#ለልደቴ፣
እጣ ፈንታ
ባልመረጥሁት ዘመን፣ ባልመረጥኩት ቦታ
ጎዳና ላይ አውጥቶኝ
እንቅፋት በየርምጃው፣ ተለክቶ ተሰጥቶኝ
ሲሻኝ እየሸሸሁ፣ ሲሻኝ እየተዋጋሁ
እንቅፋቴን በባዶ እግሬ፣ እንደ እንቧይ እየለጋሁ
ሕመምን እየሸወድኩ፣ ሞትን እያዘናጋሁ።
መኖር ሳልጠላ
ግና ለመኖር ብየ፤ የግብር እንጀራን ሳልበላ
አሜን የሚል ቃል ሳይወጣኝ
በጌቶች ፊት በፍርሃት፣ ጎንበስ ጎንበስ ሳያቃጣኝ
ነፃነቴን ከጥልቁ ሥር፣ እንደ ብርቅ አሳ አስግሬ
ያሻኝን ተናግሬ
ተጨብጭቦልኝ
አንዳንዴም ተወግሬ
ያለ አጀብ ያለጋሻ ጃግሬ
ባሻኝ እየገሰገስኩ
እንደ ወፍ በነፃነት፣ አገር ምድሩን እያዳረስኩ
በመረጥሁት ዛፍ ስር ተኝቼ
በጅሎች ካብ ስር ሸንቼ
እያወጋሁ፣ እየገጠምኩ፣ እያለመጥሁ፣ እያላገጥሁ
እንባዎቼን በቃል ምትሐት፣ ወደ ሣቅ እየለወጥሁ።
እየጣልኩ እየወደቅሁ እየማቀኩ እየደላኝ
እንሆ አርባ ዓመት ሞላኝ።
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
እጣ ፈንታ
ባልመረጥሁት ዘመን፣ ባልመረጥኩት ቦታ
ጎዳና ላይ አውጥቶኝ
እንቅፋት በየርምጃው፣ ተለክቶ ተሰጥቶኝ
ሲሻኝ እየሸሸሁ፣ ሲሻኝ እየተዋጋሁ
እንቅፋቴን በባዶ እግሬ፣ እንደ እንቧይ እየለጋሁ
ሕመምን እየሸወድኩ፣ ሞትን እያዘናጋሁ።
መኖር ሳልጠላ
ግና ለመኖር ብየ፤ የግብር እንጀራን ሳልበላ
አሜን የሚል ቃል ሳይወጣኝ
በጌቶች ፊት በፍርሃት፣ ጎንበስ ጎንበስ ሳያቃጣኝ
ነፃነቴን ከጥልቁ ሥር፣ እንደ ብርቅ አሳ አስግሬ
ያሻኝን ተናግሬ
ተጨብጭቦልኝ
አንዳንዴም ተወግሬ
ያለ አጀብ ያለጋሻ ጃግሬ
ባሻኝ እየገሰገስኩ
እንደ ወፍ በነፃነት፣ አገር ምድሩን እያዳረስኩ
በመረጥሁት ዛፍ ስር ተኝቼ
በጅሎች ካብ ስር ሸንቼ
እያወጋሁ፣ እየገጠምኩ፣ እያለመጥሁ፣ እያላገጥሁ
እንባዎቼን በቃል ምትሐት፣ ወደ ሣቅ እየለወጥሁ።
እየጣልኩ እየወደቅሁ እየማቀኩ እየደላኝ
እንሆ አርባ ዓመት ሞላኝ።
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
#ለልደቴ
እጣ ፈንታ
ባልመረጥሁት ዘመን፣ ባልመረጥኩት ቦታ
ጎዳና ላይ አውጥቶኝ
እንቅፋት በየርምጃው፣ ተለክቶ ተሰጥቶኝ
ሲሻኝ እየሸሸሁ፣ ሲሻኝ እየተዋጋሁ
እንቅፋቴን በባዶ እግሬ፣ እንደ እንቧይ እየለጋሁ
ሕምምን እየሸወድኩ፣ ሞትን እያዘናጋሁ።
መኖር ሳልጠላ
ግና ለመኖር ብዬ፤ የግብር እንጀራን ሳልበላ
አሜን የሚል ቃል ሳይወጣኝ
በጌቶች ፊት በፍርሃት፣ ጎንበስ ጎንበስ ሳያቃጣኝ
ነፃነቴን ከጥልቁ ሥር፣ እንደ ብርቅ አሳ አስግሬ
ያሻኝን ተናግሬ
ተጨብጭቦልኝ
አንዳንዴም ተወግሬ
ያለ አጀብ ያለጋሻ ጃግሬ
ባሻኝ እየገሰገስኩ
እንደ ወፍ በነፃነት፣ አገር ምድሩን እያዳረስኩ
በመረጥሁት ዛፍ ስር ተኝቼ
በጅሎች ካብ ስር ሸንቼ
እያወጋሁ፣ እየገጠምኩ፣ እያለመጥሁ፣ እያላገጥሁ
እንባዎቼን በቃል ምትሐት፣ ወደ ሣቅ እየለወጥሁ፡
እየጣልኩ እየወደቅሁ፤ እየማቀቅሁ እየደላኝ
እንሆ አርባ አመት ሞላኝ!
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
እጣ ፈንታ
ባልመረጥሁት ዘመን፣ ባልመረጥኩት ቦታ
ጎዳና ላይ አውጥቶኝ
እንቅፋት በየርምጃው፣ ተለክቶ ተሰጥቶኝ
ሲሻኝ እየሸሸሁ፣ ሲሻኝ እየተዋጋሁ
እንቅፋቴን በባዶ እግሬ፣ እንደ እንቧይ እየለጋሁ
ሕምምን እየሸወድኩ፣ ሞትን እያዘናጋሁ።
መኖር ሳልጠላ
ግና ለመኖር ብዬ፤ የግብር እንጀራን ሳልበላ
አሜን የሚል ቃል ሳይወጣኝ
በጌቶች ፊት በፍርሃት፣ ጎንበስ ጎንበስ ሳያቃጣኝ
ነፃነቴን ከጥልቁ ሥር፣ እንደ ብርቅ አሳ አስግሬ
ያሻኝን ተናግሬ
ተጨብጭቦልኝ
አንዳንዴም ተወግሬ
ያለ አጀብ ያለጋሻ ጃግሬ
ባሻኝ እየገሰገስኩ
እንደ ወፍ በነፃነት፣ አገር ምድሩን እያዳረስኩ
በመረጥሁት ዛፍ ስር ተኝቼ
በጅሎች ካብ ስር ሸንቼ
እያወጋሁ፣ እየገጠምኩ፣ እያለመጥሁ፣ እያላገጥሁ
እንባዎቼን በቃል ምትሐት፣ ወደ ሣቅ እየለወጥሁ፡
እየጣልኩ እየወደቅሁ፤ እየማቀቅሁ እየደላኝ
እንሆ አርባ አመት ሞላኝ!
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