ሴተኛ አዳሪዎች የሉም።
“ኧረ አብርሽ በእግዚአብሔር፣ የተከበረ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነው…” ትላለች መአዚ።
“አንቺ ስለ እሱ ሕያወት ስታጣሪ ነው የምትውይው? ምን ታውቂያለሽ…”
“እኔማ ምን አውቃለሁ ራሱ ነው በቲቪ ከነሚስቱ ቀርቦ ኢንተርቪው ሲሰጥ ያየሁት።” ትላለች
ጩኸቴ አስደንግጧት።
“እና በቴሌቪዥን ቀርቦ ጠጣለሁ፣ እቅማለሁ፣ ሴት አይተርፈኝም ይበል…?” እልና ሙዓዚ ላይ
አፈጥባታለሁ። መዓዚ በግርምት እየተመለከተችኝ ዝም ትላለች። ፊልም በተከፈተ ቁጥር መዓዛ
የምታደንቀውን ሰው ስዘልፍና ሳጣጥል ፊልሙን በቅጡ ሳናየው ስለሚያልፍ መዓዘ. ቀስ በቀስ
ማድነቋን አቆመች። እኔ ግን መቅናቴን አላቆምኩም። አንዱ ወንድ ተዋናይ በተናገረው ነገር ከሳቀች ወይም በመደነቅ ራሷን ከነቀነቀች ቅናቴ ያስለፈልፈኛል፤ እነዚህ የጠላ ቤትና የጫት ቤት ቀልድ እያመጡ ይቀባጥራሉ፤…አይ የኢትዮጵያ ፊልም እንዲህ የዱርዬ መናኸሪያ ሆኖ ይቅር…! ምን የፊልም ኢንዱስትሪ ነው፣ የዱርዬ፣ የሥራ ፈት ኢንዱስትሪ ቢሉት ይሻላል።”
ይሄ ባህሪዬ ሲያስመርራት መዓዚ ከእኔ ጋር ፊልም ማየት አቆመች፡፡ በፊት ፊልምሲከፈት ተንደርድራ
መጥታ ጎኔ ትቀመጥና ራሷን ትከሻዬ ላይ ዘንበል አድርጋ ነበር የምትመለከተው። የሚያስቅ ነገር
ስትመለከት አንገቴ ሥር ገብታ ፍርፍር ብላ ትስቅ ነበር። ዕድሜ ለቅናቴ! ይሄው ፊልም ከእኔ ጋር
ማየት አቆመችና አረፈችው። ፊልም ሲከፈት ወይ ጓዳ ገብታ ትንጎዳጉዳለች፣ ወይ መኝታ ቤት ትገባና ትተኛለች፣ ወይም ታነባለች፡፡
“ፊልም አታይም እንዴ?” እላታለሁ።
"ይቼዋለሁ።”
“የት አየሽሁ?”
"ባለፈው እማዬጋ የሄድኩ ጊዜ።"
"እማዬ ቴሌቪዥናቸው ተበላሸ አላልሽም…?”
“ሌላ ገዛች።”
“ማን "ገዛላቸው?”
"ኧረ አብርሽ በእግዚአብሔር አታጨናንቃኝ” ትልና በምሬት ታየኛለች። በቃ እናቷ ቤት አይደለም ያየችው …. የሆነ ወንድ ጋር ትክሻው ላይ ራሷን ጣል አድርጋ (በየመሀሉም እየተሳሳሙም ሊሆን ይችላል)፣
በቃ እንደዛ ነው ያየችው፣ … ልክስክስ ውይ ሴቶች ! እብሰለሰላለሁ፡፡ ትከሻውን የተደገፈችው ወንድ ማን ይሆን…? ምናልባት አብረውም ተኝተው ሊሆን ይችላል፤ አብራ ፌልም ለማየት ያልተመለሰች
እሺ ለእናቷ ማን ቴሌቪዥን ገዛላቸው? ይሄው ታሪኩ ሲገጣጠም መዓዛ ሀብታም ወንድ ጋር ሄደች…፣ ቤቱ ሄደው ፊልም አብረው አዩ፣ (ሶፋ ላይ አብረው ተቀምጠው፣ ጫማዋን አውልቃ፣ የሚያማምሩ እግሮቿን ሶፋው ላይ ሰብስባ አስቀምጣ፣ ልክ እንደ ቤቷ ዘና ብላ….)፣ ከዛ አብረው መኝታ ቤት ገቡ …፣ ኧረ ሶፋውን ማን ይዞባቸው ከዛ ነፍሳቸው መለስ ሲል አወሩ፣
ፊልም ትወጂያለሽ የኔ ቆንጆ ሊላት ይችላል፣ ግን “የኔ ማር" ነው የሚላት፣
“በ.ጣ.ም!!” ትለዋለች ደረቱ ላይ ተለጥፉ! ይቺ መዥገር። ሁለቱም መዥገር ናቸው እንጂ እሷም እሱ
ላይ እሱም ትዳራ ላይ የተጣበቁ መዥገሮች!!
"እና በየቀኑ ትመለክቻለ?”
"በፊት ነበር፤ አሁን ባሌ እየተነዛዘነዘ በየት በኩል ሊያሳየኝ ብለህ።”
"ኦ..ባልሽ ግን ምናይነት ደደብ ቅል ራስ ነው ባክሽ። ሙቪ እያያችሁ ይነዛነዛል ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ አሜዚንግ !
