#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ስድስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#የጌታዬ_ሥራ
፡
ሰዎች በመንገድ ላይ ለመዘዋወር እንኳን በሚፈሩበት ከተማ ሥራ የት እንደማገኝ የሚያውቀው አምላክ ነው፡፡ ውድቅዳቂ ፈንጂዎች የኪጋሊን መንገዶች ሞልተዋቸዋል፤ ለመሥራት ከፈለግሁ ግን በነዚህ ጎዳናዎች ሥራን እያነፈነፍኩ መኳተን ይኖርብኛል፡፡ የሕዝብ ማጓጓዣ ተሸከርካሪዎች መንቀሳቀሳቸውን ትተዋል፤ ለአነስተኞቹም ማጓጓዣዎች የምከፍለው ምንም ገንዘብ አልነበረኝም፡፡
ፋሪን በቤቱ አቅራቢያ ያሉ ክፍት የሥራ ቦታ ያላቸውን ድርጅቶችን ያውቅ እንደሆነ ጠየቅሁት፡፡ ‹‹አሁን ማንም እየቀጠረ ስላልሆነ አማራጮችሽ በጣም ውሱን ናቸው›› ሲል መለሰልኝ፡፡ ‹‹ያለው ብቸኛ አማራጭ የተመድ ነው … እዚያ ለመግባት ግን እንግሊዝኛ መናገር ያስፈልጋል፡፡››
በአእምሮዬ የሆነ ነገር ብልጭ አለልኝ፡፡ በእርግጥ! እግዚአብሔር በመታጠቢያ ክፍሉ እንግሊዝኛ እንዳጠና ያደረገኝ ዋነኛው ምክንያት እኮ የተመድ ነው፡፡ በተመድ የመሥራት ሕልምም ነበረኝ፡፡
በዚያን ምሽት ልብሶቼን በሚገባ አጥቤ አምላክ በተመድ ሥራ እንዳገኝ ያግዘኝ ዘንድ ጸለይኩ፡፡ በመጨረሻ እንግሊዝኛዬን በሥራ ላይ የማውልበት መሆኑን አስቤ በጣም ተደስቼ አብዛኛውን የሌሊቱን ጊዜ መስታወት ሳይና ራሴን በራሴ ያስተማርኳቸውን ሐረጋት ስለማመድ ቆየሁ፡፡
‹‹እንደምን አደራችሁ››
‹‹እንዴት ነዎት?››
‹‹ሥራ ፈልጌ ነው፡፡›› ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡››
‹‹ሩዋንዳዊት ነኝ፡፡››
‹‹ቡታሬ ባለው ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ አጥንቻለሁ፡፡››
‹‹ሥራ ፈልጌ ነው፡፡››
አቤት! እንዴት ደስ ይላል! ትክክለኛ የእንግሊዝኛ አረፍተ ነገሮችን መናገር ጀምሬያለሁ፤ ነገ በአዲስ ቋንቋ እነጋገራለሁ … ከዚያም አዲሱን ሥራዬን እሠራለሁ! ተመስገን አምላኬ!
