#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታረ
“ሶራ ልታስብበት ይገባል" አለችው በጥሞና እያየችው፡
"ወደ ኢትዮጵያ አብሬሽ ልሂድና የአያትሽን የትውልድ ቦታ ላፈላልግሽ እፈልጋለሁ፡፡ ያሳየሽኝ መቀመጫ ታችኛው የኦሞ ወንዝ አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ማህበረሰቦች በሙሉ ይጠቀሙበታል። ኤርቦሬ
ሐመር በና ካሮ መቀመጫው በእርግጥም የኦሞ ህዝቦች ብቻ
እንደሆነ አምናላሁ" አላት።
ጥሩ! እኔ የተዘጋጀሁት ለአንድ ሰው በሚበቃ ባጀት ነው" በግልፅ ችግሯን ገለፀችለት፡
“እኔ ደግሞ የራሴን እችላለሁ በዚያ በኩል አታስቢ"
አመሠግናለሁ ሶራ በእውነት አንተን ማግኘቴ ያላሰብሁት
እድል ነው" ብላ ፈገግ አለችለት::
ሶራና ኮንችት በዚህ መልክ ለአፍሪካ ጉዞዋቸው
መሰናዶአቸውን አብረው ቀጠሉ፡፡
ከሁዌልቫ ሊዝበን በመርከብ የሚፈጀወ ጊዜ ግማሽ ቀን ብቻ ነው፡፡ ከጅበላርታር ለንደን በሚወስደው የጉዞ መስመር መርከቡ
አቅጣጫውን ካስተካከለ በኋላ ተጓዡ እንደየግል ፍላጎቱ ተሰማራ፡፡
ኮንችትና ሶራ በመርhቡ ግራ ጎን ባለው ማማ ላይ ወጥተው በርቀት የተዘረጋውን የአትላንቲክ ውቅያኖስ እያዩ ተቀምጠዋል፡፡
ኮንችትና ሶራ የለበሱት ነጭ ቲሸርት ነው፡፡ በሁለቱ መካከል የአለባበስ ልዩነቱ ኮንችት ነጭ አጭር ቀሚስ በሰፊ ቀበቶ ሶራ
ደግሞ ቡላ ሲልክ ሱሪ መልበሳቸው ነው፡፡ ሁለቱም ጥቁር የፀሐይ መነፅር አድርገዋል። ቀኑ ሞቃታማና ፀሐያማ ነው፡፡
ወደ ሊዝበን የመሄዱን ሐሳብ ያመጣችው ኮንችት ናት ሶራን የተለያዩ ቦታዎችን ሙዚዬሞችን ታሪካዊ ቦታዎችን መዝናኛዎችን… እንዲያይ ብዙ ጊዜ እየጋበዘች ወስዳዋለች፡፡
ስለ ፖርቹጋሎች ምን ታውቃለህ?" አለችው አንድ ቀን በማድሪድ ከተማ መናፈሻ ውስጥ እንደተቀመጡ፡፡
“ባህረተኞችና ቅኝ ገዥዎች እንደነበሩ"
“አዎ! ፖርቹጋሎች ማንም እሚያውቃቸው በባህር ላይ
ህይወታቸውና ለቅኝ ገዥነት በብዙው የዓለም ክፍል በተለይም በአፍሪካና በላቲን አሜሪካ ያደርጉት የነበረውን ቅኝት ነው፡ ይህ ጥንት ሌላው ስለእነሱ ያውቅ የነበረው እውቀት ነው በአሁን ሰዓት ግን ፖርቹጋል ብዙ ቱሪስት የሚስተናገድባት አገር ናት።
“ሙዚየሞቻቸው የዓለምን ቅርስ የያዙ ናቸው ይባላል።
ስለ ዓለም ይበልጥ ማወቅ የማፈልገው ይህ ትውልድ ደግሞ ቅርሶች አሉ የተባለበት መጉረፉ የተለመደ ነው፡፡
“አፍሪካ የራሷ ካሏት ቅርሶች ይልቅ በአውሮፓ ያሏት ቅርሶች ይበልጣሉ፡ የሚያሳዝነው ግን አፍሪካ ለቅርሷ የባለቤትነት