በጣ…ም…! ምን ቅል ብቻ፡ ድንጋይ …! ባልጩት ራስ ነገር ነው እንጂ። ሲጋባ ሲዉጣ መነዛነዝ ነው።
እንዳልተሳካላት ተዋናይ ያየውን ተዋናይ ሁሉ ምዠመዝለፍ ነው ስራው” ትለዋለች::
እሷን ባፈቀርናት፣ ቤቴን ትዳሬን ባልኩ የማንም ዱርዬ ጋር ስታማኝ አያበሳጭም? (ውስጤ ይብከነክናል፤) ላብ ላብ ይለኛል! በላብ የጨቀየ መዳፌን በእልህ ጨብጬ ሶፋውን በቡጢ እነርተዋል መዓዛ በድንጋጤ ከራማዋ ተገፍፎ እያማተበች ትቀርበኝና ጭንቀት በወረረው ፊቷ ላይ እንባ በቋጠሩ ዓይኖቿ እየተመለከተቸኝ፣
“ምነው ፍቅር ምን ሆንክ? ከሰው ጋር ተጣላህ እንዴ? ላብ በላብ ሆንክ እኮ፧ አመመህ እንዴ የኔ
ፍቅር…?” ጉንጬ ላይ እጇን ልታሳርፍ ስትልክ እጇን ወደዛ አሽቀንጥሬ ተነስቼ ወደ መኝታ ቤቴ እገባና የቁም ቅዠቴን ተኝቼ እቀጥላለሁ፡ እሷም ግራ በመጋባት ወገቧን ይዛ መኝታ ቤት በር ላይ ቆማ ትቆያለች፣ “ምን እዳ ገባሁ!” እያለች።
እቀናለሁ…. እቀናለሁ ! እቀናለሁ ! አንዳንዴማ በህልሜ ሁሉ ስለምቃዥ መዓዛ ፀበል እንሂድ
ትለኛለች። ቢመቻት እብድ ነው ብላ አማኑኤል አሳሰራኝ ዓለሟን ከሌላ ወንድ ጋር ልትቀጭ
እንዳሰበች እጠረጥራለሁ… ተገኝቶ ነው ?አሁን ሌላ ወንድ ጋር ብትሄድ ሰው እያስቀምጣትም፣ እስኪ ምን አጥታ ጥጋብ ልክስክስነት እኝጂ ቱ ይሄን የመሰለ ሸበላ የጠገበ ደመውዝ የሚያበላ ባል ትታ …ወይ ጥጋብ ይላታል .. ካበድኩላት ግን እንዳሻት ትዘላለች ሰውም አይቃወማትም ምን ታድርግ
እብድ ጋር ትኑር እንዴ ታዲያ? ወጣት ናት! ቆንጆ ናት! ስንት ነገር ያምራታል! ምን አልባት…” ሊሉ
ይችላሉ። እኔ ደግሞ ለእልኳ አላብድ ሲያምራት ይቅር!!
:
:
#በአሌክስ_አብርሃም
ለሚስቴ ያለኝ ፍቅር ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረ ነው የሚሄደው። ችግሩ ፍቅሩ የሚጨምረው
ብቻውን አልነበረም፤ እግር እጅ ከሌለው ቅናት ጋር እንጂ። በእኔ ልብ ውስጥ ፍቅርና ቅናት
እንደመንትያ ልጆች እኩል ነበር የሚያድጉት። እየቆየ ግን የፍቅር አቅም እየኮሰመነ፣ የቅናቴ ጡንቻ
እየፈረጠመ ሄደና ቅናቴ እንደ ምርቃት ቆብ ከነመነሳንሱ በፍቅሬ አናት ላይ በኩራት ጉብ አለ።
አያድርስ ነው! ርኩሳዊ ቅናት የሰይጣን አንዱ ሥራ ሳይሆን ሰይጣን ራሱ ሳይሆን አይቀርም። ሚስቴ መዓዛ ጨዋነቷን አገር ይመሰክርላታል። ግን ምን ዋጋ አለው። የእኔ የባሏ ሆድ ግልፅ ባልሆነ ምከንያት ሻክሯል።
“ምን ስታደርግ አይተሀት ቀናህ?” ብባል መልስ የለኝም። ግን እቀናለሁ። ስቀና እስሳጭባታለሁ።
አንዳንዴ እንደውም ከመሬት ተነስቼ ሁለት-ሦስት ቀን አኮርፋታለሁ፤ ግራ ይገባታል። የምትይዝ የምትጨብጠውን ታጣለች። አንዲት ጠባብ ክፍል ውስጥ እየኖርን ስዘጋት የምታደርገውን ነገር ታጣለች። ..ደስ ይለኛል፡፡ ጭንቀቷ ነፍሴን ያረካታል፡፡ አንዳች የመበቀል እርካታ ይሰማኛል። ከንፈሯ እየተንቀጠቀጠና ቀይ ጉንጯ በርበሬ መስሎ ግራ ተጋብታ ስመለከታት በኩራት ኩፍስ ብዬ በስቃይዋ
እዝናናለሁ!
ብዙ ጊዜ፣ በተለይ ወንዶች በፍቅረኝነት እያሉ ቅናት ያጠቃቸዋል። ያፈቀሯትን ሲያገቡ ግን በቁጥጥራቸው የዋለች መስሎ ስለሚሰማቸው አይቀኑም ሲባል ነበር የሰማሁት። የእኔ ቅናት ግን የተገላቢጦሽ ነው። በፍቅረኝነት እንደነበርንም ይሁን የተጋባን ሰምን አልቀናም ነበር። ለዛም ሳይሆን አይቀርም መዓዛን ብዙም ትኩረት ሰጥቼ የት ገባች፣ የት ወጣች የማልለው። የኋላ ኋላ ግን ቅናት ከነ የልጅ ልጁ ሰፈረብኝ።
የቅናት ትልቁ ችግር የሚቀናበት ሰው እንደሚያስቡት መሆን አለቀመሆኑ ላይ አይደለም። የሚቀናውን ሰው ራሱን በበታችነት ስሜት አጥለቅልቆ ያልሆነውን ማድረጉ እንጂ። መዓዛ ፊልም እየተመለከተች አንዱን የፊልም ተዋናይ ካደነቀች የጨጓራ ሕመሜ ይነሳል። በቃ ስለምቀና፣ አገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀውን ጎበዝ የፊልም ተዋናይ ማጣጣል እጀምራለሁ። መዓዛ ከተከራከረችኝማ በቃ ሰውነቴ ሁሉ
በብስጭት ይንገበገባል፤ እቀናለሁ !