ልክ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ላይ በተመድ ሕንጻ በር ፊት ለፊት ሄጄ ቆሜያለሁ፡፡ ጋናዊ ዘበኛ እንግሊዝኛ በሚመስል ቋንቋ ሞቅ አድርጎ ሰላምታ ሰጠኝ፡፡ ‹‹እንደምን አደርሽ፣ ምን ልርዳሽ?›› ያለኝ ይመስለኛል፡፡ እኔ የሰማሁት ግን ‹‹ታታታ ታታታ ታታታታ?›› ዓይነት ነገር ነው፡፡ ምንም እንዳለ አንዳች ፍንጭ ባላገኝም የገባኝ አስመሰልኩ፡፡ ራሴን ከፍ፣ አገጬን ወጣ አድርጌ ‹‹እንዴት ነዎት? ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡ ሥራ ፈልጌ ነው›› አልኩ በእንግሊዝኛ፡፡
ውይ፡፡ የዓይኖቹ አኳኋን አነጋገሬ እንዴት አስቂኝ እንደሆነበት ነገረኝ፡፡ ቢሆንም ግን እንደገና ሞከርኩ፡፡ ይህን ሁሉ ርቀት የመጣሁት ተመለሽ ለመባል አልነበረም፡፡ ‹‹እንዴት ነዎት? ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡ ሥራ ፈልጌ ነው››
‹‹አሃ! ሩዋንዳዊት ነሽ… የምትችይው ፈረንሳይኛ መሆን አለበት›› አለኝ፡፡ ፈገግ ብዬ በአዎንታ ራሴን ነቀነቅሁ፡፡ ዋናውን በር ከፍቶልኝ ሌላ ዘበኛ ወደ አንዲት ትንሽ የእንግዳ መቀበያ ክፍል ወሰደኝ፤ ብዙ ቅጻቅጾችን ሞልቼ እንድጠብቅ ተነገረኝ፡፡ ጠበቅሁም … ጠበቅሁ… ጠበቅሁ … ጠበቅሁ፡፡ የተመድ ሠራተኞች ማታ ከሥራ ሲወጡ እንግዳ ተቀባይዋን ሥራውን እስካገኝ ምን ያክል መጠበቅ እንዳለብኝ ጠየኳት፡፡
‹‹ረጅም ጊዜ ትጠብቂያለሽ ውዴ … ሥራ የለም፡፡››
ወደ ቤቴ ተበሳጭቼ ግን ተስፋ ሳልቆርጥ ሄድኩ፡፡ በተመድ መሥራት ዕጣ ፈንታዬ - የማልመውና ቆርጬ የተነሣሁበት ጉዳይ ነው፡፡ ፈጣሪ እዚያ እንድሠራ ከፈቀደ ከግቤ ከመድረስ ምንም አያስቆመኝም፡፡
በቀጣዩም ቀን ተመለስኩ፣ እነዚያኑ ቅጾች ሞላሁና ከሰዓቱን ጠበቅሁ፡፡ በቀጣዩም ቀን ይህንኑ አደረግሁ፤ በቀጣዩም፤ በቀጣዩም፡፡ ቅጾችን ስሞላና ስጠብቅ ከሁለት ሳምንታት በላይ ፈጀሁ፡፡ በየቀኑ ወደ ቤቴ ስሄድ እንግዳ ተቀባይዋ ‹‹እኔ አንቺን ብሆን ተመልሼ አልመጣም ነበር ውዴ፡፡ ምንም ሥራ እኮ የለም›› ትለኛለች፡፡ በሁለተኛው ሳምንት መጨረሻ ተስፋዬ እየተሟጠጠ መጣ፡፡ ሥራ ሳላገኝ ወደ አሎይዜ ቤት መሄድ አስፈራኝ፡፡ ስለሆነም ለራሴ አዝኜ በቤታችን ሰፈር በፈራረሱ መንገዶች እዞር ገባሁ፡፡ በራሴ ዐቅም ላይ ለማተኮር ከአምላክ ጋር ጸጥታ የተሞላበት ተግባቦት እያደረግሁ ለመቀመጥ ፈለግሁ፤ ለዚያ ተመስጦ ግን የአሎይዜ ቤት በጣም ረብሻ የሚበዛበት ነው፡፡ እርስዎ አመኑኝም አላመኙኝ ከአምላኬ ጋር ለሰዓታት ያለማቋረጥ የማወራበትን በቄሱ መታጠቢያ ክፍል ያሳለፍኩትን ወቅት ናፈቅሁ፡፡ በነዚያ ረጃጅም ጸጥ ያሉ ጸሎቶቼ ወቅት ልቤን የሞላበትን ደስታና ሰላም አስታወስኩ