መብት የላትም፡፡ በኮለኒያሊስቶች የተዘረፈችው ቅርስ አሁንም የእነሱ ኪስ ማድለቢያ ነው፡፡
“ከኢትዮጵያ የመጡ
ቅርሶች ከዚህ በፊት ፈረንሳይ እንግሊዝ ጣሊያን… ሄጄ አይቻለሁ፡፡ ፖርቹጋልም እንደዚሁ ብዙ
የሃይማኖት መጽሐፍትና የታሪክ ቅርሶች አሉ: አንዳንዴ ሳስበው እንዲያውም ኢትዮጵያውያን
የታሪክ የባህል ተመራማሪዎች ወደ ፊት በአገራቸው ታሪክና ባህል ላይ ምርምር ማድረግ ቢፈልጉ ዋቢ ቅርሶችን ለማየት ወደ አውሮፓ ብቅ ማለታቸው የግድ
ይመስለኛል
“አውሮፖና በሌላው የሰለጠነው ዓለም አንድ ወቅት የቅርስ ዝርፊያ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን በስምምነት አንዱ ዘንድ ያለው ወደ ሌላው እየተመለሰ ነው። ባይመለስ እንኳን የዛ ቅርስ ባለቤት
የሚሆነው በመጀመሪያ ባለቤት የነበረው አገር ነው፡፡ ለዚህ ውጤት
ግን ብዙዎች ልሳናቸው እስኪዘጋ እየጮሁ ታግለዋል፡፡ ግዞት ስደት
እስራትም ደርሶባቸዋል: አሁን ግን ቀስ በቀስ ህልማቸው እውን
እየሆነ ነው:
ሶራ አንተም ፖርቹጋል ያሉትን ሙዚየሞች ስታይ
እርግጠኛ ነኝ ብዙ የአገርህን ቅርሶች ታያለህ የኢትዮጵያ ቅርሶች
የሚል ጽሁፍ ግን አይታይባቸውም፡፡ አንድ እውነት ግን በህሊናህ
ይመጣል! ቅርስ ለአንድ ሀገር ህዝብ ማንነት ምን ያህል አስፈላጊ
መሆኑን ትገነዘባለህ፡፡
የአውሮፓውያን ስልጣኔ ባሰባሰቡት ቅርስ ላይ የተመስረተ ነው ለቅርሶች ልዩ ከበሬታ መስጠትም የአንድ ሃገር ስልጣኔያዊ
ብስለት መለኪያ ነው፡
“ሶራ ስለ! ሌላውን ለማወቅ ከሌላው ለመማር ራስሀን
ለማነፃዐር ያጣኸውን ለመፈለግ… ጉብኝት አስፈላጊ ነው" አለችው፡፡
ልክ ነሽ ኮንችት ለምን ለጊዜው ፖርቹጋልን አብረን
አናይም?” አላት፡
“በደስታ! ሶራ" ብላ ሳቋን ለቀቀችው: ኪሊሊ... የሚለውን ሳቋን ሰማው: ናፍቆት ነበር ሣቋ::
“ሳቅሽ ደስ ይለኛል አላት ፈገግ ብሎ፡፡
“አመለግናለሁ” አለችው። ኪሊሊ ብላ እየሳቀች:: እያያት አሰበ: ሌላውን ማወቅ ነው….. የተናገረችውን አስታወሰ፡
አውሮፓውያን ስልጣኔ ባሰባሰቡት ቅርስ ላይ የተመሰተ ነው ገረመው: በልተህ በልተህ ወደ አገርህ አንጋጥ ተሪቱማ እሱም
አገር አለ፡፡ ተግባሩ ግን ጠፋ፡፡ ሌላው እስኪጀምረው መጠበቅ አንዱ የአፍሪካውያን ችግር ነው። እና የሚጠቅመውን ሁሉ ለአገሩ ጆሮ