“ምናባቱ ይሄ ሴታሴት ካሜራ ፊት ጀግና ይመስላል፣ ልክስክስ፣ እዚህ ካዛንችስ መጠጥ ቤት በመጠጥ ቤት፣ ጫት ቤት ለጫት ቤት ሲዞር አይደል የሚውለው!? እሱ ያልተኛቸው ሴተኛ አዳሪዎች የሉም።
“ኧረ አብርሽ በእግዚአብሔር፣ የተከበረ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነው…” ትላለች መአዚ።
“አንቺ ስለ እሱ ሕያወት ስታጣሪ ነው የምትውይው? ምን ታውቂያለሽ…”
“እኔማ ምን አውቃለሁ ራሱ ነው በቲቪ ከነሚስቱ ቀርቦ ኢንተርቪው ሲሰጥ ያየሁት።” ትላለች
ጩኸቴ አስደንግጧት።
“እና በቴሌቪዥን ቀርቦ ጠጣለሁ፣ እቅማለሁ፣ ሴት አይተርፈኝም ይበል…?” እልና ሙዓዚ ላይ
አፈጥባታለሁ። መዓዚ በግርምት እየተመለከተችኝ ዝም ትላለች። ፊልም በተከፈተ ቁጥር መዓዛ
የምታደንቀውን ሰው ስዘልፍና ሳጣጥል ፊልሙን በቅጡ ሳናየው ስለሚያልፍ መዓዘ. ቀስ በቀስ
ማድነቋን አቆመች። እኔ ግን መቅናቴን አላቆምኩም። አንዱ ወንድ ተዋናይ በተናገረው ነገር ከሳቀች ወይም በመደነቅ ራሷን ከነቀነቀች ቅናቴ ያስለፈልፈኛል፤ እነዚህ የጠላ ቤትና የጫት ቤት ቀልድ እያመጡ ይቀባጥራሉ፤…አይ የኢትዮጵያ ፊልም እንዲህ የዱርዬ መናኸሪያ ሆኖ ይቅር…! ምን የፊልም ኢንዱስትሪ ነው፣ የዱርዬ፣ የሥራ ፈት ኢንዱስትሪ ቢሉት ይሻላል።”
ይሄ ባህሪዬ ሲያስመርራት መዓዚ ከእኔ ጋር ፊልም ማየት አቆመች፡፡ በፊት ፊልምሲከፈት ተንደርድራ
መጥታ ጎኔ ትቀመጥና ራሷን ትከሻዬ ላይ ዘንበል አድርጋ ነበር የምትመለከተው። የሚያስቅ ነገር
ስትመለከት አንገቴ ሥር ገብታ ፍርፍር ብላ ትስቅ ነበር። ዕድሜ ለቅናቴ! ይሄው ፊልም ከእኔ ጋር
ማየት አቆመችና አረፈችው። ፊልም ሲከፈት ወይ ጓዳ ገብታ ትንጎዳጉዳለች፣ ወይ መኝታ ቤት ትገባና ትተኛለች፣ ወይም ታነባለች፡፡
“ፊልም አታይም እንዴ?” እላታለሁ።
"ይቼዋለሁ።”
“የት አየሽሁ?”
"ባለፈው እማዬጋ የሄድኩ ጊዜ።"
"እማዬ ቴሌቪዥናቸው ተበላሸ አላልሽም…?”
“ሌላ ገዛች።”
“ማን "ገዛላቸው?”
"ኧረ አብርሽ በእግዚአብሔር አታጨናንቃኝ” ትልና በምሬት ታየኛለች። በቃ እናቷ ቤት አይደለም ያየችው …. የሆነ ወንድ ጋር ትክሻው ላይ ራሷን ጣል አድርጋ (በየመሀሉም እየተሳሳሙም ሊሆን ይችላል)፣
በቃ እንደዛ ነው ያየችው፣ … ልክስክስ ውይ ሴቶች ! እብሰለሰላለሁ፡፡ ትከሻውን የተደገፈችው ወንድ ማን ይሆን…? ምናልባት አብረውም ተኝተው ሊሆን ይችላል፤ አብራ ፌልም ለማየት ያልተመለሰች
እሺ ለእናቷ ማን ቴሌቪዥን ገዛላቸው? ይሄው ታሪኩ ሲገጣጠም መዓዛ ሀብታም ወንድ ጋር ሄደች…፣ ቤቱ ሄደው ፊልም አብረው አዩ፣ (ሶፋ ላይ አብረው ተቀምጠው፣ ጫማዋን አውልቃ፣ የሚያማምሩ እግሮቿን ሶፋው ላይ ሰብስባ አስቀምጣ፣ ልክ እንደ ቤቷ ዘና ብላ….)፣ ከዛ አብረው መኝታ ቤት ገቡ …፣ ኧረ ሶፋውን ማን ይዞባቸው ከዛ ነፍሳቸው መለስ ሲል አወሩ፣
ፊልም ትወጂያለሽ የኔ ቆንጆ ሊላት ይችላል፣ ግን “የኔ ማር" ነው የሚላት፣
“በ.ጣ.ም!!” ትለዋለች ደረቱ ላይ ተለጥፉ! ይቺ መዥገር። ሁለቱም መዥገር ናቸው እንጂ እሷም እሱ
ላይ እሱም ትዳራ ላይ የተጣበቁ መዥገሮች!!
"እና በየቀኑ ትመለክቻለ?”
"በፊት ነበር፤ አሁን ባሌ እየተነዛዘነዘ በየት በኩል ሊያሳየኝ ብለህ።”
"ኦ..ባልሽ ግን ምናይነት ደደብ ቅል ራስ ነው ባክሽ። ሙቪ እያያችሁ ይነዛነዛል ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ አሜዚንግ !