- ከዚያ በኋላ አገኝ የነበረውን የአእምሮ ንጽሕናም ጭምር፡፡
ከአሎይዜ ቤት ሁለት ግቢ አልፎ ወደተቃጠለ ቤት ፍርሥራሽ ሄድኩ፡፡ በጉልበቶቼ በተቃጠለው ፍርሥራሽና በተሰባበረው መስታወት ላይ ተንበርክኬ ጸሎቶቼን ጀመርኩ፡፡ ‹‹እግዚአብሔር ሆይ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ጴጥሮስ ሌሊቱን ሙሉ ዐሳ ለማጥመድ ቢሞክርም ምንም ሳይዝ ቀርቶ ተስፋው ቢሟጠጥ፤ አንተ ግን በዚያው ቦታ ላይ ሄዶ እንዲያጠምድ ነገርከው - እናም ብዙ ዐሳ አጠመደ! በጣም ደስተኛም ሆነ! እኔንም ታዲያ ወደ ተመድ ስለመራኸኝ እስካሁን ይህን ሁሉ ቀን ሥራ ‹እንዳጠመድኩ› አለሁ፡፡ ግን ምንም ዓሶች እዚህ የሉም፡፡ እግዚአብሔር፣ ምን እንደማደርግ አላውቅም፡፡ ገንዘብ የለኝም፤ ልብሶቼ እየተበጣጠሱ ነው፤ ሥራም አያስገኙኝም፡፡ ስለዚህ እገዛህን እፈልጋለሁ፡፡ እነዚህን የተመድ ሰዎች እንዲያዩኝና ጥሩ የጽሕፈት ቤት ሥራ እንዲሰጡኝ አድርግ፤ አንተ እንደምፈልገው ታውቃለህ፡፡ አግዘኝ፤ እኔም በበኩሌ ራሴን አግዛለሁ! ይሁን ይደረግልኝ፡፡››
ራሴን አጸዳድቼና የፈራረሰውን ቤት ትቼ በታደሰ የራስ መተማመን ሄድኩ፡፡ እግዚአብሔርን እገዛውን ጠየቅሁት፤ የምፈልገው አሁን እንዲከሰት ማድረጉ የራሴ ድርሻ እንደሆነ ታውቆኛል፡፡ በተመድ መሥራት የምፈልገውን በአእምሮዬ መቅረጽ ጀመርኩ - ማስታወሻ መያዝ፣ ስልክ መመለስና ጠቃሚ ውሳኔዎች ሲደረጉ ማገዝ፡፡ ወደ ቤት ስሄድ የተመዱን ሥራዬን አንዴ ካገኘሁ በኋላ ስለሚያስፈልጉኝ ነገሮች ሳስብ ቆየሁ፡፡ የተወሰኑ ለሰው ፊት የሚቀርቡ ልብሶች ሊኖሩኝ ይገባል፤ እናም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ያጠናቀኩበት ምስክር ወረቀትና ዩኒቨርሲቲ ለሦስት ዓመታት መከታተሌን የሚያረጋግጥ መረጃ ያስፈልጉኛል፡፡ ያለመታደል ሆኖ ሁሉም ንብረቶቼ አራት ሰዓት በተሽከርካሪ በሚያስነዳው ቡታሬ በሚገኘው በትምህርት ቤት የመኝታ ክፍሌ ናቸው፤ እንደሚታወቀው ወደዚያ ለመሄድ ደግሞ የምከፍለው ገንዘብ የለኝም፡፡