ለማድረስ ለአገሩ ሕዝብ ለማሳየት የተማረውን ዜጋ ህሊና ለማንኳኪያ ከእንቅልፍ ለመቀስቀሻ ሊጠቀምበት እንደሚገባ ቃል ገባ: እራሱን ግን ተጠራጠረው “ፍርፋሬ ያዘናጋኝ ይሆን?” አለ።
ኮንችት ያለውን አልሰማችም፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሁለቱ መንገደኞች መርከቡ ጉዞ ከጀመረ በኋላ
ጨዋታቸውን ጀመሩ፡፡
“…ለወላጆቼ የመጀመሪያ ነኝ፡ ከኔ በታች ሁለት ታናናሽ
ወንድሞች አሉኝ፡ በተለይ ከኔ ተከታይ ጋር በሰፊ አልጋ አብረን ነበር የምንተኛው።
አባቴ ፍራንሲስኮ ፔሶ ቤኒ ለወደፊቱ መፃኢ እድላችን
ስለሚያስብ ገንዘብ ለማስቀመጥ ቢጥርም ግማሽ ኢትዮጵያዊቷ እናቱ
ካሪና ግን ለግል ውበቷ ብቻ የምትጪነቅ አባካኝ በመሆኗ አባቴ
እንዳሰበው ገንዘብ የማስቀመጥ ህልሙ አልሳካ ሲለው በእናቴና
በአባቴ መካከል አለመጣጣሙ እየበዛ በመምጣቱ ተለያዩ በዚህ
ሳቢያ አባቴ ወደ ቤታችን የሚመጣው በጣም እየቆዬ ሆነ፡ እኔ ደግሞ የመጀመሪያ ልጅ እንደመሆኔ መጠን የአባቴን ፍቅር በምሻበት
ወቅት ላገኘው ባለመቻሌ ከልቤ ጠላሁት ስለዚህ ከአባቴ ይልቅ ለኢትዮያዊው አያቴ ለሎካዬ ሆነ ፍቅሬ” ብላ ክሊሊ… ብላ ሳቀች
እሱም ፈገግ አለ ጉሮሮዋን ለማራስ የቆርቆሮ ቢራዋን ለመክፈት ዘወር ስትል የቢራው ቆርቆሮ ወደቀባት ለማንሳት ጎንበስ ስትል
አየው ጥቁር ፓንቷን
አፈር አለና ፊቱን ወደ አትላንቲክ ውቂያኖስ አዙሮ
ሲመለከት hርቀት የሆነ ብረት አዬ
ኮንችት ተመልከች ያ ምንድው?” አላት።
መርከብ ነው የመሬት ክብነትን ስትማር ስለዚህ
አልተማርህም..."
አዎ አሁን ትዝ አለኝ: ሳታይ የተማርሽው ቶሎ
ይዘነጋል እሽ ጨዋታሽን ቀጥይ? አላት አንጋጣ አንዴ ጉንጯን ሞልታ ተጎነጨችና
"ኧህ ብላ ጨዋታዋን ያቆመችበትን አሰብ በማድረግ
ቸበርቻቻ ወዳጅዋን እናቴን ግን እወዳት ነበር በፊት
እንነገርሁህ በቁመናዬ ሳቢያ በትርፍ ጊዜዬ የግል ገቢ ማግኘት የጀመርሁት ገና በህፃንነቴ ቢሆንም እናቴ እናደ ሌሉች ልጆች
አስባ ልብስ ስለማትገልኝና ከሷ የምጠብቀውን አንድም ቀን "ቆንጆ ብላኝ ስለማታውቅ ለእሷ የነበረኝ ፍቅር እየሟሽሽ የጥላቻ
ስሜት ህሊናዬን ይተናነቀው ጀመር አንድ ቀን እንዲያውም አባቴ ጠፍቶ ከርሞ በመጣበት አጋጣሚ
እናቴና አባቴ አንድ ላይ በሚገኙበት ወቅት ጠባቂ በነበረኝ ገንዘብ ላይ ስጦታ ገዝቼ አልጋቸው ላይ አስቀመጥኩላቸ
ንግግሯን ሳትጨርስ ሶራ
አቋረጣትና
ይቅታ ስላቋረጥኩሽ የዚያን ጊዜ የስንት ዓመት ልጅ ነበረሽ።
ምናልባት የአስራ አራት ዓመት ከዚያ አይበልጠኝም
አለችው።