በጣ…ም…! ምን ቅል ብቻ፡ ድንጋይ …! ባልጩት ራስ ነገር ነው እንጂ። ሲጋባ ሲዉጣ መነዛነዝ ነው።
እንዳልተሳካላት ተዋናይ ያየውን ተዋናይ ሁሉ ምዠመዝለፍ ነው ስራው” ትለዋለች::
እሷን ባፈቀርናት፣ ቤቴን ትዳሬን ባልኩ የማንም ዱርዬ ጋር ስታማኝ አያበሳጭም? (ውስጤ ይብከነክናል፤) ላብ ላብ ይለኛል! በላብ የጨቀየ መዳፌን በእልህ ጨብጬ ሶፋውን በቡጢ እነርተዋል መዓዛ በድንጋጤ ከራማዋ ተገፍፎ እያማተበች ትቀርበኝና ጭንቀት በወረረው ፊቷ ላይ እንባ በቋጠሩ ዓይኖቿ እየተመለከተቸኝ፣
“ምነው ፍቅር ምን ሆንክ? ከሰው ጋር ተጣላህ እንዴ? ላብ በላብ ሆንክ እኮ፧ አመመህ እንዴ የኔ
ፍቅር…?” ጉንጬ ላይ እጇን ልታሳርፍ ስትልክ እጇን ወደዛ አሽቀንጥሬ ተነስቼ ወደ መኝታ ቤቴ እገባና የቁም ቅዠቴን ተኝቼ እቀጥላለሁ፡ እሷም ግራ በመጋባት ወገቧን ይዛ መኝታ ቤት በር ላይ ቆማ ትቆያለች፣ “ምን እዳ ገባሁ!” እያለች።
እቀናለሁ…. እቀናለሁ ! እቀናለሁ ! አንዳንዴማ በህልሜ ሁሉ ስለምቃዥ መዓዛ ፀበል እንሂድ
ትለኛለች። ቢመቻት እብድ ነው ብላ አማኑኤል አሳሰራኝ ዓለሟን ከሌላ ወንድ ጋር ልትቀጭ
እንዳሰበች እጠረጥራለሁ… ተገኝቶ ነው ?አሁን ሌላ ወንድ ጋር ብትሄድ ሰው እያስቀምጣትም፣ እስኪ ምን አጥታ ጥጋብ ልክስክስነት እኝጂ ቱ ይሄን የመሰለ ሸበላ የጠገበ ደመውዝ የሚያበላ ባል ትታ …ወይ ጥጋብ ይላታል .. ካበድኩላት ግን እንዳሻት ትዘላለች ሰውም አይቃወማትም ምን ታድርግ
እብድ ጋር ትኑር እንዴ ታዲያ? ወጣት ናት! ቆንጆ ናት! ስንት ነገር ያምራታል! ምን አልባት…” ሊሉ
ይችላሉ። እኔ ደግሞ ለእልኳ አላብድ ሲያምራት ይቅር!!
👍45
#ሊሆን_ይችላል
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም (መጨረሻው)
...ትቻት ወጣሁ። ለምን እንደሆነ እንጃ እንደማላከበራት ማሳየት እፈልጋለሁ።
በር ላይ አንድ የማልወደው ጎረቤቴ ደረቱን ገልብጦ በጠዋቱ በፓክ አውትና በቁምጣ ኮንዶሚኒየም ደረጃ ላይ እገኘሁት። እኔ ስወርድ እሱ ሲወጣ ነበር የተገናንነው፡፡ በእጁ የመዝለያ ገመድ ይዟል፤
ከስፖርት እየተመለሰ ነው።
“ሰላም አብርሽ!” አለኝ በፈገግታ።
"ሰላም ሰለሞን!” ብዬው ላልፍ ስል፣
“ምነው ይሄ አለባበስህ ትንሽ አልደመቀም…?” አለና ፈገግ አለ። ቀልዶ ምቷል ለዛ ቢስ ለካፌ ሁላ!!
እንዳልሰማሁ አለፍኩት። ጣሳ ራስ እሱ ስለኔ አለባበስ ምን አገባው!? ይሄ ቦዘኔ ጎረቤቴ ሥራው ምን እንደሆነ እንጃለት (ሥራ እንኳን ያለው አይመስለኝም) ሁልጊዜ የምንጋራው በረንዳ ላይ ወንበር
ያወጣና ዝሆኔ የያዘው የሚመስል (ፈርጣማ ይሉታል አንዳንዶች) ጠብደል ግንዲላ እግሩን ዘርግቶ
ጋዜጣ ያነባል። ኑሮው ዘና ያለ ነው።አንዳንዴ ውድ የሆነ ሙሉ ልብሱን ይለብስና ዲ ኤክስ መኪናውን አስነስቶ ይሄዳል … አፍታ ሳይቆይ ያመለሳል፡፡ ቤቱ ውስጥ የቀበረው ነገር ሳይኖር አይቀርም፤ ከቤቱ ርቆ አይሄድም፡፡ ይዞት ይሂድና! ቆይ ግን ቤት እየዋለ እንዲህ ተዝናንቶ የሚውልበትን ገንዘብ ከየት
አባቱ ነው የሚያመጣው። ሌባ ይሆን…? ወይንስ ቅጥር ነፍሰ ገዳይ …?