በሐሳብ በጣም ተውጬ አንድ ተሸከርካሪ በአጠገቤ አልፎ ነጂው ስሜን ሲጣራ ልብ አላልኩትም ማለት እችላለሁ - በዩኒቨርሲቲዬ መምህር የሆነው ዶክተር አቤል፡፡ ‹‹መች አወቅሁሽ ኢማኪዩሌ›› አለኝ፡፡ በጣም ከስተሻል! በመትረፍሽ በጣም ተደስቻለሁ … እንዲያው ምግብስ እየበላሽ ነው? የምትኖሪበትስ ቦታ አለሽ?›› ዶክተር አቤል የህክምና ዶክተር በመሆኑ ስላለፍኩበት ሁኔታና ስለጤናዬ ጉዳይ ጠየቀኝ፡፡ ለማገገም እንዲያግዘኝ ከእርሱ፣ ከሚስቱና ከቤተሰቡ ጋር ቡታሬ እንድኖር ቢጋብዘኝም አመስግኜው የምቆይባቸው ቤተሰብ እንዳሉኝ ነገርኩት፡፡ በቅርቡ ግን ቡታሬ የሚሄድ ከሆነ እንዲወስደኝ ነገርኩት፡፡
‹‹ምን ችግር አለ? በእርግጥ ነገ ሂያጅ ነኝ፡፡››
እንደገና የዕድል ገጠመኝ ነው ብዬ ባሰብኩት በዚህ ጉዳይ የአምላክን
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ስድስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#የጌታዬ_ሥራ
፡
ሰዎች በመንገድ ላይ ለመዘዋወር እንኳን በሚፈሩበት ከተማ ሥራ የት እንደማገኝ የሚያውቀው አምላክ ነው፡፡ ውድቅዳቂ ፈንጂዎች የኪጋሊን መንገዶች ሞልተዋቸዋል፤ ለመሥራት ከፈለግሁ ግን በነዚህ ጎዳናዎች ሥራን እያነፈነፍኩ መኳተን ይኖርብኛል፡፡ የሕዝብ ማጓጓዣ ተሸከርካሪዎች መንቀሳቀሳቸውን ትተዋል፤ ለአነስተኞቹም ማጓጓዣዎች የምከፍለው ምንም ገንዘብ አልነበረኝም፡፡
ፋሪን በቤቱ አቅራቢያ ያሉ ክፍት የሥራ ቦታ ያላቸውን ድርጅቶችን ያውቅ እንደሆነ ጠየቅሁት፡፡ ‹‹አሁን ማንም እየቀጠረ ስላልሆነ አማራጮችሽ በጣም ውሱን ናቸው›› ሲል መለሰልኝ፡፡ ‹‹ያለው ብቸኛ አማራጭ የተመድ ነው … እዚያ ለመግባት ግን እንግሊዝኛ መናገር ያስፈልጋል፡፡››
በአእምሮዬ የሆነ ነገር ብልጭ አለልኝ፡፡ በእርግጥ! እግዚአብሔር በመታጠቢያ ክፍሉ እንግሊዝኛ እንዳጠና ያደረገኝ ዋነኛው ምክንያት እኮ የተመድ ነው፡፡ በተመድ የመሥራት ሕልምም ነበረኝ፡፡
በዚያን ምሽት ልብሶቼን በሚገባ አጥቤ አምላክ በተመድ ሥራ እንዳገኝ ያግዘኝ ዘንድ ጸለይኩ፡፡ በመጨረሻ እንግሊዝኛዬን በሥራ ላይ የማውልበት መሆኑን አስቤ በጣም ተደስቼ አብዛኛውን የሌሊቱን ጊዜ መስታወት ሳይና ራሴን በራሴ ያስተማርኳቸውን ሐረጋት ስለማመድ ቆየሁ፡፡
‹‹እንደምን አደራችሁ››
‹‹እንዴት ነዎት?››
‹‹ሥራ ፈልጌ ነው፡፡›› ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡››
‹‹ሩዋንዳዊት ነኝ፡፡››
‹‹ቡታሬ ባለው ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ አጥንቻለሁ፡፡››
‹‹ሥራ ፈልጌ ነው፡፡››
አቤት! እንዴት ደስ ይላል! ትክክለኛ የእንግሊዝኛ አረፍተ ነገሮችን መናገር ጀምሬያለሁ፤ ነገ በአዲስ ቋንቋ እነጋገራለሁ … ከዚያም አዲሱን ሥራዬን እሠራለሁ! ተመስገን አምላኬ!