እሽ ቀጥይ አላት ሶራ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታረ
“ሶራ ልታስብበት ይገባል" አለችው በጥሞና እያየችው፡
"ወደ ኢትዮጵያ አብሬሽ ልሂድና የአያትሽን የትውልድ ቦታ ላፈላልግሽ እፈልጋለሁ፡፡ ያሳየሽኝ መቀመጫ ታችኛው የኦሞ ወንዝ አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ማህበረሰቦች በሙሉ ይጠቀሙበታል። ኤርቦሬ
ሐመር በና ካሮ መቀመጫው በእርግጥም የኦሞ ህዝቦች ብቻ
እንደሆነ አምናላሁ" አላት።
ጥሩ! እኔ የተዘጋጀሁት ለአንድ ሰው በሚበቃ ባጀት ነው" በግልፅ ችግሯን ገለፀችለት፡
“እኔ ደግሞ የራሴን እችላለሁ በዚያ በኩል አታስቢ"
አመሠግናለሁ ሶራ በእውነት አንተን ማግኘቴ ያላሰብሁት
እድል ነው" ብላ ፈገግ አለችለት::
ሶራና ኮንችት በዚህ መልክ ለአፍሪካ ጉዞዋቸው
መሰናዶአቸውን አብረው ቀጠሉ፡፡
ከሁዌልቫ ሊዝበን በመርከብ የሚፈጀወ ጊዜ ግማሽ ቀን ብቻ ነው፡፡ ከጅበላርታር ለንደን በሚወስደው የጉዞ መስመር መርከቡ
አቅጣጫውን ካስተካከለ በኋላ ተጓዡ እንደየግል ፍላጎቱ ተሰማራ፡፡
ኮንችትና ሶራ በመርhቡ ግራ ጎን ባለው ማማ ላይ ወጥተው በርቀት የተዘረጋውን የአትላንቲክ ውቅያኖስ እያዩ ተቀምጠዋል፡፡
ኮንችትና ሶራ የለበሱት ነጭ ቲሸርት ነው፡፡ በሁለቱ መካከል የአለባበስ ልዩነቱ ኮንችት ነጭ አጭር ቀሚስ በሰፊ ቀበቶ ሶራ
ደግሞ ቡላ ሲልክ ሱሪ መልበሳቸው ነው፡፡ ሁለቱም ጥቁር የፀሐይ መነፅር አድርገዋል። ቀኑ ሞቃታማና ፀሐያማ ነው፡፡
ወደ ሊዝበን የመሄዱን ሐሳብ ያመጣችው ኮንችት ናት ሶራን የተለያዩ ቦታዎችን ሙዚዬሞችን ታሪካዊ ቦታዎችን መዝናኛዎችን… እንዲያይ ብዙ ጊዜ እየጋበዘች ወስዳዋለች፡፡
ስለ ፖርቹጋሎች ምን ታውቃለህ?" አለችው አንድ ቀን በማድሪድ ከተማ መናፈሻ ውስጥ እንደተቀመጡ፡፡
“ባህረተኞችና ቅኝ ገዥዎች እንደነበሩ"
“አዎ! ፖርቹጋሎች ማንም እሚያውቃቸው በባህር ላይ
ህይወታቸውና ለቅኝ ገዥነት በብዙው የዓለም ክፍል በተለይም በአፍሪካና በላቲን አሜሪካ ያደርጉት የነበረውን ቅኝት ነው፡ ይህ ጥንት ሌላው ስለእነሱ ያውቅ የነበረው እውቀት ነው በአሁን ሰዓት ግን ፖርቹጋል ብዙ ቱሪስት የሚስተናገድባት አገር ናት።
“ሙዚየሞቻቸው የዓለምን ቅርስ የያዙ ናቸው ይባላል።
ስለ ዓለም ይበልጥ ማወቅ የማፈልገው ይህ ትውልድ ደግሞ ቅርሶች አሉ የተባለበት መጉረፉ የተለመደ ነው፡፡
“አፍሪካ የራሷ ካሏት ቅርሶች ይልቅ በአውሮፓ ያሏት ቅርሶች ይበልጣሉ፡ የሚያሳዝነው ግን አፍሪካ ለቅርሷ የባለቤትነት