ድንገት አንድ ሐሳብ እእምሮዬ ውስጥ ፈነዳና ቀጥ ብዬ ቆምኩ፤ ፋጭጭጭጭጭጭጭ እንደ
መኪና አቋቋሜ ድንገተኛ ስለነበር ከኋላዬ የነበረች ልጅ ልትጋጨኝ ለትንሽ ተረፈች። ቆይ ይሄ ጎረቤቴ
ቤት ሲወል ምን እያደረገ ይውላል? መደዳውን አራት ቤቶች አሉ። ጥግ ላይ የኔ ቤት። መዓዛ ሥራ ስለሌላት ቤት ነው የምትውለው። ቀጥሎ ሁልግዜ ዝግ የሆነው እንደኔ ከርታታው ጎረቤቴ (ፊልድ ነው ሥራው)፤ ቤቱ ሁልግዜ ዝግ ነው፤ የሸረሪት ድር ሁሉ በሩ ላይ ያደራል። ቀጥሎ ይሄ ቦዘኔ አለ። ቦዘኔው
መልኩ ጥቁር ነው፡፡ ልክ እንደ ፊልም የሚስቴ ንግግር በምልሰት ታየኝ፤ “ጥቁር እንኳን ብትሆን…”
ነው ያለችው አይደል?…ቢንጎ !!!
ቦዘኔው ቤት ነው የሚውለው። ምን ቤት እኔ ቤት ልበል እንጂ ! መቼስ በአንድ ዝግ ቤት ዳርና
ዳር ቦዘኔውና ሚስቴ ብቻቸውን ሲውሉ አይነጋገሩም ማለት ዘበት ነው። እንዴ አብረውም ፊልም
ሊመለከቱ ይችላሉ እንጂ። በእኔው ቴሌቪዥን፣ በእኔው ዲቪዲ፣ እኔው ሶፋ ላይ !...
ሊሆን ይችላል !!
ተመልሼ ወደ ቤቴ ሮጥኩ!
ጉድና ጅራት አሉ ! ወይ ድፍረት……!
በቤቴ … በራሴ ቤት … በራሴ አልጋ … በራሴ ብርድ ልብስ … በራሴ እንሶላ … በራሴ ፍራሽ … በራሴ ሚስት በራሴ … ! ባፍጢሜ እስከምደፋ ታጣደፍኩ። ምን ዋጋ አለው እስካሁን ነገር የተበላሸውን !አልጋውን እንደሆነ እኔ ሚስኪኑ እኔ ራሴ እንደ መኪና አሙቄ ትቼለት ወጥቻለሁ። መዓዛንም ቢሆን ሌሊቱን ልታቅፈኝ ስትሞክር በኩርፊያ እጇን እየገፋሁ ጀርባዬን ሰፕቻት በአምሮት አቃጥያት ነው
ትቻት የወጣሁት። በስስ ፒጃማ የሞቀ አልጋ ውስጥ እሳት ሆና ትጠብቀዋለች። በቃ ምን ቸገረው
ቁምጣውን ወለቅ አድርጎ በጠዋቱ ገነት መግባት ነው !!! ጉድ ጉድ ጉድ አሟሙቄ ለሰው። ወይ ነዶ
!! ሮጥኩ! ኮቴ እንደ ክንፍ እየተውለበለበ ወደ ቤቴ … ምን ቤት አለኝ ቤቴ ፈራርሶ ! ሱናሚ አውሎ ነፉስ ከሥር መሠረቱ ቤቴን ነቅሎ የሚጥል ጎርፍ ከጎረቤት አገር !
መንገዱ ረዘመብኝ። የመዓዛ ደረት የተላለጠ ሸንኩርት መስሎ ታየኝ። ጡቶቿ ስስ ፒጃማዋን ወጥረው
ጫፋቸው ባቄላ ባቄላ መስሎ… ቀይ ከንፈሯ እየተንቀጠቀጠ ከሥር ተንጋልላ.. የሚያማምሩ እግሮቿ በጠረንገሎው ዙሪያ ተጠምጥመው ታየችኝ። እግሮቿማ ለምን አያምሩ፧ እሾህ አይወጋቸው ጋሬጣ ሎሚ መስለው እንደተቀመጡ ሳይወጡ ሳይወርዱ ቤታቸው። መኝታ ቤታቸው ድረስ ካንድ አይሉ ሁለት ባል ሲመጣላቸው …፤ ያ የገደል ስባሪ የሚያህል ቦዘኔ ጎረቤቴ ከነለቡ፣ ከነጠረኑ አልጋ
ላይ ታየኝ። ምናለ ሻወር እንኳን ቢወሰድ የሰው እልጋ መድፈሩ ካልቀረ ለወጉ ለሥርዓቱ ሰውነቱን
ለቅለቅ ብሎ ቢዳፈር ምናለ! ስራ ውዬ ደክሞኝ ነው የምገባው ለኔስ አያዝኑም? አንሶላ መጋፈፉን
ቢቀማኝ አንሳላ ለብሼ ኩርምት የምልባትን አልጋ ምናለ ቢተውልኝ? ወይ ጭካኔ ! ታየኝ ላቡ እንደማስቲሽ መዓዛ ውብ ሰውነት ላይ ታመርጎ አልለቅም ሲል። ማን ያውቃል የራሴ ሚስት በስሜት እየተስረቀረቀች የኔ ጌታ! ጠረንህ የናርዶስ ሽቶ ነው› እያለችው ይሆናል፤ ፍቅር እንኳን አፍንጫን እእምሮን ይዘጋ የለ!
ሲሆይችላል!!
ደግሞ እንደ አባወራ ቤት አለኝ ብዬ ሶፋ ላይ ተጎልቼ የማላውቀው አገር እሳተ ገሞራ ሲፈነዳ በሐዘን
ከንፈሬን እየመጠጥኩ ቢቢሲ አያለሁ…. የዋህ ኣባወራ እሳቱን ጎረቤት አስቀምጦ እሳተ ጎሞራ በዜና ያያል። እኔን ራሴን ዜና አደረጉኝ፤ ዕድሜ ለሚስቴ፣ እኔን ራሴን ዜና ! ያውም ሰበር ዜና …! ሞራሌንም ቅስሜንም የሚሰባብር የሚያነካካት ሰበር ዜና ! ሞኝ ጋዜጠኛ አለ እዚህ አገር …ቢኖርማ ካሜሬአቸውን ይዘው ከኋላዬ ተከትለውኝ በሮጡ ነበር ! ዝም ብለው ስለግድብ ያውሩ … እዚህ ስንት ሚሊዮን ሜጋ ዋት እሳት ከመኝታ ቤቴ ሲመነጭ መቼ በቁም ነገር ተመለከቱት…!!