ልክ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ላይ በተመድ ሕንጻ በር ፊት ለፊት ሄጄ ቆሜያለሁ፡፡ ጋናዊ ዘበኛ እንግሊዝኛ በሚመስል ቋንቋ ሞቅ አድርጎ ሰላምታ ሰጠኝ፡፡ ‹‹እንደምን አደርሽ፣ ምን ልርዳሽ?›› ያለኝ ይመስለኛል፡፡ እኔ የሰማሁት ግን ‹‹ታታታ ታታታ ታታታታ?›› ዓይነት ነገር ነው፡፡ ምንም እንዳለ አንዳች ፍንጭ ባላገኝም የገባኝ አስመሰልኩ፡፡ ራሴን ከፍ፣ አገጬን ወጣ አድርጌ ‹‹እንዴት ነዎት? ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡ ሥራ ፈልጌ ነው›› አልኩ በእንግሊዝኛ፡፡
ውይ፡፡ የዓይኖቹ አኳኋን አነጋገሬ እንዴት አስቂኝ እንደሆነበት ነገረኝ፡፡ ቢሆንም ግን እንደገና ሞከርኩ፡፡ ይህን ሁሉ ርቀት የመጣሁት ተመለሽ ለመባል አልነበረም፡፡ ‹‹እንዴት ነዎት? ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡ ሥራ ፈልጌ ነው››
‹‹አሃ! ሩዋንዳዊት ነሽ… የምትችይው ፈረንሳይኛ መሆን አለበት›› አለኝ፡፡ ፈገግ ብዬ በአዎንታ ራሴን ነቀነቅሁ፡፡ ዋናውን በር ከፍቶልኝ ሌላ ዘበኛ ወደ አንዲት ትንሽ የእንግዳ መቀበያ ክፍል ወሰደኝ፤ ብዙ ቅጻቅጾችን ሞልቼ እንድጠብቅ ተነገረኝ፡፡ ጠበቅሁም … ጠበቅሁ… ጠበቅሁ … ጠበቅሁ፡፡ የተመድ ሠራተኞች ማታ ከሥራ ሲወጡ እንግዳ ተቀባይዋን ሥራውን እስካገኝ ምን ያክል መጠበቅ እንዳለብኝ ጠየኳት፡፡
‹‹ረጅም ጊዜ ትጠብቂያለሽ ውዴ … ሥራ የለም፡፡››
ወደ ቤቴ ተበሳጭቼ ግን ተስፋ ሳልቆርጥ ሄድኩ፡፡ በተመድ መሥራት ዕጣ ፈንታዬ - የማልመውና ቆርጬ የተነሣሁበት ጉዳይ ነው፡፡ ፈጣሪ እዚያ እንድሠራ ከፈቀደ ከግቤ ከመድረስ ምንም አያስቆመኝም፡፡
በቀጣዩም ቀን ተመለስኩ፣ እነዚያኑ ቅጾች ሞላሁና ከሰዓቱን ጠበቅሁ፡፡ በቀጣዩም ቀን ይህንኑ አደረግሁ፤ በቀጣዩም፤ በቀጣዩም፡፡ ቅጾችን ስሞላና ስጠብቅ ከሁለት ሳምንታት በላይ ፈጀሁ፡፡ በየቀኑ ወደ ቤቴ ስሄድ እንግዳ ተቀባይዋ ‹‹እኔ አንቺን ብሆን ተመልሼ አልመጣም ነበር ውዴ፡፡ ምንም ሥራ እኮ የለም›› ትለኛለች፡፡ በሁለተኛው ሳምንት መጨረሻ ተስፋዬ እየተሟጠጠ መጣ፡፡ ሥራ ሳላገኝ ወደ አሎይዜ ቤት መሄድ አስፈራኝ፡፡ ስለሆነም ለራሴ አዝኜ በቤታችን ሰፈር በፈራረሱ መንገዶች እዞር ገባሁ፡፡ በራሴ ዐቅም ላይ ለማተኮር ከአምላክ ጋር ጸጥታ የተሞላበት ተግባቦት እያደረግሁ ለመቀመጥ ፈለግሁ፤ ለዚያ ተመስጦ ግን የአሎይዜ ቤት በጣም ረብሻ የሚበዛበት ነው፡፡ እርስዎ አመኑኝም አላመኙኝ ከአምላኬ ጋር ለሰዓታት ያለማቋረጥ የማወራበትን በቄሱ መታጠቢያ ክፍል ያሳለፍኩትን ወቅት ናፈቅሁ፡፡ በነዚያ ረጃጅም ጸጥ ያሉ ጸሎቶቼ ወቅት ልቤን የሞላበትን ደስታና ሰላም አስታወስኩ
- ከዚያ በኋላ አገኝ የነበረውን የአእምሮ ንጽሕናም ጭምር፡፡