መብት የላትም፡፡ በኮለኒያሊስቶች የተዘረፈችው ቅርስ አሁንም የእነሱ ኪስ ማድለቢያ ነው፡፡
“ከኢትዮጵያ የመጡ
ቅርሶች ከዚህ በፊት ፈረንሳይ እንግሊዝ ጣሊያን… ሄጄ አይቻለሁ፡፡ ፖርቹጋልም እንደዚሁ ብዙ
የሃይማኖት መጽሐፍትና የታሪክ ቅርሶች አሉ: አንዳንዴ ሳስበው እንዲያውም ኢትዮጵያውያን
የታሪክ የባህል ተመራማሪዎች ወደ ፊት በአገራቸው ታሪክና ባህል ላይ ምርምር ማድረግ ቢፈልጉ ዋቢ ቅርሶችን ለማየት ወደ አውሮፓ ብቅ ማለታቸው የግድ
ይመስለኛል
“አውሮፖና በሌላው የሰለጠነው ዓለም አንድ ወቅት የቅርስ ዝርፊያ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን በስምምነት አንዱ ዘንድ ያለው ወደ ሌላው እየተመለሰ ነው። ባይመለስ እንኳን የዛ ቅርስ ባለቤት
የሚሆነው በመጀመሪያ ባለቤት የነበረው አገር ነው፡፡ ለዚህ ውጤት
ግን ብዙዎች ልሳናቸው እስኪዘጋ እየጮሁ ታግለዋል፡፡ ግዞት ስደት
እስራትም ደርሶባቸዋል: አሁን ግን ቀስ በቀስ ህልማቸው እውን
እየሆነ ነው:
ሶራ አንተም ፖርቹጋል ያሉትን ሙዚየሞች ስታይ
እርግጠኛ ነኝ ብዙ የአገርህን ቅርሶች ታያለህ የኢትዮጵያ ቅርሶች
የሚል ጽሁፍ ግን አይታይባቸውም፡፡ አንድ እውነት ግን በህሊናህ
ይመጣል! ቅርስ ለአንድ ሀገር ህዝብ ማንነት ምን ያህል አስፈላጊ
መሆኑን ትገነዘባለህ፡፡
የአውሮፓውያን ስልጣኔ ባሰባሰቡት ቅርስ ላይ የተመስረተ ነው ለቅርሶች ልዩ ከበሬታ መስጠትም የአንድ ሃገር ስልጣኔያዊ
ብስለት መለኪያ ነው፡
“ሶራ ስለ! ሌላውን ለማወቅ ከሌላው ለመማር ራስሀን
ለማነፃዐር ያጣኸውን ለመፈለግ… ጉብኝት አስፈላጊ ነው" አለችው፡፡
ልክ ነሽ ኮንችት ለምን ለጊዜው ፖርቹጋልን አብረን
አናይም?” አላት፡
“በደስታ! ሶራ" ብላ ሳቋን ለቀቀችው: ኪሊሊ... የሚለውን ሳቋን ሰማው: ናፍቆት ነበር ሣቋ::
“ሳቅሽ ደስ ይለኛል አላት ፈገግ ብሎ፡፡
“አመለግናለሁ” አለችው። ኪሊሊ ብላ እየሳቀች:: እያያት አሰበ: ሌላውን ማወቅ ነው….. የተናገረችውን አስታወሰ፡
አውሮፓውያን ስልጣኔ ባሰባሰቡት ቅርስ ላይ የተመሰተ ነው ገረመው: በልተህ በልተህ ወደ አገርህ አንጋጥ ተሪቱማ እሱም
አገር አለ፡፡ ተግባሩ ግን ጠፋ፡፡ ሌላው እስኪጀምረው መጠበቅ አንዱ የአፍሪካውያን ችግር ነው። እና የሚጠቅመውን ሁሉ ለአገሩ ጆሮ
ለማድረስ ለአገሩ ሕዝብ ለማሳየት የተማረውን ዜጋ ህሊና ለማንኳኪያ ከእንቅልፍ ለመቀስቀሻ ሊጠቀምበት እንደሚገባ ቃል ገባ: እራሱን ግን ተጠራጠረው “ፍርፋሬ ያዘናጋኝ ይሆን?” አለ።