ቤት ስደርስ ሰሩ ብርግድ ብሏል…!
እግዚኣ ድፍረት ! ያምናለ በሩን እንኳን መለስ ገርበብ ቢያደርጉት ሰው ባይፈሩ ነፉስ እንኳን አይፈሩም ወይስ የመኝታ ቤቱን በር ቆልፈው ሊሆን ይችላል !!
በተከፈተው በር ተወርውሬ ስገባ መዓዛ “አብርሽዬ ድረስ…" ብላ በእጇ የያዘችውን የዱቄት ሳሙና
በቁሟ ለቀቀችው፤ (ሳትለኝም ደርሼ ነበር እኔማ). ... ዱቄት መስሎ ሳሎኑ ምንጣፍ ላይ ተዘራ። ራቅ ብሎ ሊታጠብ የተዘጋጀ የእኔ የቆሸሸ ልብስ ተከምሯል! በዚህ ሌሊት ልብሴን ልታጥብ እየተዘጋጀች ነበር፤ መዓዛ ! የሐፍረቴን ወደ መኝታ ቤት ገብቼ ኮሜዲኖውን ከፈትኩና የረሳሁትን እቃ የወሰድኩ
መስዬ ተመልሼ ወደ ሥራዬ ሮጥኩ። ትንሽ ሐፍረት ቢሰማኝም አእምሮዬ ውስጥ ግን አንድ ሐሳብ
መጣብኝ ..
መዓዛ ልብስ አጥባ ካሰጣጥቻ በኋላ እስከሚደርቅ ምን ትሠራላች በተሰጣት ልብስ ውስጥ
ጠረንገሎ፤ ጎረቤቴ እየተሽሎከለከ ወደ ቤቴ ሲገባ … በሩ ሲዘጋ … ታየኝ !
ሊሆን ይችላል!
ከሰዓት ከምሠራበት አየር መንገድ ቢሮዬ ሆኜ ለመዓዛ ስልክ ደወልኩላት። አንዴ ጠራ …. 2 3 4
5. የደወሉላቸው ደንበኛ ስልክ አይመልስም? እባክዎ …”
ወይ እባክዎ … ምኑን ተከበርኩት … ምኑን ለአንቱታ በቃሁት… ኮት መልበስ ብቻውን አንቱ አያስብል
ቢሮ ያማረ ወንበር ላይ መጎለት አንቱ እያስብል … ጓዳዬ እየፈረሰ ቤቴ እየተገረሰሰ .… ሦስት ጉልቻ
ያልኩት ትዳሬ ስድስት ጉልቻ እየሆነ ወይ አንቱታ : ሰልኩ ያለው ሳሎን፤ ሚስቴ እሰካሁን መኝታ
ቤት ... ወይም የጠረንገሎው ጎረቤቴ ቤት ትሆናለች … ማን ያንሳው ስልኩን … ዘመድ እንደሌለው ሐዘንተኛ ብቻውን ያልቅስ አንጂ…፤ ብቻውን ስልኩ…!
ስብሰለሰል ስልኬ ጠራ …. መዓዛ ነበረች።
"የት ሄደሽ ነው ስልኩ ይሄን ያህል ሲጠራ…"
"ልብስ ሳጥብ ውዬ አሁን ገና ጨረስኩና ሻወር ገብቼ እኮ ነው…! ከነሳሙናዬ ራቁቴን ነው አሁን የቆምኩት ፍቅር ብታየኝ ሳስቅ…
"ማን አለ?”
“ማን አለ? የት አለች በግርምትና ግራ መጋባት። ያመለጠኝን ጥያቄ አልደገምኩትም፡ መዓዛም ከዛ
በኋላ አላነሳችውም።
ቅናቴ ሲጨምር ልፍስፍስና በራሴ የማልተማመን ሰው ሆንኩ። በፊት በቀላሉ የምሠራውን ነገር ሁሉ
መስራት አልቻልኩም። ቅናት አቅም ያሳጣል። አንድ የማይረባ ነገር ላይ ብቻ በማተኮር በዙሪያችን ያሉ መልካም ነገሮችን ሁሉ ይጋርድብናል።
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም (መጨረሻው)
...ትቻት ወጣሁ። ለምን እንደሆነ እንጃ እንደማላከበራት ማሳየት እፈልጋለሁ።
በር ላይ አንድ የማልወደው ጎረቤቴ ደረቱን ገልብጦ በጠዋቱ በፓክ አውትና በቁምጣ ኮንዶሚኒየም ደረጃ ላይ እገኘሁት። እኔ ስወርድ እሱ ሲወጣ ነበር የተገናንነው፡፡ በእጁ የመዝለያ ገመድ ይዟል፤
ከስፖርት እየተመለሰ ነው።
“ሰላም አብርሽ!” አለኝ በፈገግታ።
"ሰላም ሰለሞን!” ብዬው ላልፍ ስል፣
“ምነው ይሄ አለባበስህ ትንሽ አልደመቀም…?” አለና ፈገግ አለ። ቀልዶ ምቷል ለዛ ቢስ ለካፌ ሁላ!!