ከአሎይዜ ቤት ሁለት ግቢ አልፎ ወደተቃጠለ ቤት ፍርሥራሽ ሄድኩ፡፡ በጉልበቶቼ በተቃጠለው ፍርሥራሽና በተሰባበረው መስታወት ላይ ተንበርክኬ ጸሎቶቼን ጀመርኩ፡፡ ‹‹እግዚአብሔር ሆይ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ጴጥሮስ ሌሊቱን ሙሉ ዐሳ ለማጥመድ ቢሞክርም ምንም ሳይዝ ቀርቶ ተስፋው ቢሟጠጥ፤ አንተ ግን በዚያው ቦታ ላይ ሄዶ እንዲያጠምድ ነገርከው - እናም ብዙ ዐሳ አጠመደ! በጣም ደስተኛም ሆነ! እኔንም ታዲያ ወደ ተመድ ስለመራኸኝ እስካሁን ይህን ሁሉ ቀን ሥራ ‹እንዳጠመድኩ› አለሁ፡፡ ግን ምንም ዓሶች እዚህ የሉም፡፡ እግዚአብሔር፣ ምን እንደማደርግ አላውቅም፡፡ ገንዘብ የለኝም፤ ልብሶቼ እየተበጣጠሱ ነው፤ ሥራም አያስገኙኝም፡፡ ስለዚህ እገዛህን እፈልጋለሁ፡፡ እነዚህን የተመድ ሰዎች እንዲያዩኝና ጥሩ የጽሕፈት ቤት ሥራ እንዲሰጡኝ አድርግ፤ አንተ እንደምፈልገው ታውቃለህ፡፡ አግዘኝ፤ እኔም በበኩሌ ራሴን አግዛለሁ! ይሁን ይደረግልኝ፡፡››
ራሴን አጸዳድቼና የፈራረሰውን ቤት ትቼ በታደሰ የራስ መተማመን ሄድኩ፡፡ እግዚአብሔርን እገዛውን ጠየቅሁት፤ የምፈልገው አሁን እንዲከሰት ማድረጉ የራሴ ድርሻ እንደሆነ ታውቆኛል፡፡ በተመድ መሥራት የምፈልገውን በአእምሮዬ መቅረጽ ጀመርኩ - ማስታወሻ መያዝ፣ ስልክ መመለስና ጠቃሚ ውሳኔዎች ሲደረጉ ማገዝ፡፡ ወደ ቤት ስሄድ የተመዱን ሥራዬን አንዴ ካገኘሁ በኋላ ስለሚያስፈልጉኝ ነገሮች ሳስብ ቆየሁ፡፡ የተወሰኑ ለሰው ፊት የሚቀርቡ ልብሶች ሊኖሩኝ ይገባል፤ እናም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ያጠናቀኩበት ምስክር ወረቀትና ዩኒቨርሲቲ ለሦስት ዓመታት መከታተሌን የሚያረጋግጥ መረጃ ያስፈልጉኛል፡፡ ያለመታደል ሆኖ ሁሉም ንብረቶቼ አራት ሰዓት በተሽከርካሪ በሚያስነዳው ቡታሬ በሚገኘው በትምህርት ቤት የመኝታ ክፍሌ ናቸው፤ እንደሚታወቀው ወደዚያ ለመሄድ ደግሞ የምከፍለው ገንዘብ የለኝም፡፡
በሐሳብ በጣም ተውጬ አንድ ተሸከርካሪ በአጠገቤ አልፎ ነጂው ስሜን ሲጣራ ልብ አላልኩትም ማለት እችላለሁ - በዩኒቨርሲቲዬ መምህር የሆነው ዶክተር አቤል፡፡ ‹‹መች አወቅሁሽ ኢማኪዩሌ›› አለኝ፡፡ በጣም ከስተሻል! በመትረፍሽ በጣም ተደስቻለሁ … እንዲያው ምግብስ እየበላሽ ነው? የምትኖሪበትስ ቦታ አለሽ?›› ዶክተር አቤል የህክምና ዶክተር በመሆኑ ስላለፍኩበት ሁኔታና ስለጤናዬ ጉዳይ ጠየቀኝ፡፡ ለማገገም እንዲያግዘኝ ከእርሱ፣ ከሚስቱና ከቤተሰቡ ጋር ቡታሬ እንድኖር ቢጋብዘኝም አመስግኜው የምቆይባቸው ቤተሰብ እንዳሉኝ ነገርኩት፡፡ በቅርቡ ግን ቡታሬ የሚሄድ ከሆነ እንዲወስደኝ ነገርኩት፡፡
‹‹ምን ችግር አለ? በእርግጥ ነገ ሂያጅ ነኝ፡፡››
እንደገና የዕድል ገጠመኝ ነው ብዬ ባሰብኩት በዚህ ጉዳይ የአምላክን
👍4