ኮንችት ያለውን አልሰማችም፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሁለቱ መንገደኞች መርከቡ ጉዞ ከጀመረ በኋላ
ጨዋታቸውን ጀመሩ፡፡
“…ለወላጆቼ የመጀመሪያ ነኝ፡ ከኔ በታች ሁለት ታናናሽ
ወንድሞች አሉኝ፡ በተለይ ከኔ ተከታይ ጋር በሰፊ አልጋ አብረን ነበር የምንተኛው።
አባቴ ፍራንሲስኮ ፔሶ ቤኒ ለወደፊቱ መፃኢ እድላችን
ስለሚያስብ ገንዘብ ለማስቀመጥ ቢጥርም ግማሽ ኢትዮጵያዊቷ እናቱ
ካሪና ግን ለግል ውበቷ ብቻ የምትጪነቅ አባካኝ በመሆኗ አባቴ
እንዳሰበው ገንዘብ የማስቀመጥ ህልሙ አልሳካ ሲለው በእናቴና
በአባቴ መካከል አለመጣጣሙ እየበዛ በመምጣቱ ተለያዩ በዚህ
ሳቢያ አባቴ ወደ ቤታችን የሚመጣው በጣም እየቆዬ ሆነ፡ እኔ ደግሞ የመጀመሪያ ልጅ እንደመሆኔ መጠን የአባቴን ፍቅር በምሻበት
ወቅት ላገኘው ባለመቻሌ ከልቤ ጠላሁት ስለዚህ ከአባቴ ይልቅ ለኢትዮያዊው አያቴ ለሎካዬ ሆነ ፍቅሬ” ብላ ክሊሊ… ብላ ሳቀች
እሱም ፈገግ አለ ጉሮሮዋን ለማራስ የቆርቆሮ ቢራዋን ለመክፈት ዘወር ስትል የቢራው ቆርቆሮ ወደቀባት ለማንሳት ጎንበስ ስትል
አየው ጥቁር ፓንቷን
አፈር አለና ፊቱን ወደ አትላንቲክ ውቂያኖስ አዙሮ
ሲመለከት hርቀት የሆነ ብረት አዬ
ኮንችት ተመልከች ያ ምንድው?” አላት።
መርከብ ነው የመሬት ክብነትን ስትማር ስለዚህ
አልተማርህም..."
አዎ አሁን ትዝ አለኝ: ሳታይ የተማርሽው ቶሎ
ይዘነጋል እሽ ጨዋታሽን ቀጥይ? አላት አንጋጣ አንዴ ጉንጯን ሞልታ ተጎነጨችና
"ኧህ ብላ ጨዋታዋን ያቆመችበትን አሰብ በማድረግ
ቸበርቻቻ ወዳጅዋን እናቴን ግን እወዳት ነበር በፊት
እንነገርሁህ በቁመናዬ ሳቢያ በትርፍ ጊዜዬ የግል ገቢ ማግኘት የጀመርሁት ገና በህፃንነቴ ቢሆንም እናቴ እናደ ሌሉች ልጆች
አስባ ልብስ ስለማትገልኝና ከሷ የምጠብቀውን አንድም ቀን "ቆንጆ ብላኝ ስለማታውቅ ለእሷ የነበረኝ ፍቅር እየሟሽሽ የጥላቻ
ስሜት ህሊናዬን ይተናነቀው ጀመር አንድ ቀን እንዲያውም አባቴ ጠፍቶ ከርሞ በመጣበት አጋጣሚ
እናቴና አባቴ አንድ ላይ በሚገኙበት ወቅት ጠባቂ በነበረኝ ገንዘብ ላይ ስጦታ ገዝቼ አልጋቸው ላይ አስቀመጥኩላቸ
ንግግሯን ሳትጨርስ ሶራ
አቋረጣትና
ይቅታ ስላቋረጥኩሽ የዚያን ጊዜ የስንት ዓመት ልጅ ነበረሽ።
ምናልባት የአስራ አራት ዓመት ከዚያ አይበልጠኝም
አለችው።
እሽ ቀጥይ አላት ሶራ
👍21