እንዳልሰማሁ አለፍኩት። ጣሳ ራስ እሱ ስለኔ አለባበስ ምን አገባው!? ይሄ ቦዘኔ ጎረቤቴ ሥራው ምን እንደሆነ እንጃለት (ሥራ እንኳን ያለው አይመስለኝም) ሁልጊዜ የምንጋራው በረንዳ ላይ ወንበር
ያወጣና ዝሆኔ የያዘው የሚመስል (ፈርጣማ ይሉታል አንዳንዶች) ጠብደል ግንዲላ እግሩን ዘርግቶ
ጋዜጣ ያነባል። ኑሮው ዘና ያለ ነው።አንዳንዴ ውድ የሆነ ሙሉ ልብሱን ይለብስና ዲ ኤክስ መኪናውን አስነስቶ ይሄዳል … አፍታ ሳይቆይ ያመለሳል፡፡ ቤቱ ውስጥ የቀበረው ነገር ሳይኖር አይቀርም፤ ከቤቱ ርቆ አይሄድም፡፡ ይዞት ይሂድና! ቆይ ግን ቤት እየዋለ እንዲህ ተዝናንቶ የሚውልበትን ገንዘብ ከየት
አባቱ ነው የሚያመጣው። ሌባ ይሆን…? ወይንስ ቅጥር ነፍሰ ገዳይ …?
ድንገት አንድ ሐሳብ እእምሮዬ ውስጥ ፈነዳና ቀጥ ብዬ ቆምኩ፤ ፋጭጭጭጭጭጭጭ እንደ
መኪና አቋቋሜ ድንገተኛ ስለነበር ከኋላዬ የነበረች ልጅ ልትጋጨኝ ለትንሽ ተረፈች። ቆይ ይሄ ጎረቤቴ
ቤት ሲወል ምን እያደረገ ይውላል? መደዳውን አራት ቤቶች አሉ። ጥግ ላይ የኔ ቤት። መዓዛ ሥራ ስለሌላት ቤት ነው የምትውለው። ቀጥሎ ሁልግዜ ዝግ የሆነው እንደኔ ከርታታው ጎረቤቴ (ፊልድ ነው ሥራው)፤ ቤቱ ሁልግዜ ዝግ ነው፤ የሸረሪት ድር ሁሉ በሩ ላይ ያደራል። ቀጥሎ ይሄ ቦዘኔ አለ። ቦዘኔው
መልኩ ጥቁር ነው፡፡ ልክ እንደ ፊልም የሚስቴ ንግግር በምልሰት ታየኝ፤ “ጥቁር እንኳን ብትሆን…”
ነው ያለችው አይደል?…ቢንጎ !!!
ቦዘኔው ቤት ነው የሚውለው። ምን ቤት እኔ ቤት ልበል እንጂ ! መቼስ በአንድ ዝግ ቤት ዳርና
ዳር ቦዘኔውና ሚስቴ ብቻቸውን ሲውሉ አይነጋገሩም ማለት ዘበት ነው። እንዴ አብረውም ፊልም
ሊመለከቱ ይችላሉ እንጂ። በእኔው ቴሌቪዥን፣ በእኔው ዲቪዲ፣ እኔው ሶፋ ላይ !...
ሊሆን ይችላል !!
ተመልሼ ወደ ቤቴ ሮጥኩ!
ጉድና ጅራት አሉ ! ወይ ድፍረት……!
በቤቴ … በራሴ ቤት … በራሴ አልጋ … በራሴ ብርድ ልብስ … በራሴ እንሶላ … በራሴ ፍራሽ … በራሴ ሚስት በራሴ … ! ባፍጢሜ እስከምደፋ ታጣደፍኩ። ምን ዋጋ አለው እስካሁን ነገር የተበላሸውን !አልጋውን እንደሆነ እኔ ሚስኪኑ እኔ ራሴ እንደ መኪና አሙቄ ትቼለት ወጥቻለሁ። መዓዛንም ቢሆን ሌሊቱን ልታቅፈኝ ስትሞክር በኩርፊያ እጇን እየገፋሁ ጀርባዬን ሰፕቻት በአምሮት አቃጥያት ነው
ትቻት የወጣሁት። በስስ ፒጃማ የሞቀ አልጋ ውስጥ እሳት ሆና ትጠብቀዋለች። በቃ ምን ቸገረው
ቁምጣውን ወለቅ አድርጎ በጠዋቱ ገነት መግባት ነው !!! ጉድ ጉድ ጉድ አሟሙቄ ለሰው። ወይ ነዶ
!! ሮጥኩ! ኮቴ እንደ ክንፍ እየተውለበለበ ወደ ቤቴ … ምን ቤት አለኝ ቤቴ ፈራርሶ ! ሱናሚ አውሎ ነፉስ ከሥር መሠረቱ ቤቴን ነቅሎ የሚጥል ጎርፍ ከጎረቤት አገር !
መንገዱ ረዘመብኝ። የመዓዛ ደረት የተላለጠ ሸንኩርት መስሎ ታየኝ። ጡቶቿ ስስ ፒጃማዋን ወጥረው
ጫፋቸው ባቄላ ባቄላ መስሎ… ቀይ ከንፈሯ እየተንቀጠቀጠ ከሥር ተንጋልላ.. የሚያማምሩ እግሮቿ በጠረንገሎው ዙሪያ ተጠምጥመው ታየችኝ። እግሮቿማ ለምን አያምሩ፧ እሾህ አይወጋቸው ጋሬጣ ሎሚ መስለው እንደተቀመጡ ሳይወጡ ሳይወርዱ ቤታቸው። መኝታ ቤታቸው ድረስ ካንድ አይሉ ሁለት ባል ሲመጣላቸው …፤ ያ የገደል ስባሪ የሚያህል ቦዘኔ ጎረቤቴ ከነለቡ፣ ከነጠረኑ አልጋ
ላይ ታየኝ። ምናለ ሻወር እንኳን ቢወሰድ የሰው እልጋ መድፈሩ ካልቀረ ለወጉ ለሥርዓቱ ሰውነቱን
ለቅለቅ ብሎ ቢዳፈር ምናለ! ስራ ውዬ ደክሞኝ ነው የምገባው ለኔስ አያዝኑም? አንሶላ መጋፈፉን
ቢቀማኝ አንሳላ ለብሼ ኩርምት የምልባትን አልጋ ምናለ ቢተውልኝ? ወይ ጭካኔ ! ታየኝ ላቡ እንደማስቲሽ መዓዛ ውብ ሰውነት ላይ ታመርጎ አልለቅም ሲል። ማን ያውቃል የራሴ ሚስት በስሜት እየተስረቀረቀች የኔ ጌታ! ጠረንህ የናርዶስ ሽቶ ነው› እያለችው ይሆናል፤ ፍቅር እንኳን አፍንጫን እእምሮን ይዘጋ የለ!
ሲሆይችላል!!
ደግሞ እንደ አባወራ ቤት አለኝ ብዬ ሶፋ ላይ ተጎልቼ የማላውቀው አገር እሳተ ገሞራ ሲፈነዳ በሐዘን
ከንፈሬን እየመጠጥኩ ቢቢሲ አያለሁ…. የዋህ ኣባወራ እሳቱን ጎረቤት አስቀምጦ እሳተ ጎሞራ በዜና ያያል። እኔን ራሴን ዜና አደረጉኝ፤ ዕድሜ ለሚስቴ፣ እኔን ራሴን ዜና ! ያውም ሰበር ዜና …! ሞራሌንም ቅስሜንም የሚሰባብር የሚያነካካት ሰበር ዜና ! ሞኝ ጋዜጠኛ አለ እዚህ አገር …ቢኖርማ ካሜሬአቸውን ይዘው ከኋላዬ ተከትለውኝ በሮጡ ነበር ! ዝም ብለው ስለግድብ ያውሩ … እዚህ ስንት ሚሊዮን ሜጋ ዋት እሳት ከመኝታ ቤቴ ሲመነጭ መቼ በቁም ነገር ተመለከቱት…!!
ቤት ስደርስ ሰሩ ብርግድ ብሏል…!
እግዚኣ ድፍረት ! ያምናለ በሩን እንኳን መለስ ገርበብ ቢያደርጉት ሰው ባይፈሩ ነፉስ እንኳን አይፈሩም ወይስ የመኝታ ቤቱን በር ቆልፈው ሊሆን ይችላል !!
በተከፈተው በር ተወርውሬ ስገባ መዓዛ “አብርሽዬ ድረስ…" ብላ በእጇ የያዘችውን የዱቄት ሳሙና
በቁሟ ለቀቀችው፤ (ሳትለኝም ደርሼ ነበር እኔማ). ... ዱቄት መስሎ ሳሎኑ ምንጣፍ ላይ ተዘራ። ራቅ ብሎ ሊታጠብ የተዘጋጀ የእኔ የቆሸሸ ልብስ ተከምሯል! በዚህ ሌሊት ልብሴን ልታጥብ እየተዘጋጀች ነበር፤ መዓዛ ! የሐፍረቴን ወደ መኝታ ቤት ገብቼ ኮሜዲኖውን ከፈትኩና የረሳሁትን እቃ የወሰድኩ
መስዬ ተመልሼ ወደ ሥራዬ ሮጥኩ። ትንሽ ሐፍረት ቢሰማኝም አእምሮዬ ውስጥ ግን አንድ ሐሳብ
መጣብኝ ..
መዓዛ ልብስ አጥባ ካሰጣጥቻ በኋላ እስከሚደርቅ ምን ትሠራላች በተሰጣት ልብስ ውስጥ
ጠረንገሎ፤ ጎረቤቴ እየተሽሎከለከ ወደ ቤቴ ሲገባ … በሩ ሲዘጋ … ታየኝ !
ሊሆን ይችላል!
ከሰዓት ከምሠራበት አየር መንገድ ቢሮዬ ሆኜ ለመዓዛ ስልክ ደወልኩላት። አንዴ ጠራ …. 2 3 4
5. የደወሉላቸው ደንበኛ ስልክ አይመልስም? እባክዎ …”
ወይ እባክዎ … ምኑን ተከበርኩት … ምኑን ለአንቱታ በቃሁት… ኮት መልበስ ብቻውን አንቱ አያስብል
ቢሮ ያማረ ወንበር ላይ መጎለት አንቱ እያስብል … ጓዳዬ እየፈረሰ ቤቴ እየተገረሰሰ .… ሦስት ጉልቻ
ያልኩት ትዳሬ ስድስት ጉልቻ እየሆነ ወይ አንቱታ : ሰልኩ ያለው ሳሎን፤ ሚስቴ እሰካሁን መኝታ
ቤት ... ወይም የጠረንገሎው ጎረቤቴ ቤት ትሆናለች … ማን ያንሳው ስልኩን … ዘመድ እንደሌለው ሐዘንተኛ ብቻውን ያልቅስ አንጂ…፤ ብቻውን ስልኩ…!
ስብሰለሰል ስልኬ ጠራ …. መዓዛ ነበረች።
"የት ሄደሽ ነው ስልኩ ይሄን ያህል ሲጠራ…"
"ልብስ ሳጥብ ውዬ አሁን ገና ጨረስኩና ሻወር ገብቼ እኮ ነው…! ከነሳሙናዬ ራቁቴን ነው አሁን የቆምኩት ፍቅር ብታየኝ ሳስቅ…
"ማን አለ?”
“ማን አለ? የት አለች በግርምትና ግራ መጋባት። ያመለጠኝን ጥያቄ አልደገምኩትም፡ መዓዛም ከዛ
በኋላ አላነሳችውም።
ቅናቴ ሲጨምር ልፍስፍስና በራሴ የማልተማመን ሰው ሆንኩ። በፊት በቀላሉ የምሠራውን ነገር ሁሉ
መስራት አልቻልኩም። ቅናት አቅም ያሳጣል። አንድ የማይረባ ነገር ላይ ብቻ በማተኮር በዙሪያችን ያሉ መልካም ነገሮችን ሁሉ ይጋርድብናል።
👍27